TIKVAH-ETHIOPIA
1.44M subscribers
55.9K photos
1.4K videos
202 files
3.77K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Free_Nazrawit_Abera!!

መንግስት በቻይና መንግስት እፅ በማዘዋወር ተጠርጥራ እስር ላይ የምትገኘውን ናዝራዊት አበራን ጉዳይ በቅርበት እየተከታተለው መሆኑን ገለጸ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነቢያት ጌታቸው ከfbc ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ መንግስት #ጓንዡ_ግዛት በሚገኘው ማረሚያ ቤት የምትገኘውን የናዝራዊት አበራን ጉዳይ #በቅርበት እየተከታተለው መሆኑን ተናግረዋል።

በስፍራው በሚገኘው የኢፌዴሪ ቆንስላ ፅህፈት ቤት ሰራተኞችም ናዝራዊት በምትገኝበት ማረሚያ ቤት ሶስት ጊዜ በመሄድ ያለችበትን ሁኔታ ተመልክተዋል ነው ያሉት።

መንግስትም ዜጋውን የመከታተል መብቱን ተጠቅሞ ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተለው መሆኑን ጠቅሰው፥ ተጠርጣሪዋን በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ እየተናፈሱ ያሉ ወሬዎች #ሃሰት መሆናቸውንም ነው የተናገሩት።

በተለይም ከተጠረጠረችበት ጉዳይ ጋር በተያያዘ #የሞት_ፍርድ_ተፈርዶባታል በሚል እየተናፈሰ ያለው ወሬ ሃሰት መሆኑንም ገልጸዋል።

ተጠርጣሪዋ አሁን ላይ በማረሚያ ቤት የምትገኝ ሲሆን አቃቤ ህግም ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ክሱን ካቀረበ በኋላ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት አምርቶ #እንደሚወሰንም አስረድተዋል።

መንግስት አሁን ላይ እንደ ዜጋ መጠየቅ የሚችለውን እያደረገ ሲሆን፥ ትክክለኛ ፍርድ እንድታገኝ ክትትል ይደረጋልም ነው ያሉት።

ምንጭ፦ ፋና
@tsegabwolde @tijvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️

ዋልታ ፖሊስ ትግራይ የእግር ኳስ ክለብ ዛሬ ጠዋት ባልታወቁ #ታጣቂዎች ጥቃት እንደደረሰበት ለማወቅ ተችሏል። በአንደኛ ሊግ ተሳታፊ የሆነው ዋልታ ፖሊስ ትግራይ ከሰሜን ሸዋ ደብረብርሃን ጋር ጨዋታ አድርጎ ወደ #መቐለ ሲመለስ በጉዞ ላይ እያለ ነበር በአፋር ክልል #ገዋኔ አካባቢ ባልታወቁ ታጣቂዎች ጥቃት የደረሰባቸው። እስካሁን ባለሁ ሁኔታም በአንድ የቡድኑ አባል ላይ #የሞት አደጋ መድረሱ ሲረጋገጥ በስምንት የቡድኑ አባላት ላይም ከበድ ያለ ጉዳት መድረሱን የቡድኑ መሪ ለትግራይ ቴሌቪዥን ገልፀዋል። በኮንስታብል ዮሃንስ ሲሳይ የሚመራው ዋልታ ፖሊስ በ1960ዎቹ የተመሰረተ አንጋፋ ክለብ ሲሆን በጥቃቱ ዙርያ እስካሁን የተሰጠው ይፋዊ መግለጫ የለም።

Via ሶከር ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert

በአዲስ አበባ ቦሌ ድልድይ ስካይ ላይት ሆቴል አካባቢ የመብራት ፖል ወድቆ በአንድ ሰዉ ላይ የሞተ አደጋ ደርሰ። በቦሌ ክፍለ ከተማ ስካይ ላይት ሆቴል ፊት ለፊት ረፋድ 5 ሰዓት አካባቢ መብራት ፖል ተሰብሮ በስራ ላይ በነበረ የመብራት ሀይል ሰራተኛ ላይ #የሞት አደጋ አጋጥሟል፡፡

በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ባለሙያዉ ሳጅን ምትኩ መንገሻ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቁት፤ በአካባቢዉ የሚገኝ አንድ የመብራት ፖል ለመንቀል በክሬን መኪና እየተሰራ ባለበት ወቅት ፤ፖሉ ከክሬኑ አምልጦ በሰራተኛዉ ላይ ጉዳት አድርሷል ብለዋል፡፡

የመብራት ፖሉ በሰዉ ሃይል አልነቀል በማለቱ በመኪና ክሬን ፖሉን ለማንሳት በሚደረግበት ወቅት ፖሉ በሰረተኛዉ ላይ ማረፉንም ሳጅን ምትኩ ተናግረዋል፡፡

ግለሰቡ ወዲያዉኑ ህይዎቱ ያለፈ ሲሆን የግለሰቡን ማንነት ለመለየት ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ እያደረገ ነዉ ብለዋል፡፡ የመኪናዉ አሽከርካሪም በቁጥጥር ስር መዋሉን ሳጅን ምትኩ አረጋግጠዋል፡፡

Via #ኢትዮ_ኤፍኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ናዝራዊት_አበራ

እፅ በማዘዋወር #ተጠርጥራ ቻይና ጉዋንዡ እስር ቤት የምትገኘው #ኢትዮጵያዊቷ ናዝራዊት አበራ ከወር በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት መቅረቧንና የመጨረሻውን ፍርድ እየተጠባበቁ እንደሆነ እህቷ #ቤተልሔም_አበራ ለቢቢሲ ገለፁ።

ናዝራዊት አበራ በቻይና በእፅ ዝውውር ተጠርጥራ በቁጥጥር ሥር መዋሏ ከተሰማ ስድስት ወራቶች አልፈዋል።

አንድ ሰው እፅ ሲያዘዋውር ከተገኘ #የሞት ፍርድ እንዲበየንበት የሚያዘው የቻይና ህግ በናዝራዊት ላይ ተግባራዊ ይሆናል በሚል በቤተሰቦቿ፣ በቅርብ ዘመዶቿ እንዲሁም በበርካታ ሰዎች ዘንድ ስጋትን አሳድሯል።

የቢቢሲን ዘገባ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/NA-07-22
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሳዑዲ_አረቢያ የሳዑዲ አረቢያ መንግስት በሪያድ የቀስተደመና ቀለም ያላቸውን እቃዎች ከሱቆች እና ከመደብሮች እየሰብሰበ ይገኛል። የሳዑዲ መንግስት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ያስተዋውቃል በሚል የቀስተደመና ቀለም ያላቸውን አሸንጉሊቶች፣ ቲሸርቶች፣ የጸጉር ማስያዣዎች፣ ኮፊያ፣ እና የእርሳስ መያዣወችን ከየመደብሩ እንዲሰበሰቡ እያደረገ ነው። የሀገሪቱ መንግስት ህፃናትን ለመጠበቅ ሲል " መርዛማ መልዕክት…
" እኛ የሙስሊም ሀገር ነን። ባህሎች እና ወጎች አሉን እናም እስልምና እነዚህን ድርጊቶች (የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን) ይከለክላል " - አል ሃማሚ

ኢራቅ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል እንዲሆንና ከፍተኛ የሆነ ቅጣት እንዲጣል እየሰራች መሆኗን አሳውቃለች።

የኢራቅ መንግስት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት የሚከለክል ህግ ለማፅደቅ ማቀዱን አስታውቋል።

ኢራቅ በመካከለኛው ምስራቅ ከሚገኙ ሶስት ብዙ አረቦች ከሚኖሩበት ሀገር መካከል አንዷና የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን #በግልፅ ወንጀል እንደሆነ ካላወጁ ሀገራት የምትጠቀስ ናት፤ ሌሎቹ ጆርዳን እና ባህሬን ናቸው።

ምንም እንኳን በግልፅ ወንጀል ነው ተብሎ ባይገለፅም ድርጊቱ በማህበረሰቡ ዘንድ እጅግ በጣም የተወገዘ ነው።

አሁን ያለው ሁኔታ ያላማራት ኢራቅ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል እንደሆነ በህግ ለመደንገግ እየሰራች ሲሆን ህጉ ከወጣ ኢራቅ ሌሎች ድርጊቱን በህግ ወንጀል እንደሆነ ካፀደቁ ሀገራት ተርታ ትሆናለች።

አብዛኛዎቹ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን በቀጥታ በግልፅ የሚከለክሉ እና ወንጀል ነው ያሉ ሲሆን ከገንዘብ ቅጣት እስከ እስራት ፤ ሳውዲ አረቢያ ደግሞ #የሞት_ቅጣት ትቀጣለች።

በኢራቅ ፓርላማ የህግ ኮሚቴ ውስጥ ያሉት የፓርላማ አባል አሬፍ አል ሃማሚ ለDW በሰጡት ቃላቸው ፥ " አዲሱ ህግ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ያላቸውን በወንጀል ተጠያቂ ያደርጋል ፤ በእነሱ ላይም ከባድ ቅጣት ይጥላል " ብለዋል።

ህጉ እስካሁን ድምጽ ያልተሰጠበት ሲሆን ድምፅ እንዲሰጥበት እየተሰራ ነው።

አል ሃማሚ ፤ ከሀገር ውስጥ እና ከዓለም አቀፍ #የሰብአዊ_መብት_ተሟጋች_ድርጅቶች ትችት ቢሰነዘርም ህጉ ይፀድቃል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።

ያንብቡ telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-07-19

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
አፅድቀውታል ፤ ፈርመውበታል !

ዩጋንዳ የ " ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት " ን ወንጀል የሚያደርገውን ሕግ አፀደቀች።

ዛሬ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ያፀደቁት / ፊርማቸውን ያኖሩበት የረቂቅ አዋጅ ሕግ ተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት የሚፈጽሙ ሰዎችን ሁሉ በዕድሜ ልክ እስራት የሚያስቀጣ ነው።

በአንዳንድ ሁኔታዎች ዳግሞ #የሞት ቅጣትን የሚያስከትል ነዉ።

ረቂቅ ሕጉ ባለፈው መጋቢት ወር ላይ በአገሪቱ ምክር ቤት አባላት ተቀባይንት ያገኘ ሲሆን፣ ማሻሻያ እንዲደረግበት ለፓርላማው ተመልሶ ቀርቦ ነበር።

ቀደም ሲል ቀርቦ በነበረው ረቂቅ ሕግ ላይ ማንኛውም ራሱን በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አፍቃሪነት የመደበ፣ ወይም የጾታ ለውጥ ያስደረገ እንዲሁም ከዚሁ ጋር በተያያዘው ዝርዝር ውስጥ የሚካተት የጾታ ዝንባሌ ያለው ዜጋን ሁሉ ወንጀለኛ የሚያደርግ ነበር።

ሆኖም ግን ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ይህ ሰዎች እንዲታሰሩ እና በአካላዊ ገጽታቸው ብቻ እንዲከሰሱ ያደርጋል ሲሉ ሳይቀበሉት ቀርተዋል።

ፕሬዝዳንቱ ረቂቅ ሕጉ እንዲሻሻል ወደ ፓርላማ መልሰውት ነበር።

በዚህ መሠረት ተሻሽሎ አሁን ላይ የቀረበው ረቂቅ ሕግ፣ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ወንጀልነት ወንድ ከወንድ ጋር በሚያደርገው ወሲባዊ ድርጊቶች ላይ የተወሰነ ሆኗል።

ይህንን ሕግ ተላልፈው የተገኙም እስከ እድሜ ልክ እስራት ይጠብቃቸዋል።

ለከባድ ወንጀሎች ማለትም ወሲባዊ ጥቃቱ #በሕጻናት_ላይ ፣ በአካል ጉዳተኛ እንዲሁም ተጋላጭ በሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ላይ በሚፈፀምበት ጊዜ አሊያም የጥቃት ሰለባዎቹ ለዕድሜ ልክ ህመም የሚዳረጉ ከሆነ በድርጊቱ ፈፃሚ ላይ #የሞት ቅጣትን ይደነግጋል።

ማኅበረሰቡ #በሕጻናት ወይም በሌሎች ተጋላጭ በሆኑ የሕብረተሰቡ አባላት ላይ ማንኛውንም ዓይነት የተመሳሳይ ጾታ ጥቃት በሚያዩ አልያም በሚሰሙበት ጊዜ ለባለሥልጣናት ማሳወቅ እንደሚጠበቅባቸው ቢቢሲ ዘግቧል።

በምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ኡጋንዳ የተመሳሳይ ጾታ ቀድሞም ሕገ ወጥ ተደርጎ ነው የቆየው ፤ ይህ ሕግ ከሕገ ወጥነቱ አልፎ ነገሩን ወንጀልና በተራዘመ እስር የሚያስቀጣ ያደርገዋል።

#ምዕራባውያን ሀገራትና #ተቋማት በተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ጉዳይ በዩጋንዳ ፓርላማ የተላለፈውን ውሳኔ ሲቃወሙና ፕሬዜዳንቱ #እንዳይፈርሙ ሲያሳስቡ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃለማርያም ሀገር ጥለው ከወጡ ዛሬ ድፍን 33 ዓመት ሆኗቸዋል።

የቀድሞ የኢትዮጵያ መሪ ግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ/ም ነው ከሀገር የወጡት።

የድርግ ውድቀትን እና የ #ኢህአዴግ ወደ አዲስ አበባ መቃረብን ተከትሎ ከሀገር እንደወጡ የሚነገርላቸው ኮ/ሌ መንግሥቱ ኃለማርያም በአንድ ወቅት ፤ " እኔ ኮብልዬ አልወጣሁም " ሲሉ ነበር ቃላቸውን የሰጡት።

ኬንያ የሄዱትም ' #አሰብ ' በሻዕብያ በመያዙ ለመልሶ ማጥቃት የሚሆን ሌላ በር እንዲኖር ከኬንያ፣ ከጅቡቲ እና ሰሜን ሶማሊያ መንግስታት ጋር ለመነጋገርና ለመመለስ እንደነበረና ይህም ጥብቅ ሚስጥራዊ ጉዞ እንደሆነ ተናግረው ነበር።

ጥዋት 2:20 ወደ ኬንያ ጉዞ እንደጀመሩ እዚህ ስብሰባ መጀመሩና ኬንያ እንዳሉ ከቀን 7:00 ሰዓት ከስልጣን እንደወረዱ እንደሰሙ ገልጸው ነበር።

በራሳቸው አንደበትም ፥ ምንም አይነት #ገፊ ምክንያት በሌለበት በአሻጥር ከሀገር እንዲወጡ መገደዱን ነው በአንድ ወቅት ሲናገሩ የተደመጡት።

ዛሬ ላይ ሀገር ጥለው ከወጡ 33 ዓመት የደፈናቸው ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም በዚምባቡዬ ውስጥ ይኖራሉ።

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዜዳት ከዓመታት በፊት ፦
° በዘር ማጥፋት ፣
° በግድያ፣
° ከህግ ውጪ ሰዎችን በማሰር
° ንብረትን በመውረስ ጥፋተኛ ተብለው በሌሉበት #የሞት ፍርድ ተወስኖባቸዋል።

@tikvahethiopia
#Adama

ተከሳሽ ቶሎሳ ወይም ፍቅሩ አሸናፊ ይባላል።

በአዳማ ከተማ ቦሌ ክፍል ከተማ በተለምዶ ደካ አዲ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሚያዝያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም እናቱን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሏል።

ተከሳሹ እናቱን በስለት (ቢላዋ) በአሰቃቂ ሁኔታ ወግቶ ነው ህይወታቸውን እንዲያጡ ያደረገው።

ተከሳሹ ድርጊቱን የፈጸመው #በቁማር_የተበላዉን ገንዘብ እናቱ ያላቸውን ንብረት በመሸጥ እንዲተኩለት ለማድረግ ሲል እየደበደበ ያሰቃያቸው እንደነበር ዐቃቤ ሕግ በማስረጃ አረጋግጧል።

በዚህ ብቻ ያላበቃው ተከሳሽ ሚያዚያ 21/ 2016 ዓ/ም ጠዋት በአሰቃቂ ሁኔታ የእናቱ ህይወት እንዲያልፍ በማድረጉ ከባድ የግድያ ወንጀል ክስ ቀርቦበታል።

ጉዳዩን የተመለከተው የአዳማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት በሞት እንዲቀጣ ወስኗል።

በተከሳሹ ላይ የተጣለው #የሞት_ፍርድ በአገሪቱ ርዕሰ ብሔር ሲጸድቅ ነው ተፈጻሚ የሚሆነው። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#ሞት_ተፈርዶበታል !

ከአባቱ ጋር በገባበት " #የጥቅም_ግጭት " መላው ቤተሰቦቹን በጥይት ገድሎ ሊጨርስ የነበረው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተፈረደበት።

ተከሳሽ ከፍታ ካፋላ ይባላል።

በጋርዱላ ዞን የሃይበና ቀበሌ ነዋሪ ነው።

ግለሰቡ ቤተሰቦቹ በሚኖሩበት በኮንሶ ዞን ሠገን ዙሪያ ወረዳ ሠገን ገነት ቀበሌ በመሄድ በ4 ቤተሰቦቹ ላይ የጥይት እሩምታ ይከፍታል።

በዚህም ሶስቱን ሲገድል አንዱን አቁስሏል።

በጥይት እሩምታ የገደላቸው ፦
- #አባቱ
- #እናቱ
- #አጎቱ ሲሆኑ የመቁሰል አደጋ የደረሰበት የ9 አመት ታናሽ ወንድሙ ነው።

ግለሰቡ ይህን ፈጽሞ ከአካባቢዉ ቢሰወርም የጸጥታ ኃይሉ ከማህበረሰቡ ጋር ተባብሮ ባደረገዉ ክትትል ከ5 ወራት በኋላ ሊያዝ ችሏል።

ፖሊስም ስራውን አጠናቆ ለፍርድ ቤት አቅርቧል።

ተከሳሹም ፤ ከወላጅ #አባቱ ጋር በገባበት ' የጥቅም ግጭት ' ምክኒያት ወንጀሉን እንደፈጸመ ለፍርድ ቤቱ አምኖ ቃሉን ሰጥቷል።

ይህም ቃሉም ከቀረበበት የሰውና የሰነድ ማስረጃ ጋር ተዳምሮ የፍርድ ሂደቱን ቀላል እንዳደረገዉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።

በዚህም በኃላ ጉዳዩን ሲመረምር የነበረዉ የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ተከሳሽ ከፍታ ካፋላ #በሞት እንዲቀጣ ወስኗል።

በተከሳሹ ላይ የተጣለው #የሞት_ፍርድ በአገሪቱ ርዕሰ ብሔር ሲጸድቅ ነው ተፈጻሚ የሚሆነው።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia