TIKVAH-ETHIOPIA
1.44M subscribers
55.9K photos
1.4K videos
202 files
3.77K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Hawassa

" . . . ማንም አካል በመንግስት ንብረት የግል ፍላጎቱን ማራመድ አይችልም ፤ እንዲህ አይነት ፍላጎት ያለዉ አካል ስልጣኑን ለቆ ፍላጎቱን ማሳካት ይችላል " - የሲዳማ ክልል የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ

" ጉዳዩ በውስጣዊ አሰራር ህግና ደንብ መሰረት ተይዞ በሂደት ላይ ነው። " - የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ

" ... ለጊዜዉ በሌለሁበት ከስራ እንድታገድ ወስነዉብኛል። ነገር ሁሉ ለበጎ ነው ብዬ እየጠበኩ ነው። " - ኢኒስፔክተር ተስፋዬ

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ መነጋገሪያ ሆነው የሰነበቱት የሀዋሳ ከተማ ትራፊክ ፖሊስ ማስተባበሪያ ኃላፊዉ ኢንስፔክተር ተሰፋዬ ደምሴ ላልተወሰነ ጊዜ ከስራ ታግደዋል።

ይህ በተመለከት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ኢንስፔክተር ተስፋዬን እና ጉዳዩ ይመለከታቸው ያላቸውን አካላት ለማነጋገር ጥረት አድግጓል።

ከሰሞኑ የሲዳማ ክልል የጸጥታ አካላት ያደረጉትን ስብሰባ ተከትሎ በተለቀቀዉ አንድ ተንቀሳቃሽ ምስል ፤ ኢንስፔክተር ተስፋዬ ነጻና ገለልተኛ ሁኖ ማህበረሰቡን የሚያገለግለዉን የፖሊስ ንብረት በግላቸዉ ለሚከተሉት ሀይማኖታዊ አገልግሎት በማዋላቸዉ ምክኒያት ላልተወሰነ ጊዜ ከስራ መታገዳቸዉ ይገልጻል።

በወቅቱ ስብሰባዉን የመሩት የክልሉ የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ኃላፊዉ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ ባስተላለፉት መልእክት ፤ ማንም አካል በመንግስት ንብረት የግል ፍላጎቱን ማራመድ እንደማይችልና እንዲህ አይነት ፍላጎት ያለዉ አካል ስልጣኑን ለቆ ፍላጎቱን ማሳካት እንደሚችል ገልጸዋል።

በጉዳዩ ላይ ከቲክቫህ ኢትዮጰያ ተጨማሪ ማብራሪያ የተጠየቀዉ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ በበኩሉ ጉዳዩ በዉስጣዊ አሰራር ህግና ደንባቸዉ መሰረት ተይዞ በሂደት ላይ ያለ መሆኑን አሳውቋል።

ይሁንና ከሰሞኑ በነበረዉ ስብሰባ ወቅት የተነሳዉን የኢንስፔክተር ተስፋዬን ከስራ መታገድ በተመለከተ ለጊዜዉ ዝርዝር ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥቧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ኢንስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ ስለሁኔታው ምን ምላሽ እንዳላቸው በስልክ ጠይቋቸው " ኢየሱስ ይመጣል የሚለዉን መልእክት ባስተላለፍኩበት ወቅት እንዳያችሁት በተፈጠረዉ ሁኔታ ከስራ ታግጃለሁ ፤ ለጊዜዉ በሌለሁበት ከስራ እንድታገድ ወስነዉብኛል። " ብለዋል።

" ነገር ሁሉ ለበጎ ነዉ ብዬ እየጠበኩ ነው እግዚያብሄር መልካም ነዉ " ሲሉ አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Hawassa

በፀጋ በላቸው ላይ የጠለፋና አስገድዶ መድፈር ወንጀል የተከሰሰው ኮንስታብል የኋላመብራት ወልደማርያም በ16 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል።

የህግ አማካሪና ጠበቃ እንዲሁም በፆታዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰሩት አበባየሁ ጌታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ ውሳኔው የከተማውን ገፅታ የሚያበላሽ እንደሆነ ስለታሰበ ነው መፍትሄ ያገኘው ብለዋል።

አበባየሁ ጌታ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ምን አሉ ?

-  ሚዲያ ላይ ባለመውጣታቸው ብዙ ተሸፋፍነው የቀሩ የጠለፋ ወንጀሎች በከተማው አሉ።

-  ይህ ውጤት የተገኘው በተለያዩ መንገዶች በማህበራዊ ሚዲያው ላይ ከፍተኛ ትኩረት ስላገኘ ነው።

-  ጉዳዩ አነጋጋሪ የሆነው የከንቲባው የግል ጠባቂ ከመሆኑ፣ የመንግስትን ንብረት ተጠቅሞ በመሆኑ በከተማው ገፅታ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ስለነበረው ነው ይህ ጉዳይ እልባት ያገኘው።

-  ታህሳስ 04 ቀን 2016 ዓ.ም. በዋለው ችሎት ተጠርጣሪው በተከሰሰባቸው ሁለት ወንጀሎች ማለትም በጠለፋ እና አስገድዶ መድፈር ጥፋተኛ ተብሏል።

- በመቀጠል ታህሳስ 08 ቀን 2016 ዓ.ም. በዋለው ችሎት ላይ ከሁለቱም ወገኖች የቅጣት ማቅለያ እና ማክበጃ እንዲያቀርቡ ተደርጎ ነበር።

-  በዛሬው እለት ከተያዘበት ቀን ጀምሮ በ16 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ፍርድ ተሰጥቷል።

ባለሙያው በአጠቃላይ ፆታዊ ጥቃቶችን በተመለከተ ምን አሉ ?

* ወደሐዋሳ አካባቢ መሰል ችግሮችን በሽምግልና መፍታት እና ከባህል ጋር የማያያዝ አዝማሚያ አስቸጋሪ ነው። እንደዚህ አይነት ነገሮች በሽምግልና መፈታት የለባቸውም።

* የህግ አካላት በማህበራዊ ሚዲያ የማይጮኹ ጉዳዮችንም ትኩረት አለመስጠት እና ተባባሪ አለመሆንም መስተካከል ይገባዋል።

* በትምህርት፣ በስልጠና እና በመሰል አስተማሪ ቅጣቶች ለፆታዊ ጥቃቶች ትኩረት መስጠት ይገባል።

የዳሸን ባንክ ሰራተኛ እንዲሁም የአላሙራ ሙሉወንጌል ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆነችው ፀጋ በላቸው ፤ ግንቦት 15 ቀን 2015 ከስራ ስትወጣ በወቅቱ የከተማው ከንቲባ የግል ጠባቂ በነበረው ኮንስታብል የኃላመብራት ወ/ማርያም የተባለ ግለሰብ በመኪና ታግታ መወሰዷና አድራሻዋም ሳይታወቅ ለቀናት መቆየቱ የሚታወስ ነው።

የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በወቅቱ እንዳስታወቀው ተጠርጣሪው ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን ከፀጥታ ሀይል ለማምለጥ ሲል በሻፋሞ ጫካ ለጫካ ሲዘዋወር እንደነበረ እና ተጠርጣሪው ግለሰብ ወንጀሉን ለመፈጸም ሲጠቀምባቸው ከነበሩ አንድ ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያና ሽጉጥ ጋር  ህዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም. መያዙን የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታውቆ ነበር።

መረጃው ተዘጋጅቶ የተላከው በአዲስ አበባ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#Hawassa #ጤና

በሀዋሳ ከተማ በሚገኝ " ፓነሲያ ሆስፒታል " 2,094 የሀሞት ከረጢት ጠጠር በቀዶ ህክምና ከአንዲት 40 ዓመት ሴት በሆስፒታሉ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት በዶ/ር ፀጋዬ ቸቦና በስራ ባልደረቦቻቸው የቀዶ ህክምና ቡድን አማካኝነት ወጥቷል።

ጉዳዩን በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡት ዶ/ር ፀጋዬ ፤ ይህ በኢትዮጵያ እንዲሁም በአፍሪካ አህጉር ደረጃ በቁጥር ብዛት የመጀመሪያ የሆነና እስከዛሬ ያልተመዘገበ ከ2,094 በላይ ቁጥር ያለው የሀሞት ከረጢት ጠጠር (Symptomatic Multiple Cholelithiasis) ነው ብለዋል።

ቀዶ ህክምናው 2 ሰዓታት ከ30 ደቂቃ የፈጀ ሲሆን በተሳካ ሁኔታ ማስወገድ መቻሉን አስረድተዋል።

የሀሞት ከረጢት ጠጠሮቹ በቀዶ ህክምና ቡድን የተቆጠሩ ሲሆን ጠጠሮቹን ለመቁጠር ከ45 ደቂቃ በላይ መፍጀቱን ዶ/ር ፀጋዬ ገልጸዋል።

የ40 ዓመት እድሜ ያላት ታካሚዋ ለ3 ዓመታት የቆየ በአብዘኛው ጊዜ ቅባታማ ምግቦችን ከተመገቡ በሗላ የሚከሰት ለረጅም ሰዓታት የሚቆይ ፦
- የሆድ የላይኛው ቀኝ ክፍል የመውጋትና የማቃጠል ህመም ፣
- ምግብ ያለመፈጨት ችግሮች ፣
- የቀኝ ትከሻ እና የጀርባ ህመም ስለነበራቸው ነው ወደ ሆስፒታሉ ያቀናችው።

አስፈላጊው ምርመራ ከተደረገላት በኃላ ነው የሀሞት ከረጢት ጠጠር (Symptomatic Cholelithiasis) እንዳለባቸው በመታወቁ ቀዶ ህክምና እንደሚያስፈልጋት የተነገራት።

የቀዶ ህክምናው ውስብስብነት ላይ ውይይት ከተደረገና በቂ መረጃ ከተሰጣቸው በኋላ ተጨማሪ ስምምነት ፈርመው ነው ቀዶ ህክምናውን ለማደረግ የወሰኑት።

የታካሚዋ ቀዶ ህክምና ከባድና ውስብስብ ያደረገው ምንድነው ?

* በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ሆስፒታሎች ሶስት ጊዜ (3x) የእንቅርት ዕጢ/ካንሰር ቀዶ ህክምና የተደረገላቸው መሆኑ
* ከቀዶ ህክምናው በሗላ በታካሚዋ ላይ የነበረባቸው ተጓዳኝ የጉሮሮ ነርቭ  ጉዳት ፤
* የድምፅ ለውጥ/የድምፅ ኃይል መቀነስ እና አልፎ አልፎ የነበረባቸው የአተነፋፈስ ችግሮች የድህረ- ቀዶ ህክምናው ፅኑ እንክብካቤ እና እርዳታ ውስብስብ አድርጎታል።

ምንም እንኳን ቀዶ ህክምናው ታካሚዋ በነበረባቸው  ተጓዳኝ ችግሮች ውስብስብ ቢሆንም በሆስፒታሉ የቀዶ ህክምና ቡድን ቅንጅት ቀዶ ህክምናው በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል።

🔹በዓለም አቀፍ ደረጃ በሳይንሳዊ መጽሔቶች እና ምርምር ሪፖርቶች ላይ ከፍተኛ ብዛት ያላቸው የሀሞት ከረጢት ጠጠር በህንድ በሪከርድነት ተይዞ ይገኛል።

🔹በአፍሪካ ጆርናሎችና ሳይንሳዊ ወረቀቶች ወስጥ በዚህ ደረጃ ብዛት ያላቸው የሀሞት ከረጢት ጠጠር ተመዝግቦ አልተገኘም። እስካሁን ባሉ መረጃዎች በኢትዮጵያ ሳይንሳዊ ጆርናሎች ላይ 146 የሃሞት ጠጠር ከፍተኛ ቁጥር ሆኖ ተመዝግቦ ይገኛል።

በፓነሲያ ሆስፒታል-ሀዋሳ በቀዶ ህክምና የወጣዉ ከ2,094 በላይ ብዛት ያለው የሀሞት ከረጢት ጠጠር በኢትዮጵያ እንዲሁም በአፍሪካ አህጉር ደረጃ በቁጥር ብዛት በሳይንሳዊ መጽሔቶች እና ምርምር ወረቀት ሪፖርቶች ላይ አዲስ ሪከርድ ሆኖ ሊመዘገብ የሚችል መሆኑን ዶ/ር ፀጋዬ ቸቦ ተናግረዋል።

ለጥንቃቄ . . .

በአብዘኛው ጊዜ ቅባታማ ምግቦችን ከተመገቡ በሗላ የምከሰት ለረጅም ሰዓት የሚቆይ የሆድ ህመም ካላ ፦
☑️ በሆድ የላይኛው ቀኝ ክፍል ድንገተኛ የመውጋትና የማቃጠል ህመም ፣
☑️ በቀኝ ትከሻ ላይና በትከሻ መሳቢያዎች መካከል የጀርባ ህመም፣
☑️ የሆድ መነፋት ስሜት እና ምግብ ያለመፈጨት ችግሮች ካሳየና ካለዎት ፤ ይህ የሀሞት ከረጢት ጠጠር ህመም (Symptomatic Cholelithiasis) ምልክት ሊሆን ስለምችል ባፋጣኝ ወደ ሆስፒታል ማቅናት ያስፈልጋል።

@tikvahethiopia
#Hawassa

" የውሀ እጥረት በመከሰሰቱ  ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠናል " - በሀዋሳ  ከተማ የጋራ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎች

" ከኦሮሚያ ክልል የሚመጣዉ ውሀ በመቋረጡ የድሀ ግብአታችን ላይ ከፍተኛ እጥረት ተከስቶብናል " -  የሀዋሳ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀዋሳ ከተማ በተለይም በጋራ መኖሪያ ቤቶች እንዲሁም በአዲስከተማ ክፍለከተማ ስር ባሉ ቀበሌዎችና አዋሳኝ ክፍለከተሞች ከፍተኛ የውሀ እጥረት ተከስቷል ሲሉ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸዉን ገልጸዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸው በሀዋሳ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የውሀ ስርጭት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር  አቶ ዮሴፍ ዮንኩራ ፤ ችግሩ የተፈጠረዉ ከሲዳማ ክልል ውጭ በኦሮሚያ ክልል ከተቆፈረዉ የውሀ ጉድጓድ ይገኝ የነበረዉ ውሀ በመቋረጡ መሆኑን ገልጸዋል።

በሻሸመኔ ከተማ ስር ከቢሻን ጉራቻ (ጥቁር ውሀ) በቅርብ ርቀት ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር ጉድጓድ ተቆፍሮ የውሀ አገልግሎት ሲሰጥ ቢቆይም አሁን ግን የአካባቢው ማህበረሰብና አመራሮች ውሃውን መጠቀም አለብን በሚል ጥያቄ እና በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ በደረሰ ጉዳት ምክንያት ውሀውን  መጠቀም አልተቻለም ብለዋል።

አቶ ዮሴፍ አክለዉም ፤ የዉሀ ማስተላለፊያ መስመሮች በግለሰቦች መወጋታቸዉንና ለብልሽት መዳረጋቸዉን ተከትሎም ጥገና ማድረግ አለመቻሉን ገልጸዋል።

በዚህም ምክንያት ከተማዉ እስከ ሀያ በመቶ የውሀ አጥረት መግጠሙን ፤ የተጠቀሱት ክፍለከተሞችና የጋራ መኖሪያ ቤቶችም ለችግር መጋለጣቸዉን አስረድተዋል።

የአካባቢው አስተዳደር ለውሀ ጉድጓዱ የተፈረመዉን ብድር ከፍሎ ውሀዉን እንዲጠቀም አለበለዚያም የራሱን ጉድጓድ እንዲያስቆፍር ቢጠየቅም አለመስማማቱን የሚጠቅሱት ዳይሬክተሩ ችግሩን የዉሀና ኢነርጅ ሚኒስቴር ይቀርፈዋል ብለዉ እንደሚያምኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

መረጃውን የላከው የሀዋሳው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#Sidama #Hawassa

" የግብር መክፈያ መለያ ቁጥር ባለማግኘታችን ከሀገር ወጭ ያገኘነው የስራ እድል ሊያልፍብን ነው " - ወጣቶች

" ያለው አንድ ማሽን ብቻ በመሆኑ ችግሩን ባፋጣኝ መቅረፍ አልተቻለም " -  የሀዋሳ ከተማ ገቢዎች መምሪያ

በሀዋሳ ከተማ እና በአካባቢዉ ያሉ ስራ አጥ ወጣቶች ያገኙትን የውጭ ሀገር የስራ እድል ተከትሎ ማሟላት ካለባቸዉ መስፈርት ውስጥ አንዱ የሆነዉ የግብር መለያ ወይም ቲን ነምበር ለማግኘት ወደ ሀዋሳ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ቢያቀኑም ላለፉት ሰላሳ ቀናት ሊሳካላቸዉ አልቻለም።

እነዚህ ከሀዋሳና አካባቢዋ የተሰባሰቡ ወጣቶች ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት አስተያየት በተለያዬ መልኩ ያገኙትን የስራ እድል ለመጠቀም የጀመሩትን እንቅስቃሴ  የቲን ነምበር ጉዳይ እንቅፋት እንደሆነባቸዉና አሁን ላይ ጭራሹኑ " አናስተናግድም " የሚል ማስታወቂያ መውጣቱን ይናገራሉ።

ከዚህ በተጨማሪም ቢሮዉ " አናስተናግድም " የሚል ማስታወቂያ ካወጣ በኋላ በጎን አገልግሎት ሲሰጥ ይገኛል የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎች በዚህ ምክኒያትም በከፍተኛ  ሁኔታ እየተጉላሉ መሆኑን ያነሳሉ።

ጉዳዩን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ በሀዋሳ ከተማ ገቢዎች መምሪያ የግብር አወሳሰንና የደንበኞች አገልግሎት ሀላፊዋ ወይዘሮ ሙላት ዮሴፍ እንደገለፁት ፤ በከተማዉ አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ስምንት የቲን ነምበር ማሽኖች ስራ ማቆማቸዉን በማንሳት አሁን ላይ በአንድ ማሽን ብቻ እየታገሉ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም " በከተማዉ አገልግሎት እየሰጠ ያለዉ አንድ ማሽን ብቻ በመሆኑ መፍትሄ መስጠት አልቻልንም " ያሉት ሀላፊዋ አገልግሎቱ እስከ ጥር ሰላሳ የታገደው ጫና በመፈጠሩና ወሩ የግብር መሰብሰቢያ ወቅት በመሆኑ ወጣቶችን ማስተናገድ ባለመቻሉ መሆኑን አስረድተዋል።

በሌላ በኩል ፤ የክልሉ መንግስት እንደሀገር የተጀመረዉን የውጭ ሀገር ህጋዊ  የስራ ስምሪትና ኮታ ተከትሎ የተቀመጠውን የትምህርት ደረጃ እድሜና ፍላጎት የመሳሰሉ መስፈርቶች ያሟሉ ከ900 በላይ ወጣቶች ወደ ሳውዲና መሰል የአረብ ሀገራት መላኩን በመግለጽ  አሁን ላይ የቲን ነምበር ፍላጎት ያላቸዉ ወጣቶች እድሉን በመንግስት በኩል ያገኙ  ሳይሆን ይልቁንም በራሳቸዉ መንገድ ያገኙ መሆናቸዉን የክልሉ የስራ ክህሎት ኢንተርፕራይዞች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረጺዮን አበበ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ኃላፊዋ እንደሚሉት ወደ #ካናዳ እና ሌሎችም ሀገራት በራሳቸዉ ጥረት ለመሄድ ቲን ነምበር የሚያስፈልጋቸው ወጣቶችን ለመርዳት ጥረት ላይ መሆናቸውን በመግለጽ መምሪያዉ ያለዉ አንድ ብቻ የቲን ነምበር ማሽን ግን ችግር መፍጠሩን አመልክተዋል።

ችግሩ የሚፈታበትን መንገድ ለመፍጠር ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር እየተወያዩ መሆኑን አስረድተዋል።

አሁን ላይ እስከ ጥር 30 አገልግሎት እንደማይኖር የሚገልጸዉን ማስታወቂያ የሰሙ ወጣቶች ጭንቀት ዉስጥ ሲሆኑ የሚመለከተዉ አካል አስፈላጊዉን መፍትሄ እንዲሰጣቸዉ ጠይቀዋል።

ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የህዝብ ግንኙነት ክፍል ጥያቄ ብናቀርብም አስተያዬት ከመስጠት ተቆጥቧል።

መረጃውን የላከው የሀዋሳዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነዉ።

@tikvahethiopia
#Hawassa

" ተማሪው ላይ ጾታዊ ትንኮሳ ፈጽሟል " በሚል #የተጠረጠረው ርእሰ መምህር በቁጥጥር ስር እንዳሚገኝ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።

በሀዋሳ ከተማ ታቦር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወስጥ አንዲት ተማሪ ርእሰ መምህሯን " ጾታዊ ትንኮሳ ፈጽሞብኛል " በሚል ክስ መመስረቷን ተከትሎ ፖሊስ ተጠርጣሪዉን ግለሰብ ከስራ ገበታዉ ድረስ በመሄድ በቀን 20/05/2016 ዓ/ም በቁጥጥር ስር ማዋሉን ለማወቅ ተችሏል።

የሀዋሳ ከተማ ሴቶችና ህጻናት ቢሮ ሀላፊዋ ወይዘሮ ፍሬህይወት ወልደጻዲቅ ጉዳዩን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጽያ የሀዋሳው አባል ጋር በነበራቸዉ ቆይታ ፤ " የተጠቂዋ ቤተሰቦች ጉዳዩን ይዘዉ ቅድሚያ ለማመልከት የመጡት ወደእኛ ቢሮ ነበር " ያሉ ሲሆን ጉዳዩን ወደ ህግ እንዲወስዱት በማድረግ ማንኛዉንም የህግ ከለላና አስፈላጊ ድጋፎችን ሊሰጡ እንደሚችሉ ቃል ገብተው አንዳበረታቷቸው ገልጸዋል።

ከዚህ በኋላ ክሱ ተመስርቶ ተጠርጣሪዉ በህግ ጥላ እንደዋለና ምርመራ እየተደረገ መሆኑን የገለፁት ኃላፊዋ " አሁን ላይ የሀዋሳ ከተማ ትምህርት መምሪያ መረጃዎችን አጠናክሮ የክስ ሂደቱን ከኛ ጋር ለመደገፍ እንቅስቃሴ ላይ ነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዉ በትምህርት ቤት ውስጥ ሲያዝ የነበረዉን ሁኔታ እና ድርጊቱን በተመለከተ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር የሚያውቀዉ ነገር እንዳለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የትምህርት ቤቱ ምክትል ርእሰ መምህር አቶ ሀንዳሞ ፈይሳ ፤ በወቅቱ ተጠርጣሪው ለጥያቄ ትፈለጋለህ ተብለዉ መሄዳቸውን ፤ አሁን ላይ በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉ ሳምንት እንዳለፋቸው ገልጸዋል።

ክስ አቅራቢዋ ተማሪ ከትምህርት ገበታዋ ደጋግማ በመቅረቷ ምክንያት " ወላጅ አምጭ አታምጭ " በሚል ከሚመለከታቸዉ መምህራኖቿ እና ከተጠርጣሪው ርእሰ መምህር ጋር ስትጨቃጨቅ እንደነበር የሚያስታዉሱት አቶ ሀንዳሞ ፤ ይህ ጉዳይ ለእርሳቸውም ሆነ ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ #አስደንጋጭ እና ግራ ያጋባ መሆኑን አስረድተዋል።

ፖሊስ አስፈላጊዉን ማጣራት አድርጎ እዉነቱ ላይ እስኪደርስ እየጠበቁ መሆኑንም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የሐዋሳዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነዉ።

@tikvahethiopia
#Hawassa

ከሰሞኑ በሀዋሳ ከተማ የሚከሰተዉን የዋይፋይ (WiFi) አገልግሎት መቋረጥ ተከትሎ በርካቶች ስራችን ላይ እንቅፋት እየተፈጠረ ነው ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

እየተፈጠረ ላለው ችግር ኢትዮ ቴሌኮም አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ሲያስተካክለዉ ቢታይም አገልግሎቱ 24 ሰአት እንኳን ሳይቆይ መልሶ ሲቋረጥ ይስተዋላል።

በዚህም ተገልጋዮች ላልተገባ ወጭ እና እንግልት እየተዳረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም የደረሱትን ቅሬታዎች ይዞ የሚመለከተውን አካል አነጋግሯል።

በጉዳዩ ላይ ጥያቄ ያቀረብንላቸው በኢትዮ ቴሎኮም ፤ የደቡብ ሪጅን ዳይሬክተሩ አቶ ጁነዲን አብዱልቃድር " ችግሩ መኖሩ ግልጽ ነው " በማለት አሁን ላይ እንዲህ ያለው የስርቆት ሁኔታ በሁሉም አካባቢ አሳሳቢ መሆኑን ያነሳሉ።

አቶ ጁነዲን አክለዉም ፤ ኬብሉ ከውጭ በውድ ገንዘብ ተገዝቶ  ለማህበረሰቡ አገልግሎት የሚውል በመሆኑ ችግሩን ለመቅረፍ ማህበረሰቡ ከፖሊስ ጋር ተጣምሮ ሊጠብቀው ይገባል ብለዋል።

በዚህ በኩል በሀዋሳም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች ትልቅ እንቅስቃሴ መኖሩን የገለፁት ደግሞ በሪጅኑ የህግ ጉዳይ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ተድላመድህን ቀለመወርቅ ፤ " እስካሁን በተደረጉ እንቅስቃሴዎችም በርካታ ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።

ስርቆቱ #በሀዋሳ እና #ሻሸመኔ ከፍ ያለ መሆኑን የሚገልጹት አቶ ተድላመድህን ካለፈዉ ሀምሌ 1 እስከ ታህሳስ 30 እንኳን በሀዋሳ ከተማ ብቻ 4 መዝገብ ላይ ውሳኔ ተሰጥቶ ከስድስት እስከ ሁለት አመት እስራት መፈረዱን አንስተዋል።

በሀገር ደረጃ  የመሰረተልማት እንቅስቃሴዎችን ለመጠበቅ ታስቦ የወጣዉን 464/67 የተባለ አዋጅ መሰረት አድርጎ ያለመክሰስ ያለመመርመርና ውሳኔ አለመስጠት ችግር ፈተና እንደሆነባቸው ገልጸዋል።

የሚሰጡ ውሳኔዎች እስከ 20 አመት የሚዘልቁ ቢሆኑም ያ እየሆነ አለመሆኑን የሚገልጹት ስራ አስኪያጁ " በዚህ ቻሌንጅ ውስጥ ሆነንም ቢሆን አስተማሪ የሆኑ ውሳኔዎች እንዲሰጡ እየሰራን ነው "  ብለዋል።

መረጃው ተዘጋጅቶ የተላከው በሀዋሳዉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#Hawassa

➡️ " እህታችንን የጠለፋት ግለሰብ ወደ ፓሊስ እንዳንሄድ በእህታችን ህይወት እያስፈራራን ነው " - የተጠላፊዋ ውድነሽ ማቲዎስ ቤተሰቦች በእንባ የታጀበ መልእከት

➡️ " ቆየት ብዬ ዝርዝር መረጃ ሰጣችኃለሁ " - ፖሊስ

ነዋሪነቷ በሀዋሳ ከተማ ነው። ስሟ ውድነሽ ማቲዮስ ይባላል።

በቀን 28/07/2016 ቅዳሜ ምሽት ከቤት " ሰው ይጠራሻል " ተብላ እንደወጣች አልተመለሰችም።

ቤተሰቦቿ ከፖሊስ ጋር ሆነዉ ትገኛለች ብለው ያሰቡበትን ሁሉ ሲያስሱ ቢቆዩም ሊያገኟት አልቻሉም።

በመጨረሻ ያለችበትን ሁኔታ ገልጾ " ተረጋጉ " የሚል መልእክት ያስተላለፈ የስልክ ጥሪ ደረሳቸው። በዚህን ወቅት ነው መጠለፏን ያወቁት።

የተጠላፊዋ ወንድም ዘላለም ማቲዮስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " ስልክ ደውሎ #ከማስፈራሪያ ጋጋታ ጋር የመጠለፏን ዜና ጠላፊው ራሱ አሰማን " ብለዋል።

" ይህ አያሌው ጌታሁን የተሰኘ ግለሰብ ሀዋሳ በሚገኘዉ መኖሪያ ቤታችን ውስጥ ተከራይታ በምትኖረዉ እህቱ በኩል የአብረን እንሁን የሚል የፍቅር ጥያቄ ሲያቀርብ እንደነበር እናውቃለን " ሲሉ የታጋቿ ወንድም ገልጸዋል።

" ጥያቄዉ ' ፍቅረኛ አለኝ ' በሚል ምክኒያት አወንታዊ ምላሽ አለማግኘቱን ተከትሎም  ከእሷ ባለፈ የፍቅር ጓደኛዋን ሁሉ ሲያስፈራራ ቆይቷል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ይህ ሙከራዉን ጨምሮ ብዙ መንገዶች ቢሞክርም አልሳካ እንዳለዉ ሲረዳ በመጨረሻም ከእህቱ ጋር ተጋግዞ ጠለፋዉን ፈጽሟል " ሲሉ አስረድተዋል።

" አሁን ላይ ወደፖሊስ በመሄድ ሁኔታዉን አሳዉቀን ክስ ለመመስረት እንቅስቃሴ ጀምረናል " የሚለዉ የታጋቿ ወንድም " ከአጋቹ ባለፈ ተባባሪ ለነበረችው እህቱም  ላይ መጥሪያ አዉጥተናል " ብሏል።

" አሁን ላይ ወላጆቻችን በታላቅ ለቅሶና ሀዘን ውስጥ ናቸዉ የሚመለከተዉ አካል ህግ አስከብሮና ጥፋተኛዉን በመያዝ ልጃችንን ያስመልስልን " ሲል ተማጽኗል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዡን ኢንስፔክተር መልካሙ አየለን አነጋግሯል።

አዛዡ ጉዳዩን በጥብቅ እየተከታተሉት መሆኑን የገለጹ ሲሆን ዝርዝር መረጃ ቆየት ብለው እንደሚያሳዉቁን ቃል ገብተዋል።

በቀጣይ የኢንስፔክተሩን ዝርዝር ሀሳብ እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተካተቱበት መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል።

መረጃውን አዘጋጅዮ የላከው የሀዋሳው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#Hawassa

ዛሬ ከሀዋሳ ከተማ ከዩኒቨርስቲው ፊት ለፊት በተለምዶ " ፍየል ገበያ " አካባቢ አንድ ወጣት ሞቶ ተገኝቷል።

የሟችን ማንነት ማወቅ ያልቻሉት በአካባቢው ላይ የነበሩ ሰዎች ተደናግጠው ሲመለከቱ ነበር።

በአካባቢዉ የተፈጠረውን ግርግር ተከትሎ ቦታው ላይ የደረሰው የከተማው ፖሊስ ቦታው የገበያ ግርግር ያለበት ከመሆኑ የተነሳ አስክሬኑን ፎቶ ከሚያነሱ ግለሰቦች ሲጠብቅ ነበር።

በስፍራዉ የተገኘዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳ ቤተሰብ አባል ሁኔታውን ለማጣራት ባደረገዉ ጥረት የአካባቢዉ ሰዎች ግራ በሚያጋባ ሁኔታ ድንገት ሞቶ እንዳዩትና ከዚህ በፊት አይተዉት እንደማያውቁ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ስለሁኔታዉ የጠየቅናቸዉ በቦታዉ የደረሱ የፖሊስ ቡድን አባላት በበኩላቸዉ ጉዳዩን የማጣራት ስራ እንደተጀመረ በመግለፅ ለጊዜዉ ለህዝብ የሚሰጥ መረጃ እንደሌላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከመሸ የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን ስለ ጉዳዩ ጠይቋል።

በዚህም ሟች የዩኒቨርስቲ ተማሪ እንዳልነበር አረጋግጧል።

ይሁንና በሟች አስክሬን ላይ ጉዳት ስለማይታይ የሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ተወስዶ ከተመረመረ በኋላ ለተጨማሪ ምርመራ ወደ አዲስ አበባ እንዲሄድ መወሰኑን ገልጿል።

@tikvahethiopia
#Hawassa

" እንደሚወራው አይደለም ፤ ከአንድ ቤት በላይ የከፋ ጉዳት አላደረሰም " - የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ

በሀዋሳ ከተማ የተነሳ የእሳት አደጋ አንድ መዝናኛ ቤት አውድሞ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።

ዛሬ ረፋድ 4 ሰዓት አካባቢ በከተማው በተለምዶ 05 በመባል በሚታውቀዉ ሰፈር (አደባባይ አለፍ ብሎ ወይም ከመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት/አስፓልት ተሻግሮ) የተነሳው የእሳት አደጋ አንድ መዝናኛ ቤትን በከፋ ሁኔታ አውድሞ በቁጥጥር ስር ውሏል።

እሳት አደጋው የደረሰው በማህበር ተደራጅተዉ በምግብና መጠጥ ሽያጭ የሚተዳደሩ ወጣቶች ውስጥ በአንደኛው ቤት ነው።

የእሳት አደጋው መፈጠሩን ተከትሎ በአካባቢው ግርግር ቢፈጠርም ከሰአት በኋላ ሁሉም ተረጋግቶ ወደተለመደው እንቅስቃሴ ተመልሷል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የከተማው ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ወንድሙ ቶርባ ፤ " ችግሩ እንደተፈጠረ የሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና የኢንዱስትሪው መንደር የእሳት ብርጌድ በፍጥነት ደርሶ ተቆጣጥሮታል " ብለዋል።

" ከፍተኛ አደጋ በደረሰበት መዝናኛ ቤት ውስጥ በነበረ የኤሌክትሪክ ገመድ ላይ በተፈጠረ እሳት ነው አደጋው የተፈጠረው " ሲሉ ገልጸዋል።

በአደጋው በመዝናኛ ቤቱ ላይ ውድመት መድረሱን ጠቁመዋል።

አደጋው በደረሰበት ወቅት በአካባቢው ወደነበሩ ቤቶች እሳቱ እንዳይስፋፋ ሌሎች ሰዎች እቃቸዉን ቢያወጡም ቆይተው ወደቤቶቻቸዉ ተመልሰዋል ብለዋል።

" ከሁኔታው ጋር በተያያዘ ግርግር ቢፈጠርም ሰዎች ተመልሰው ወደ ስራቸዉ ገብተዋል " ሲሉ አክለዋል።

" አደጋው እንደሚወራዉ #እጅግ የከፋ አይደለም " ያሉ ሲሆን ከአንድ ቤት በላይ የከፋ ጉዳት አላደረሰም ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
#Hawassa

➡️ " ንፋስ በመጣ ቁጥር ጉዳት እየደረሰ ነው። እሮብ የአንድ ሰው ህይወት አልፏል " - የሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል

➡️ " ጉዳት የደረሰበት የካፌ አስተናጋጅ ነው። በወቅቱ ወደህክምና ተወስዶ የህክምና እርዳታ ቢደረግለትም ህይወቱ ግን ሊተርፍ አልቻልም " - የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ

በሀዋሳ ከተማ ፤ ፒያሳ በሚገኘው ንብ ባንክ ህንጻ ላይ የወደቀ መስታወት የአንድ ወጣት ህይወት ቀጥፏል።

ህንጻው በዝናብና ንፋስ ወቅት እቃ ሲወድቅበት የመጀመሪያው እንዳልሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሀዋሳ የቤተሰብ አባላቱ ጥቆማ ደርሶታል።

በቅርቡ የተመረቀዉ የንብ ህንጻ ከዘጠነኛ ፎቅ ላይ የወደቀ መስታወት የህንጻው ወለል ላይ ስራ ላይ የነበረ ሰራተኛ ላይ ማረፉን ተከትሎ ሰራተኛው ህይወቱ አልፏል።

በሀዋሳ እሮብ ከ9 ሰአት በኋላ የነበረው ከባድ ዝናብና ውሽንፍር ባስከተለዉ ነፋስ ከህንጻዉ ላይ የወደቀ መስታወት የሰዉ ህይወት ማጥፋቱን ለማረጋገጥ ችለናል።

አንድ የሀዋሳ የቤተሰባች አባል ፤ " ንፋስ በመጣ ቁጥር ከህንጻው ላይ በሚወድቅ ቁስ ተደጋጋሚ ጉዳት በግለሰቦች ላይ ሰራተኞች ላይ እየደረሰ ነው። እሮብ አንድ ሰራተኛ መስታወት ወድቆበት እጁ የመቆረጥ ፣ አናቱ ላይ የመጎዳት በኃላም ህይወቱ አልፏል። ህንጸው ግልጽ የሆነ የግንባታ ጉድለት ይታይበታል " ሲል ቃሉን ሰጥቷል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የሰጡት የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ ወንድማገኝ ቶርባ ፤ ጉዳት የደረሰበት ወጣት የካፌ አስተናጋጅ መሆኑንና በወቅቱ ወደህክምና ተወስዶ የህክምና እርዳታ ቢደረግለትም ህይወቱ ግን ሊተርፍ እንዳልቻለ ገልጸዋል።

ይሁንና " ህንጻው ላይ ተደጋጋሚ ችግር ተስተውሏል " ለሚባለዉ ቅሬታ ካሁን በፊት የደረሰ አደጋን የተመለከተ ሪፖርት የለም ሲሉ ገልጸዋል።

በወቅቱ በዚህ ህንጻ ውስጥ ከደረሰዉ አደጋ  ውጭ በከተማዉ የተከሰተዉ ነፋስ በርካታ የንብረት ጉዳት ማስከተሉንም አስታውሰዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የህንጻዉን አስተዳዳሪዎች በጉዳዩ ዙሪያ ለማነጋገር ያደረገዉ ሙከራ አልተሳካም። ምላሽ አለም ካሉ መስተናገድ ይችላሉ።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Hawassa

በሀዋሳ ከተማ የስፓርት ውርርድ ( #ቤቲንግ ) ቤቶች እየታሸጉ / እየተዘጉ ይገኛሉ።

ይህ ተከትሎ የስፖርት ውርርድ ቤት ባለቤቶች " እንዴት የንግድ ፈቃድ እያለን ይዘጋብናል ? " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

እነዚህ የስፖርት ውርርድ ቤቶች ከወራት በፊት በተለያዩ ምክኒያቶች ተዘግተው የቆዩ ሲሆን በቅርቡ ተከፍተው ነበር።

አሁን ላይ ተመልሰው መዘጋት/መታሸግ መጀመራቸው ግራ እንዳጋባቸውና ልክ እንደባለፈዉ ጊዜ ከስራቸዉ ተስተጓጉለው ቤት መዋል መጀመራቸው እንዳሳዘናቸው ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልጸዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ሀዋሳ ቤተሰብ አባል ፥
° ቤቶቹን ለምን ታሸጉ ?
° መፍትሄውስ ምንድን ነው ? ሲል የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለን ጠይቋል።

እሳቸውም ፤ " #በሲዳማ_ክልል_ስር የወጣ አንድም የንግድ ፈቃድ የለም " ብለዋል።

" ከወራት በፊት ከነዚህ አካላት (ቤቲንግ ቤቶች) ጋር በነበረን ውይይት የንግድ ፈቃድ በማውጣት ህጋዊ እንዲሆኑ ተግባብተን ነበር " ሲሉ አስታውሰዋል።

" ይሁንና ከረዥም ጊዜ በኋላ ዳግም ስናጣራ አሁንም ህጋዊ መሆን አልቻሉም " ያሉት ሀላፊው " ከዚህ ባለፈም እነዚህ ቤቶች በትምህርት ቤት ፣ በሀይማኖት ተቋማትና በመኖሪያ ሰፈሮች እንዲሰሩ አይፈቀድም ሌላዉ የመዘጋታቸዉ ምክኒያት ይኸው ነው " ሲሉ አሳውቀዋል።

ለግለሰቦቹ በሰላማዊ መንገድ ምክንያቱ ተነግሯቸው ቤታቸዉ እየተዘጋ መሆኑን የገለጹት አዛዡ ፤ " ከዚህ ዉጭ ' ገንዘብ ተወሰደብኝ ' እንዲሁም ' የአላግባብ ህገወጥ የሆነ ተግባር ተፈጽሞብኛል ' የሚል አካል በማንኛዉም ሰአት ወደ ሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመምጣት ሊያመለክት ይችላል " ብለዋል።

ቤቶቹ ተመልሰው #የመከፈት እድል አላቸዉ ወይ ? ተብለው የተጠየቁት ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ " መጀመሪያ ህጋዊ ይሁኑ ከዛ በኋላ ከፖሊስ በተጨማሪ የሚመለከታቸዉ አካላት የሚመለከቱት ጉዳይ ይሆናል " ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
#Hawassa

በሀዋሳ እንደ አዲስ አበባው አይነት የመንገድ ማስፋትና የማስዋብ ስራ / የኮሪደር ልማት / መታሰቡን ተከትሎ " የሚፈርሱ ይዞታዎቻችን ግምት ባልታወቀበት እና በቂ የሆነ የዝግጅት ጊዜ ባልተሰጠበት ይዞታችሁን አፍርሱ " ተብለናል ያሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ስራው ወደተግባር ከመግባቱ በፊት ካንዴም ሁለቴ ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት ማድረጉን ገልጿል።

በቅርቡ በነበረ መድረክ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ መኩሪያ ማርሻዬ ፤ 10 መንገዶች መለየታቸውን እና እነዚህን ውብና ዘመናዊ አድርጎ በመስራት ለትዉልድ የሚተላለፍ አሻራ የመጣል እቅድ መያዙን ገልጸው ነበር።

በመድረኩ ተገኝተው የነበሩ ነዋሪዎች ልማቱን እንደሚደግፉ የካሳ እና የዝግጅት ጊዜ ግን እንዲሰጣቸዉ ጠይቀው ነበር።

ይህን ተከትሎ የንብረት ግምትን በተመለከተ ተመጣጣኝ ካሳ እንደሚኖርና የቦታ ሽግሽጎችም እንደሚደረጉ በመግለጽ ከንቲባዉ ምላሽ ሰጥተዋል።

ይሁንና የከተማ መስተዳድሩ ከመረጣቸዉ 10 ቦታዎች መካከል 3ቱን ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ ማሰቡን ተከትሎ በተለይ ከስሙዳ በሳዉዝ ስታር ሆቴል ወደ ኢንዱስትሪ መንገድ የሚሄደው እና ከሻፌታ አደባባይ አስከሳዉዝ ስፕሪንግ ያለው መስመር ያሉ ነዋሪዎች ጥያቄ እንዳላቸው ገልጸዋል።

በዚህ በኩል በርካታ የመኖሪያ ቤቶች፣ ድርጅቶችና ትምህርት ቤቶች የሚነኩ መሆኑን ተከትሎ ነዋሪዎች ድንጋጤ ውስጥ መግባታቸዉን ተናግረዋል።

በከተማ መስተዳድሩ በእቅድ የተያዘዉ  የከተማ ልማት የምንደግፈዉ ቢሆንም የካሳና የቦታ ሽግሽግ ጉዳይ ባልተወሰነበትና ሰዉ ዝግጅት ባላጠናቀቀበት " በቅርቡ ፈረሳ ይጀምራል " መባሉ አሳስቦናል ብለዋል።

ነዋሪዎቹ በተሰጣቸው ደብዳቤ በ2 ቀን ውስጥ አፍርሰው ማስተካከያ እንዲያደርጉ መባላቸውን ጠቁመዋል።

በተጠቀሱት አካባቢዎች ላይ የሚፈርሱ ድርጅቶች መኖሪያ ቤቶችና አጥሮች ምልክት በመደረጉና ስራውበፍጥነት ይጀመራል መባሉን ተከትሎ ፦
➡️ የካሳና የቦታ ለዉጥ ወይም ሽግሽግ ጉዳይ ምን ይመስላል ?
➡️ በትክክል ስራዉስ መች ይጀምራል ? በማለት ጥያቄ ይዘን የሚመለከተዉን አካል ለማናገር ያደረግነዉ ጥረት አልተሳካም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ጉዳይ ምላሽ ይዞ በቅርቡ ለመምጣት ይሞክራል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
#Sidama #Hawassa

° " በሀዋሳ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ነዳጅ በመቋረጡ ለከፋ ችግር ተጋልጠናል " - የህዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪዎች

° " በእጃችን ምንም ነዳጅ ባለመኖሩ ተጠቃሚው ለተወሰነ ጊዜ ይታገሰን " - የሀዋሳ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ


ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016 በሀዋሳ ከተማ ያሉ ማደያዎች መዘጋታቸውን ተከትሎ በርካታ የህዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪዎች መቆማቸውን በመግለጽ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" ከሰሞኑ በሰልፍና በጎን በሚገቡ ህገወጥ ቀጅዎች ስንማረር መሰንበታችን ሳያንስ ዛሬ ደግሞ በየቀኑ በቴሌግራም የሚለቀቀዉ የነዳጅ ፕሮግራም ተቋርጦ በከተማው ውስጥ ያሉ ማደያዎች ሁሉ ዝግ ሆኑብን "  የሚሉት አሽከርካሪዎች በዚህም በእጅጉ ተቸግረናል ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአሽከርካሪዎቹን ቅሬታ ይዞ የሀዋሳ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ችሎትን አነጋግሯል።

እሳቸውም ፤ " እንደከተማ አንድ ማደያ ብቻ አገልግሎት እየሰጠ ነው " በማለት በከተማዉ ምንም አይነት ነዳጅ አለመኖሩን ገልጸውልናል።

የቴሌግራሙ ፕሮግራም አለመውጣቱም ከዚህ የመጣ መሆኑን አስረድተዋል።

አሁን ላይ ችግሩ በጣም አሳሳቢ በመሆኑ በጉዳዩ ላይ ስብሰባ መቀመጣቸውን ገልጸው "  ማህበረሰቡ እና አሽከርካሪዎች ይህን አውቀው እንዲታገሱ " ሲሉ ጠይቀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia