TIKVAH-ETHIOPIA
1.44M subscribers
55.9K photos
1.4K videos
202 files
3.77K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #TPLF " እኔ ሳላውቀው ያለፈው ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ጉባኤ ለማካሄድ በድብቅ ሲሰራ ነበር። ይህ እንዲሆን ለምን አስፈለገ ?  "  - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ ጉዳዮች አስመልክተው ለድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ቃለመጠይቅ ሰጥተው ነበር። አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ? - የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት…
#Tigray : " ... ከጦርነቱ በኋላ የተቋቋመው መንግስት ስራውን ለመስራት አቅም ያጣበት ወቅት ላይ እንገኛለን " - አቶ ጌታቸው ረዳ

ሀምሌ 25 እና 26/2016 ዓ.ም " የትግራይ ፓለቲካዊ አስተዳደር " በሚል ርእሰ አንድ መድረክ መቐለ ውስጥ ተካሂዶ ነበር።

የክልሉ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ተገኝተውም ንግግር አድርገው ነበር።

ምን አሉ ?

- በትግራይ የሃሳብ ጠቅላይነት ሊኖር አይችልም። ልዩነታችን በሰለጠነ መንገድ ከመፍታት ውጪ ሌላ አማራጭ የለም።

- የትግራይ ህዝብ ለዘመናት የቆዩ የዓለም ስልጣኔዎች ባለቤት የነበረ ቢሆንም እኛ ሳንሰራው በቀረ ወይንም ባለንበት አከባቢ አቀማመጥ ትውልዶች ወደ ጦርነት እየገቡ ለቀውስ እየተጋለጡ መጥቷል።

- እጅግ አሰቃቂ እና ደም አፋሳሽ በነበረው ጦርነት ጥያቄ ውስጥ የገባው የህዝቡ ህልውናውን በማረጋገጥ አንፃራዊ ሰላም ቢያገኝም ከጦርነቱ በኋላ የተቋቋመው መንግስት ስራውን ለመስራት አቅም ያጣበት ወቅት ላይ እንገኛለን።

- ፓለቲካዊ ልዩነታችን በሰለጠነ መንገድ በመፍታት በጦርነቱ ክፉኛ የተጎዳው ህዝባችን ሁሉንም አቅሞቻችን አሟጠን በመጠቀም መምራት ይጠበቅብናል።

#TikvahEthiopiaFamilyMK

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #TPLF " እኔ ሳላውቀው ያለፈው ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ጉባኤ ለማካሄድ በድብቅ ሲሰራ ነበር። ይህ እንዲሆን ለምን አስፈለገ ?  "  - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ ጉዳዮች አስመልክተው ለድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ቃለመጠይቅ ሰጥተው ነበር። አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ? - የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት…
#TPLF

የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ አባላት ነጋ አሰፋ እና ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ ህወሓት ለማካሄድ ካቀደው ድርጅታዊ ጉባኤ ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ለድምጺ ወያነ ሰጥተው ነበር።

በዚህም ፤ " ጉባኤው እንዳይካሄድ የተቋወመ የለም " ብለዋል።

ጥያቄያው መተማመንንና መግባባት የተደረሰበት አሳታፊ፣ ግልፅና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የማድረግ ጉዳይ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ከጉባኤው በፊት መታየትን መጥራት ያለባቸው በርካታ ጉዳዮች እንዳሉ የጠቀሱት ከፍተኛ አመራሮቹ " ድርጅቱ ከፍተኛ የሆነ የስትራቴጂክ አመራር ውድቀት አጋጥሞታል ሊካሄድ የታሰበው ጉባኤ ደግሞ ይህንን በመሰረቱ ሊፈታ የሚችል መሆን ይገባዋል "  ሲሉ ተናግረዋል።

" ከጉባኤው በፊት የተካሄደው ደም አፋሳሽና አሰቃቂ ጦርነት ሂደቱና ውጤቱ በጥልቀት መገምገም ይቅደም " ሲሉም ተደምጠዋል።

አሁን የሚታየው ልዩነት ከጉባኤው በፊት በመግባባት እና በመተማመን መፈታት እንደሚገባ አመልክተው " በችኮላ እንዲካሄድ ይታሰበው ጉባኤ የግል ሰብእናና ስልጣን ከማስጠበቅ ያለፈ እርባና የለውም " ብለውታል።

" የህዝብና የድርጅቱ ጥቅም የሚያስቀድም አካል ጉባኤ ለማካሄድ መጣደፍ የለበትም "  ሲሉ አሳስበዋል።

#TPLF #Tigray

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray : " ... ከጦርነቱ በኋላ የተቋቋመው መንግስት ስራውን ለመስራት አቅም ያጣበት ወቅት ላይ እንገኛለን " - አቶ ጌታቸው ረዳ ሀምሌ 25 እና 26/2016 ዓ.ም " የትግራይ ፓለቲካዊ አስተዳደር " በሚል ርእሰ አንድ መድረክ መቐለ ውስጥ ተካሂዶ ነበር። የክልሉ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ተገኝተውም ንግግር አድርገው ነበር። ምን አሉ ? - በትግራይ የሃሳብ ጠቅላይነት ሊኖር አይችልም።…
#Tigray : በትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር በተደራጀ ገለልተኛ በተባለ አንድ አጥኚ ቡድን የክልሉን ሁኔታ በተመለከተ ጥናት ተደርጎ ነበር።

በዚህም ፦

በክልሉ ሕገወጥነት መስፈኑ እና ይህም ወደ ስርዓት አልበኝነት የሚሄድበት ዕድል ከፍተኛ መሆኑን ገልጿል።

የመንግሰት መዋቅር በአንድ ፓርቲ መጠለፉን ያመለክታል።

የክልሉ ህዝብ እና መንግስት ሀብት በግለሰቦች ፣ የውጭ ዜጎች ጭምር እየተዘረፈ እንደሆነ ያሳያል።

የፍትህ ስርዓቱ ተአማኒነት ማጣቱን ያመለክታል።

በህዝቡ ዘንድን ተስፋ ማጣትና ስደት መንሰራፋቱ ይኸው ጥናት አሳይቷል።

የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፥ መንግስት ስራው እንዳይሰራ መቸገሩን ገልፀዋል።

የተቃዋሚ ፓርቲ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ ሊቀመንበር አቶ አሉላ ሃይሉ ፤ " የክልሉ አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት ከመስራት ይልቅ፥ ችግሮች በመዘርዘር ተጠምዷል " ብለዋል።

" እኔ እኮ በጣም የሚያሳዝነኝ ነገር በትግራይ ችግሮቹ ተዘርዝረው እየተነገሩ ያሉት፣ ችግሮቹን ሊፈቱ ስልጣን በያዙ ሰዎች ነው። ኃላፊነታችሁ ልትወጡ ይገባል " ሲሉ ለዶቼ ቨለ ተናግረዋል።
#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
" 75 ሺህ ታጣቂዎች ወደ ህብረተሰቡ ለመቀላቀል ያለመ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ

ትላንትና በትግራይ ታዋጊዎች ወደ ህብረተሰብ ለመመለስ ያለመ የውይይት መድረክ ተካሂዶ ነበር።

መድረኩን አዘጋጅተው የነበረው የብሄራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን እና USAID ኢትዮጵያ በትብብር ነበር።

በዚህም መድረክ የተገኙት የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ፤ " በ2015 ዓ.ም ወደ ህብረተሰብ ይቀላቀላሉ የተባሉ 50 ሺህ ታጣቂዎች ነበር በድጋፍና የማቋቋምያ እጦት በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኛሉ " ብለዋል።

" ባለፈው እጅግ ደም አፋሳሽና አሰቃቂ ጦርነት ብዙ ነገሮች ወድመዋል ተመሳቅለዋል የተሰዋ አካሉ የጎደለ ፣ ንብረቱ ወድሞበት ከሃብት ወደ ደህነት የወረደ ብዙ ነው " ብለዋል።

ጀነራል ታደሰ " ወደ ህብረተሰቡ የሚቀላቀሉ ታጣቂዎች ከባባድ ችግሮች ያለባቸው ስለሆኑ የቀናጀ ሁለንተናዊ ማቋቋምያ እንደሚያስፈልጋቸው ጠቁመዋል።

" ታጣቂው ወደ ህብረተሰቡ ተቀላቅሎ ከጦርነትና ጦርነት ወለድ አስተሳሰብ ርቆ የሰላምና  ፀጥታ ጠባቂ እንዲሁም በኢኮኖሚያዊ እድገት የሚጠበቅበት ሃላፊነት እንዲወጣ ከተፈለገ ድጋፍ ፣ ክብርና እውቅና ያሻዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ ታሳቢ ያደረገ 75 ሺህ ታጣቂዎች ወደ ህብረተሰቡ ለመቀላቀል ያለመ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።

#Tigray

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #TPLF " እኔ ሳላውቀው ያለፈው ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ጉባኤ ለማካሄድ በድብቅ ሲሰራ ነበር። ይህ እንዲሆን ለምን አስፈለገ ?  "  - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ ጉዳዮች አስመልክተው ለድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ቃለመጠይቅ ሰጥተው ነበር። አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ? - የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት…
#Tigray #TPLF

"ሊካሄድ በታቀደው ጉባኤ አልሳተፍም ! " - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዜያዊ አስታዳደር ፕሬዜዳንት እና የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ ዛሬ ዓርብ ነሀሴ 3/2016 ዓ.ም ለህወሓት ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ፣ ለድርጅቱ የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ተኽለብርሃን ኣርኣያ በፃፉት ደብዳቤ በጉባኤው እንደማይሳተፉ አረጋግጠዋል።

ፕሬዜዳንቱ በደብዳቤያቸው የድርጅቱን ከፍተኛ አመራሮች ውሳኔ በጣሰው ጉባኤና የምዝገባ ሂደት እንደማይሳተፉ በመግለፅ " ህወሓት መዳን የሚችለው አባላቱና አመራሩ በሚያካሂዱት ጤናማ እንቅሰቃሴ ነው " ሲሉ አስታውቀዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
#NewsAlert #Tigray

" የህዝብ ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ላለልተወሰነ ጊዜ የድጋፍም ይሁን የተቋውሞ ሰልፍ ማድረግ ተከልክሏል " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር፣ ምክትል ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ዛሬ ከሰዓት መግለጫ ሰጥተዋል።
 
በዚህም ፤ " ፓለቲካዊ አለመግባባት ወደ ማንኛውም የፀጥታ አደጋ እንዲሸጋገር አንፈቅድም " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

" የህዝብ ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ላለልተወሰነ ጊዜ የድጋፍም ይሁን የተቋውሞ ሰልፍ ማድረግ ተከልክሏል " ያሉት ጀነራል ታደሰ ወረደ " ፓለቲካዊ ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፈታት አለበት " ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፤ በቀላል እና ከባባድ ወንጀሎች ተሳትፈዋል ያላቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የማዋል ኦፕሬሽን መጀመሩ ይታወሳል።

ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረዳ በዛሬ መግለጫቸው ላይ በህግ ቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦችና ብዛታቸውን ባይገልጹም " የህግ የበላይነት ለማስከበር የተጀመረው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል " ሲሉ አሳውወዋል።

የዘንድሮ የአሸንዳ በዓል አከባበርና የህወሓት ጉባኤ ከመካሄድ ጋር ተያይዞ  የፀጥታ ችግር እንዳይፈጠር ተገቢ እና ጥብቅ የፀጥታ ስራ ይሰራል ሲሉም ተናግረዋል።

በህወሓት አመራሮች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ እና እየከረረ መሄዱ በርካቶችን ያሳሰበ ጉዳይ ሆኗል።

ሁኔታው የፀጥታ ስጋት ደቅኗል የሚሉ አልጠፉም።

ሌ/ጄነራል ታደሰ ግን ፓለቲካዊ ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፈታት እንዳለበት ፤ ማንኛውም ልዩነት ወደ ፀጥታ አደጋ እንዲሸጋገር የጸጥታ አካሉ እንደማይፈቅድ አስጠንቅቀዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

Photo Credit - TG TV

@tikvahethiopia            
#Tigray
 
መምህርቷ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።

በትግራይ፣ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ ነሀሴ 7/2016 ዓ.ም ሌሊት ጭካኔ የተሞላበት እጅግ አሰቃቂ ግድያ ተፈፅሟል።

አስቃቂ ግድያ የተፈፀመባት መምህርት ብርኽቲ ተስፋማርያም ትባላለች።

የትግራይ መምህራን ማህበር በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ በአባሉ ላይ በተፈፀመው ጭካኔ የተሞላበት ዘግናኝ ግድያ የተሰማው ጥልቅ ሃዘን ገልጿል።

የዚህ እጅግ አሰቃቂ የወንጀል ተግባር ፈፃሚዎች በአስቸኳይ ተጣርተው ተመጣጣኝ ቅጣት እንዲጣልባቸውም ጠይቋል።

ሟች መምህርት ብርኽቲ ተስፋማርያም ከሑመራ ተፈናቅለው ከባለቤታቸውና 3 ልጆቻቸው በእንዳስላሰ ከተማ ይኖሩ እንደነበር ማህበሩ አመልክቷል።

" የሟች ባለቤት ቤት ውስጥ አለማደሩ ያጠኑና ያረጋገጡ ግፈኞች ነሀሴ 7/2016 ዓ.ም መምህርትዋ ልጆችዋ ፊት አርደው ገድልዋታል " ብሏል የመምህራን ማህበሩ።

" ይህ አስነዋሪ የግፍ ተግባር የትግራይ ህዝብ መልካም እሴት የሚፃረርና የሚያጎድፍ ሰይጣናዊ ተግባር ነው " ያለው መገለጫው " የፍትህ አካላት የአሰቃቂ ተግባሩ ፈፃሚዎች በማጣራት የህግ የበላይነት እንዲያረጋግጡ እንጠይቃለን " ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ፣ የግድያ ተግባሩ የሚመለከት ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ወደ እንዳስላሰ ሽረ ፀጥታና ፓሊስ ፅህፈት ቤት ስልክ ደውሏል።

የከተማው ፓሊስ ዋና አዛዥ የሆነ ኢንስፔክተር አወጠሀኝ ፣ የወንጀል ተግባሩ የማጣራት ጉዳይ በሃላፊነት የያዙት የወንጀል ማጣራት ሃላፊ መሓሪ ኪዳነ ደውሎ የሁለቱም የእጅ ስልካቸው አይነሳም።

ይሁን እንጂ ከከተማው የፀጥታ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ በሪሁ ባገኘነው መረጃ በሟችዋ መምህርት ላይ የተፈፀመው የወንጀል ተግባር የሚያጣራ ከጸጥታ ከፖሊስና የህግ አካላት የተውጣጣ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየሰራ ይገኛል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
#Tigray

" ሁሉም ትግራዋይ ወዴት እያመራን ነው ? ብሎ ራሱን በራሱ በመጠየቅና በመመለስ የመፍትሄ ሃሳብ መስጠት ይገባዋል " - አቶ ጌታቸው ረዳ

በመቐለ ከተማ ዓለም አቀፍ የትግራይ ሙሁራን ማህበር (GSTS) ለ3 ቀናት ያዘጋጀው ትግራይ ክልል መልሶ በማቋቋም ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ ጀምሯል።

በመክፈቻው መርሃ ግብር ፦

➡️ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ

➡️ ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በም/ ፕሬዝዳንት ማዕረግ ያልተማከለ አስተዳደርና ዴሞክራታይዜሽን ካቢኔ ሴክሬተሪያት ኃላፊ

➡️ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወትን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተው ነበር።

በመክፈቻው አቶ ጌታቸው ንግግር አድርገዋል።

በዚህም ፥ " ሁሉም ትግራዋይ ወዴት እያመራን ነው ? ብሎ ራሱን በራሱ በመጠየቅና በመመለስ የመፍትሄ ሃሳብ መስጠት ይገባዋል " ብለዋል።

" ያለውን መድረክ በመገንዘብ የመፍትሄ ሃሳብ በማስቀመጥ የበኩሉ ሃላፊነት መወጣት አለበት " ሲሉም ተናግረዋል።

" የሙሁራኑ ውይይት ማንኛውም ፓለቲካዊ ልዩነት ይኑር ችላ መባል እና መታለፍ የሌለባቸውን በመያዝ እንዲጠሩ መስራት ይጠበቅበታል " ሲሉ አስገዝበዋል።

ለ3 ቀናት ይቆያል በተባለው የውይይት መድረክ በርካታ ጥናታዊ ፅሁፎች ይቀርባሉ ፣ ውይይትም ይደረጋል ተብሏል።

ከመላው ኢትዮጵያ ጨምሮ ፥ ከአፍሪካ ፣ አሜሪካ ፣ አወሮፓና ልሎች የዓለም ክፍሎች የተጋበዙ የትግራይ ሙሁራን ተሳታፊ እንደሆኑ ተሰምቷል።

ፎቶ ፦ ድምጺ ወያነ

@tikvahethiopia 
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF ከህወሓት ከፍተኛ አመራር አንዱ የሆኑት የማይጨው ከተማ ከንቲባ አቶ የማነ ንጉስ ለዶቼ ቨለ በሰጡት ቃል ፤ " ጉባኤው የተወሰነ ቡድን ለማጥቃት በችኮላ የተጠራ ነው " ብለዋል። በዚህም እሳቸው ጨምሮ በርካቶች ተቃውሞዋቸውን በመግለፅ ከመድረኩ መቅረታቸውን አመልክተዋል። የህወሓት ማእከላዊ ቁጥጥር ኮምሽን ሊቀ መንበር አቶ ተክለብርሃን አርአያ ትላንት በሰጡት መግለጫ ፥ " 14ተኛ ጠቅላላ…
#Tigray

" ሁሉንም የፓለቲካ ሃይሎች ያቀፈ መንግስት በአስቸኳይ መመስረት ያስፈጋል " - ሦስት የፓለቲካ ፓርቲዎች

በትግራይ የሚንቀሳቀሱት ባይቶና፣ ሳወት፣ ናፅነት የፓለቲካ ፓርቲዎች በጋራ በሰጡት መግለጫ ፤ " ሳምንቱን በስርዓቱ ባለቤቶች መካከል በመካሄድ ያለው ህገ-ወጥ እንቃስቃሴና ፍጥጫ ተው መባል ይገባዋል " ብለዋል።

በህወሓት አመራሮች የተፈጠረው ፍጥጫ ተከትሎ በህዝቡ የሚታየው መረበሽ ያወገዙት ሦስቱ  ተፎካካሪ ፓርቲዎች " ህግ እየጣሱ በህዝብ ካባ ስም ለመደበቅ የሚደረገው መሯሯጥ እናወግዛለን " ሲሉ ገልጸዋል።

" ለቡድናዊ ጥቅም ሲባል በህዝብ ቁማር መጫወት መቆም አለበት "  ያሉት ፓርቲዎቹ " ደርጅታዊ ይሁን ቡድናዊ ጉዳይ ከህዝብ ህልውና ማጣበቅ እንፀየፈዋለን እንዲቆምም እናሳስባለን " ብለዋል።  

" የህዝብ ሰላም፣ ህልውናና ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ህገ-ወጥ  ፓለቲካዊ ተግባር ሲታይ የሚመለከተው የፀጥታ አካልና ህዝብ ያለማዳላት በአስቸኳይ የማስቆም ሃላፍነቱን መወጣት አለበት " ሲሉም ገልጸዋል።

" የተፈጠረው ፓለቲካዊ አለመረጋጋት ዋነኛ መፍትሄው ሁሉም የፓለቲካ ሃይሎች በእኩልነት የሚሳተፉበት መንግስት በአስቸኳይ መመስረት ነው " የሚል የመፍትሄ ሀሳብ አቅርበዋል።  

ፓርቲዎቹ ፤ ሁሉም የፓለቲካ ሃይሎች በእኩልነት የሚሳተፉበት መንግስት በአስቸኳይ የመመስረት ጥሪ በተደጋጋሚ ማቅረባቸውና ግን ሰሚ አለማግኘታቸው  አመልክተዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF " በህወሓት (ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ) ስም ማንኛውም ፓለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ አይቻልም " - እነ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመሩት ጉባኤ ውሳኔ በአመራሮች መካከል ክፍፍል የፈጠረው የህወሓት ጉባኤ ባወጣው መግለጫ ፥ " የተለየ ሃሳብ አለኝ " የሚል በጉባኤ ያልተገኘ አካል ወደ ጉባኤው ቀርቦ ሃሳቡ በነፃነት እንዲገልፅ ፣ በዴሞክራሲያዊ ምጉት ለሚተላለፉት ውሳኔዎች ተገዢ እንዲሆን…
#Tigray🚨

" የጊዚያዊ አስተዳደሩን ስልጣን ለመንጠቅ የመሞከር እንቅስቃሴ ያደርጋሉ ብለን እንጠብቃለን " - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንትና የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ በክልሉ ወቅታዊ ሁኔታ ዛሬ ነሀሴ 11/2016 ዓ.ም መገለጫ ሰጥተዋል።

በጋዜጣዊ መግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ምንድናቸው ?

- የህወሓትና ሌሎች ህገ-ደንቦች ያላሟለና ተጨባጭ የትግራይ ሁኔታ ግምት ውስጥ ያላስገባ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ነው።

- የጉባኤው መነሻ የጥቂት የማእከላዊና ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ፍላጎት ነው።

- ትግራይ ወደ ከባድ አደጋ እንድትወድቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረገ ከፍተኛ አመራር ተመልሶ ስልጣን ላይ ለመውጣት ያደረገው እንቅስቃሴ ነው።

- ጉባኤው መላው የህወሓት አባላት የሚወክል አይደለም።

- ውጤት እንደሌለው ስለምናውቅ ወደ አላስፈላጊ መሳሳብ ላለመግባት በማሰብ ጉባኤ እንዳያካሂዱ አልከለከልንም።

- ማንነቱ ያልታወቀና ደጀን ይሆነናል የሚሉት ሃይል ተማምነው እያካሄዱት ያለው ጉባኤ ወደ አልተፈለገ ችግር ሊያስገባን የሚችል ነው።

- ድርጊታቸው የመንግስት ስራ መስራት የሚገባቸው አካላት ከስራ ውጪ የሚያደርግ ነው።

- የጊዚያው አስተዳደሩ ስልጣን ለመንጠቅ የመሞከር እንቅስቃሴ ያደርጋሉ ብለን እንጠብቃለን።

- የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች የስልጣን ፈላጊ አካላት መሳሪያ መሆን የለባቸውም።

- ህወሓት መዳን አለባት የምትድነው ግን በያዙት መንገድ አይደለም።

ትላንት የህወሓት ጉባኤ ቃለ-አቀባይ አቶ ኣማኑኤል ኣሰፋ መግለጫ ሰጥተው የነበረ ሲሆን ፤ ጉባኤው እንዲራዘም የሚጠይቅ ጥያቄ ቢነሳም በጉባኤተኞቹ ወድቅ መደረጉን ተናግረዋል።

ድርጅቱ " አጋጠሞኛል " የሚለው የስትራቴጂክ አመራር ውድቀት ለመፍታት አልሞ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ ነው " ቃለ-አቀባዩ ጨምረው የገለጹት።

ፎቶ፦ #TigraiTelevision

#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia