TIKVAH-ETHIOPIA
1.44M subscribers
55.9K photos
1.4K videos
202 files
3.77K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ትንሣኤ

ለመላው #የክርስትና_እምነት_ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ !

" በዚህ የለም ፤ እርሱ እንደተናገረው ተነሥቶአል "  


በማቴዎስ ወንጌል ፥ " እነሆ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ ወርዶአልና ፤ ቀርቦም በመቃብሩ አፍ ላይ ድንጋይዋን አንከባሎ በላይዋ ተቀመጠ፡፡

መልኩም እንደ መብረቅ ፤ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ነበር፡፡

እርሱንም ከመፍራት የተነሣ መቃብሩን የሚጠብቁ ታወኩ ፤ እንደ በድንም ሆኑ፡፡

መልአኩ መልሶ ሴቶቹን እንዲህ አላቸው፥ ' እናንተስ #አትፍሩ ፤ የተሰቀለውን #ኢየሱስን_እንደምትሹ አውቃለሁና፡፡ በዚህ የለም ፤ እርሱ እንደ ተናገረው ተነሥቶአል ' " ተብሎ እንደተጻፈው #መድኃኒዓለም ብርሃንን ተጎናጽፎ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን በክብር #ተነሥቶአል፡፡

መልካም የትንሣኤ በዓል !
በዓሉ የሰላምና የፍቅር ይሆን ዘንድ እንመኛለን !


#TikvahEthiopiaFamily❤️

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጎንደር ° “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም ” - የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ° “ ጉድጓድ ስናስቆፍር በ4 ወራት ይደርሳል ብለን አንድ ዓመት ከ8 ወራት ወስዷል ” - የከተማው ውሃና ፍሳሽ  በአማራ ክልል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ኢንተርን ሀኪሞች፣ የውሃ ችግር እንደፈተናቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። የከተማው ነዋሪዎች…
#Update

“ ‘ የ24 ሰዓት ሙሉ የውሃ አገልግሎት እንሰጣለን ’ የሚለው ውሸት ነው ” - የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቅሬታ አቅራቢዎች

“ ሆስፒታል ማለት ለተማሪ አይደለም የምንሰጠው። ሆስፓታሉ ማለት ህክምና የሚካሄድበት ነው ” - የከተማው ውሃና ፍሳሽ ቢሮ

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ኢንተርን ሀኪሞች እና ተማሪዎች የውሃ አቅርበት ከተቋረጠ ከወር በላይ ሆኖት እያለ የከተማው ውሃና ፍሳሽ ሰሞኑን የሰጠው ማብራሪያ ትክክል አለመሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በጎንደር ከተማ የውሃ አቅርቦት ችግር እንዳለ ነዋሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ ኢንተርን ሀኪሞች ቅሬታ ማቅረባቸው ይታወሳል።

በወቅቱ ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው የጎንደር ውሃና ፍሳሽ ቢሮ ፥ የከተማው ነዋሪዎች ቅሬታ ትክክል እንደሆነ አምኖ ለመፍትሄው መንግስት ርብርብ እንዲያደርግ አሳስቦ ነበር።

ቢሮው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ላይ የተነሳውን ቅሬታ በተመለከተ በሰጠው ምላሽ ግን፣ “ሆስፒታል ላይ ግን 24 ሰዓት ነው የምንሰጠው። መብራትና አጠቃላይ ምርት ቆሞ ካልሆነ አይቋረጥም” ነበር ያለው።

የዩኒቨርሲቲው የኢንተርን ሀኪሞቹ በሰጡት የአጸፋ ቃል፣ ‘የ24 ሰዓት የውሃ አገልግሎት እንሰጣለን’ የሚለው ውሸት ነው። እውነታው ውሃ የለም” ሲሉ ወቅሰዋል።

ውሃ በግቢ ከጠፋ ከወር በላይ እንደሆነው ገልጸው፣ እንኳን ለመጸዳጃ ለመጠጥ እንደተቸገሩና በቦቴ የሚቀርበውም አነስተኛ እንደሆነ አስረድተዋል።

የተነሳውን ቅሬታ በተመለከተ በድጋሚ የጠየቅናቸው የከተማው ውሃና ፍሳሽ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ አያል፣ "ሆስፒታል ማለት ለተማሪ አይደለም የምንሰጠው። ህክምና ለሚካሄድበት ነው" ብለዋል።

" በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በስኬጁል ነው የሚሰጣቸው ሌላው ማህበረሰብ በወር እያገኘ ለሀኪም 24 ሰዓት ልሰጠው አልችልም። ሆስፒታል ግን 24 ሰዓት ህክምና የሚካሄድበት ስለሆነ 24 ሰዓት ሙሉ ነው አሁንም የምንሰጠው" ነው ያሉት።

" ለሀኪሞች የራሳቸው ፕሮግራም አላቸው እንደሌላው ማህበረሰብ አይደሉም በእርግጥ በሳምንት፤ በ3፤ በ4 ቀናት ነው። ድሮ 24 ሰዓት ነበር የሚሰጣቸው። አሁን ግን የውሃ እጥረት ስላለ አንችልም " ሲሉ አክለዋል።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ልጆቻችን ... በማይናማር ! በርካታ የሀገራችን ልጆች ፦ - የወጣትነት እድሜያቸው ሳያልፍ ህይወታቸውን ለመቀየር፣ - ደክመው ያሳደጓቸውን ቤተሰቦቻቸውን ለማገዝ እንዲሁም፣ - እድሜያቸው ሳይገፋ ቤተሰብ መስርተው ጥሩ ኑሮ ለመኖር ሲሉ ወደ ተለያዩ ሀገራት ይሰደዳሉ። አንዳንዶቹ እጅግ አደገኛ ነው የተባለውን የህገወጥ ስደት በእግር ፣ በበረሃ ፣ በባህር አድርገው ይጓዛሉ። አንዳንዶች ደግሞ እዚሁ ሀገር…
ደላሎችም ይሁኑ ' ወደ ውጭ ሀገር እንልካችሏለን ' የሚሉ ኤጀንሲዎች የት እና ለምን ስራ እንደሚልኳቹ በደንብ አጣሩ !!

ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ወጣቶችን " ለብሩህ ተስፋ፣ ለጥሩ ህይወት ጠቀም ያለ ገንዘብ የሚያስገኝ ስራ በታይላንድ አለ " በማለት ወጣቶቻችንን ለከፋ የስቃይ ህይወት የሚዳርጉ ሰዎች አሉ።

አንዳንዶቹ ጭራሽ ወደ አሜሪካ ፣ ካንዳ እና አውሮፓ ሀገራት ነው የምንልካችሁ በማለት የሚያጭበረብሩ ናቸው።

በእነዚህ ደላሎች እና ኤጀንሲዎችም ጭምር ተታለው ታይላንድ ተብለው የሚሄዱ ሰዎች እጅግ አስከፊ ስቃይ እና ዓለም አቀፍ የማጭበርበር ወንጀል ወደ ሚሰራበት በታይላንድ አቅራቢ ወዳለችው ማይናማር (ድንበር ላይ) ወዳለ ካምፕ ያስገቧቸዋል።

ይህ ሁሉ የሚሆነው በኃይል ነው።

ታይላንድ የደረሱ ወጣቶች ገና ኤርፖርት ላይ ሲደርሱ ተቀባይ አላቸው።

" እፎይ አሁን ህይወታችን ሊቀየር ነው ወደ ሆቴል / ወደምንሰራበት ስፍራ ሊወስዱን ነው " ብለው ሲጠብቁ ከከተማ ውጭ በተቃራኒ መንገድ በመኪና ረጅም ጉዞ ያስጉዟቸውና ወደ አደገኛው የማፍያዎች ስፍራ ያስገቧቸዋል።

እነዚህ ቦታዎች የደህንነት ካሜራ ገና ከበር ጀምሮ ያላቸው፣ መሳሪያ በታጠቁ ሰዎችም የሚጠበቁ ሲሆኑ ማፍያዎቹ ወጣቶቹን በማስገባት ህገወጥ ስራ እንዲሰሩ ያስገድዷቸዋል።

ይኸው ህገወጥ ስራ ዓለም አቀፍ የሆነ የኦንላይን የማጭበርበር ስራ ነው።

ወጣቶቹ በይቆታቸው ፦
- አሰቃቂ ድብደባ ይደርስባቸዋል፣
- ምግብ ይከለከላሉ፣
- ሴቶች ይደፈራሉ፣
- ማሰቃየት (በኤሌክትሪክ ሾክ) ይፈጸምባቸዋል፣
- በሰንሰለት ይታሰራሉ፣
- በኤሌክትሪክ ሽቦ ይገረፋሉ።

እስከ ግድያም ሊደርስ ይችላል።

ህይወታችን ይቀየራል ብለው ከፍተኛ ዋጋ ከፍለው የሄዱ ወጣቶች ለወራት አንድም ብር ሳያገኙ ጭራሽ ህይወታቸው በስቃይ ይሞላል።

እድለኞች ከብዙ ስቃይ በኋላ ይወጣሉ።

አሁንም የውጭ ሀገር ፕሮሰስ እያደረጋችሁ ያላችሁ የሀገራችን ልጆች የት ? ለምን ? ስራ እንደምትሄዱ ጠይቁ መርምሩ።

አሁን ላይ በማይናማር እና ታይላንድ ድንበር በሚገኝ ስፍራ እንደ ባርነት የተያዙ የበርካታ ሀገራት ወጣቶች አሉ።

ኢትዮጵያውያን ወጣቶች የሚመለከተው አካል ይህን ጉዳይ ተከታትሎ እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።

ታይላንድም ይሁን አሜሪካ ፣ ካናዳም ይሁን አውሮፓ ደህንነቱ የተጠበቀ ህጋዊ ስራ ካልሆነ ባትሄዱ ይመከራል።

የሚልኳችሁን ሰዎች በትክክል የት ነው የምንሄደው ? የምናርፈው የት ነው ? የድርጅቱ ስም ምንድነው ? የመስሪያ ፍቃዱ የታለ ? አድራሻው የታለ ? ከዚህ በፊትም የሄዱ ልጆችን አገናኙን ብላችሁ ጠይቁ።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" እንደ ባሪያ ነው የምንታየው ፤ እባካችሁ ጭሁልን !! " - በማይናማር የሚገኙ ወጣቶች ማይናማር እና ታይላንድ ድንበር ላይ ከሚገኙ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የበየነ መረብ ማጭበርበር (Online Scam) ተግባራት ከሚፈጸምባቸው አንዳንድ ቦታዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክቶችን በቴሌግራም እየተቀበለ ይገኛል። እነዚህ ቦታዎች ላይ በርካታ የሀገራችን ወጣቶች ያሉ ሲሆን " ታይላንድ እንልካችኋለን " በሚል…
🔈 #ተጠንቀቁ

ወደ ተለያዩ ውጭ ሀገራት " ስራ ነው " በሚል ፕሮሰስ እያደረጋችሁ ያላችሁ ወጣቶቻችን የትም ሀገር ይሁን የምትሄዱት ስራው ምን እንደሆነ እና ለደህንነታችሁም አስተማማኝ መሆኑን አረጋግጡ።

" ለስራ ውጭ እንላካችሁ " የሚሉትን ደላሎችንም ሆነ ኤጀንሲዎች ፦
- ስራው ምንድነው ?
- በትክክል ድርጅቱ ያለበት ሀገር የት ነው ?
- የድርጅቱን ህጋዊነት የሚያሳይ ማስረጃ አሳዩን !
- ባለበት ሀገር ሕጋዊ ስርዓት የተመዘገበበትን ፋይል አሳዩን ! ብላችሁ ጠይቋቸው።

ከዚህ ውጭ በተድበሰበሰ ሁኔታ " ጠቀም ያለ ገንዘብ ነው የምታገኙት " በሚል ብቻ መረጃ ፤ ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ የሚደረግ የውጭ ሂደት ብታቋርጡ መልካም ነው።

አንዳንድ ስለ ገንዘብ እንጂ ፍጹም ስለ ሰው ህይወት የማያሳስባቸው ደላሎች እና ኤጀንሲዎች በርካታ ወጣቶችን እያታለሉ መጀመሪያ ወዳሉት ሳይሆን ወደ ሌላ ምንም ደህንነቱ ወዳልተረጋገጠ ሀገር እየላኩ ሰዎችን በማጭበርበር ላይ ወደ ተሰማሩ ድርጅቶች እያስገቧቸው ነው።

በነዚህ ድርጅቶች ውስጥ በሚቆዩበት ወቅት በርካታ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች ይፈጸምባቸዋል።

የወጣትነት ጊዜያችሁ ሳያልፍ ህይወታችሁን ለማሻሻል ብላችሁ እጅግ ተቸግራችሁ ፤ ቤተሰብም አስቸግራችሁ ብዙ ብር ከፍላችሁ ወደ ውጭ ሀገር የምትሄዱ ልጆች ስለምትሄዱበት ሀገር እና ስራ በደንብ አጣሩ አንብቡ።

ዘመኑ  የቴክኖሎጂ  ነውና በስልካችሁ ላይ ገብታችሁ የምትሄዱበት ሀገር ስላለው ደህነት፣  ስላለው የስራ ሁኔታ ፣ እናተም ትስሩታላችሁ ስለሚባለው ስራ በደንብ አረጋግጡ።

በኦንላይን የማያታውቁት ሰው ወይም በማስታወቂያ " ለስራ ወጣቶችን እንፈልጋለን " ሲሉ አትመልሱላቸው።

⚠️ በቀጣይ " ጠቀም ያለ ገቢ የሚያስገኝ ስራ ነው ! " እየተባለ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት በብዛት ወጣቶችን በማዘዋወር አንዳንድ ድርጅቶች እያስገቡ ወጣቶችን የሚያሰሯቸውን የኦንላይን ማጭበርበር  / Online Scam / ድርጊት አይነቶችን በዝርዝር እንዳስሳለን።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈 #የነዋሪዎችድምፅ “ ግድያና እገታ የሚፈጸመው መሀል ከተማ ላይ ነው፡፡ ለዛውም ፖሊስ ጣቢያ ባለበት አጠገብ፡፡ ዛሬ ህዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥቷል፡፡ ፖሊስና ሚሊሻ ወደ ህዝቡ ነው የተኮሰው ” - ነዋሪዎች በአማራ ክልል፣ ጎንደር ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች በተለይ ከሦስት ወራት ወዲህ " በታጠቁ አካላት አማካኝነት ግድያ፣ እገታና ዝርፍያ " በመበራከቱ ሰቆቃ ላይ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡…
🔈 #የዜጎችድምጽ

በኢትዮጵያ ውስጥ ከቅርብ አመታት ወዲህ እጅግ እየተስፋፋና እየተባባሰ የመጣው የእገታ ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።

ሰዎች ይታገታሉ ፤ ገንዘብ ይጠየቃል ፤ አንዳንዴማ ጭራሽ የገንዘብ ዝውውር በባንክ ይፈጸማል።

አጋቾች ዘገያችሁ በማለትም ታጋቾችን ይገድላሉ።

ህጻን፣ አዛውንት፣ ወጣት፣ ሴት ፣ ሀብታም ፣ ገንዘብ የሌለው የሚቀር የለም ይታገታል።

ድርጊቱ በተለይ አማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ላይ በስፋት የሚስተዋል ሲሆን ትግራይ ውስጥ ጦርነቱ ከቆመ ወዲህ እገታ ሲፈጸምና ሰው ሲገደልም ተሰምቷል።

አማራ ክልል ከዚህ ቀደምም እገታ ይፈጸም የነበረ ሲሆን ህዝቡ " የመፍትሄ ያለህ !! "እያለ ሲጮህ ነው የኖረው ባለፉት ዓመታ ግን በክልሉ ካለው የጸጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ እገታ እጅግ ተባብሷል።

ሰው ይታገታል ፤ ድሃው ቤተሰብ ብር አምጣ ይባላል ብር መላክ ሳይችል ሲቀር ታጋች ተገድሎ ይጣላል ፤ አዘገያችሁ እየተባለም መግደል ተጀምሯል።

አሽከርካሪዎች ተዘዋውረው ስራ መስራት ፈተና ሆኖባቸዋል። ወጥቶ መግባት ብርቅ ሆኗል። በዚህ የተማረረው ዜጋ አካባቢውን ጥሎ ለመውጣት እየተገደደ ነው። ያውም ያለው። የሌለው አማራጭ ስላጣ እዛው በሰቀቀን ይኖራል።

አሁን አሁን ግን እገታ ብቻ ሳይሆን ሰዎችን ማሸበር የተያያዘ ስራ ይመስላል። ብር ተሰጥቶ እንኳን ታጋች ተገድሎ ይጣላል። ህዝቡንና ህብረተሰቡን ተስፋ የማስቆረጥ ፤ በስነልቦና የመጉዳት ነገር !

ኦሮሚያም በተመሳሳይ ዓመታት አልፈዋል።

እጅግ በሚያስገርምና ጥያቄንም በሚፈጥር ሁኔታ አንድ ቦታ ላይ ብዙ ጊዜ ተደጋግሞ እገታ ይፈጸማል።

ተማሪ ፣ ሰላማዊ መንገደኛ ሳይቀር ታፍኖ ተወስዶ ቤተሰብ ብር ይጠየቃል። ሰው ይገደላል።

አንዳንድ ቦታዎች ጭራሽ መንገድ ሄዶ መመልስ ብርቅ ነው። ሰው አቅም የለው በአየር ትራንስፖርት እንዳይጠቀም ህይወቱን አስይዞ ለኑሮው ለስራው ሲል ይጓዛል።

ለመሆኑ አንድ ቦታ ላይ ተደጋግሞ እገታ ሲፈጸም ዘላቂ እርምጃ የማይወስደው ለምንድነው ? ፣ ሌላው ይቅር ችግሩን መፍታት ከተፈለገ የደህንነት ካሜራዎችን እንኳን እየተጠቀሙ ፣ የስልክ መስመሮችን እያጠኑ መፍትሄ መስጠት ለምን አልተቻለም ? ይህ የብዙዎች ጥያቄ ነው።

አንድ መስመር ላይ ዓመታት ሙሉ ሰው እየታገተ ገንዘብ ሲጠየቅ ችግሩን በዘላቂነት እንዲፈታ አለማድረግ ትልቅ ጥያቄ ነው የሚያስነሳው።

ትግራይ ላይ ከጦርነት ማግስት ሰዎችን አግቶ ብዙ ሚሊዮን ብር መጠየቅ የተለመደ ሆኗል። በዚህ ዓመት በርካቶች ታግተው ገንዘብ ተጠይቆባቸዋል።

ከእገታ በኃላ የተገደለም አለ።

በእርግጥ የሰላም መጥፋት ለእንዲህ ያለው ስርዓት አልበኝነት በር እንደሚከፍት የታወቀ ቢሆንም ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ ሁሉንም አቅም አሟጦ በመጠቀም ለምን አልተሰራም ?

ብዙዎች በእገታና ግድያ ተግባራት መሯቸዋል።

ከዓመታት በፊት በዚህ በሰፋ ልክ ያልተለመደ አሁን ግን ልክ ፋሽን እየሆነ የመጣን ተግባር ከምንጩ ለምን ማድረቅ እንዳልተቻለ የብዙዎች ጥያቄ ነው።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM