TIKVAH-ETHIOPIA
1.44M subscribers
55.9K photos
1.4K videos
202 files
3.77K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Humanity❤️

ይህ የሆነው በአሜሪካ ሀገር ሚኒሶታ ነው።

በሚኒሶታ በሚገኝ #ፈጣን_መንገድ ላይ አንድ አሽከርካሪ መንገድ ስቶ ወጥቶ ከመብራት ፖል ጋር ተጋጭቶ እዛው መኪና ውስጥ እያለ መኪናው በከፍተኛ እሳት መያያዝና መንደድ ይጀምራል።

በመንገዱ ሲጓዙ የነበሩ አሽከርካሪዎች ይህን አይተው አላለፉም።

መኪናቸውን አቁመው ከሚነደው መኪና ውስጥ አሽከርካሪውን ለማውጣትና ለማዳን ርብርብ ጀመሩ።

ከእሳት ነበልባል ጋር #እየታገሉ ፤ በሹፌሩ በር በኩል ያለውን መስታወት ሰብረው ከብዙ እልህ አስጨራሽ ትግል በኃላ አሽከርካሪውን በእሳት ተያይዞ ከሚነደው መኪና ውስጥ በህይወት አወጡት።

በኃላም ወደ ሆስፒታል እንዲወሰድ አደረጉ።

አሽከርካሪው ላይ ምንም አይነት የከፋ ጉዳት አልደረሰበትም ተብሏል።

ከከፍተኛ እሳት ጋር ተጋፍጠው የሰው ህይወት ለማትረፍ ርብርብ ሲያደርጉ ከነበሩት አንዱ ከድር ቶላ ይባላል። (ጥቁር ጁንስ ሱሪ በነጭ ጫማ ያደረገው)

ወደ ስራ እየሄደ በነበረበት ሰዓት ነው ይህ ክስተት ያጋጠመው።

ከድር የነፍስ አድን ስራውን ፥ " በህይወቴ እጅግ በጣም አስፈሪው ቅጽበት ነበር። ይህንን መቼም ቢሆን አልረሳውም ሁሌም ቢሆን አስታውሰዋለሁ " ሲል አስረድቷል።

አሽከርካሪው በህይወት እንዲተርፍ ቦታው ላይ የነበሩ ሁሉም ሰዎች ላደረጉት ፍጹም #ሰብዓዊ ተግባርና ርብርብ ፈጣሪን አመስግኗል።

የነበረውን የህይወት አድን ርብርብ የሚያሳይ ቪድዮ ከድር ቶላ መኪና ላይ በነበረ የዳሽቦርድ ካሜራ የተቀረጸ ነው።

Video Credit : Kadir Tolla / ከድር ቶላ

#TikvahFamily

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
በአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግ እስከ 500 ሺህ ብር ድረስ ገንዘብ መላክ መቻሉ ብዙዎች ለንግድ ቅልጥፍና ሞባይል አፓችንን ተመራጭ አድርገውታል።

ለአንድሮይድ ስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.boaMobileBanking&hl=en&gl=US

ለአፕል ስልኮች https://apps.apple.com/us/app/boamobile/id6463218765

ለሁዋዌ ስልኮች https://appgallery.huawei.com/app/C110106115
#BankofAbyssina #mobilebanking #boamobile #bankinginethiopia #banksinethiopia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
በነፃ ማውጋት፣ በቴሌብር ሱፐርአፕ ተችሏል!

በዘመነው ቴሌብር ሱፐርአፕ ከግብይት፣ ገንዘብ እና የአየር ሰዓት መላላክ ባሻገር ቪዲዮ፣ ድምጽ፣ ፎቶ፣ ጽሁፍ እና ፋይሎችን በነጻ በመጋራት ማህበራዊ ግንኙነትዎን ያጠናክሩ፤ ቢዝነስዎን ያቀላጥፉ!

በቴሌብር ኢንጌጅ፣ የዲጂታል ህይወትዎን ያቅልሉ!

መተግበሪያውን ለማዘመን ወይም ለመጫን http://onelink.to/fpgu4m ይጠቀሙ፡፡

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" 38 #ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ህይወታቸው አልፏል " - በጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በጅቡቲ የባህር ዳርቻ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ #የመን በመጓዝ ላይ በነበረች ጀልባ ላይ በደረሰ የመስጠም አደጋ 38 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ህይወታቸውን እንዳጡ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቋል። ትላንትና ሰኞ በጅቡቲ ሰሜን ምስራቅ " #ጎዶሪያ " በሚባል የባህር ዳርቻ አቅራቢያ ስልሳ (60) ኢትዮጵያውያን…
" የ5 ሕፃናት እና ሴቶችን ሕይወት ጨምሮ 16 ዜጎቻችን ሕይወታቸውን አጥተዋል " - በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ

በጀልባ መገልበጥ አደጋ #የ16_ኢትዮጵያውያን ሕይወት ሲጠፋ አብረው የተሳፈሩ 28 ዜጎችን እስካሁን ማግኘት አልተቻለም።

ትላንት ምሽቱን ከየመን የባህር ዳርቻ ልዩ ስሙ " አራ " ከሚባል ስፍራ 77 ኢትዮጵያውያን ሕገ ወጥ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ ጅቡቲ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ " ጎዶሪያ " በሚባል አካባቢ በደረሰባት የመገልበጥ አደጋ እስካሁን ድረስ የ5 ሕፃናት እና ሴቶችን ሕይወት ጨምሮ 16 ዜጎቻችን ሕይወታቸውን አጥተዋል።

እስካሁን አብረው ተሳፍረው የነበሩት ውስጥ 28 ፍልሰተኞችን ማግኘት እንዳልተቻለ እና 1 ሴትን ጨምሮ 33 ፍልሰተኞች በሕይወት ተርፈው ድጋፍ እየተደረገላቸው ነው።

ከ2 ሳምንት በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ በደረሰ አደጋ የ38 ፍልሰተኛ ዜጎች ሕይወት አልፎ ነበር።

ከጅቡቲ ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት የሚደረገው ህገ ወጥ ጉዞ እጅግ አደገኛ ከመሆኑም በላይ በየጊዜው የዜጎችን ሕይወት እያሳጣ እንደሆነ በጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ገልጿል።

በዚህም ዜጎች ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ለከፋ አደጋ እየዳረጉ ይገኛሉ ብሏል።

ዜጎች #በህገወጥ_ደላሎች የሀሰት ስብከት በመታለል ውድ ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው በዚህ አደገኛ የጉዞ መስመር ከመንቀሳቀስ እንዲቆጠቡ እና የፍትህ አካላትም ሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን ከገጠራማ የአገራችን አካባቢዎች ዜጎቻችን በመመልመል ለስደት በሚዳርጓቸው ግለሰቦች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
" ሙሉ በሙሉ ከእውነት የራቀ ነው " - ህወሓት

ዛሬ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከብልጽግና ፓርቲ ጋር ለመቀላቀል ተከታታይ ድርድር እያደረገ ነው " የሚሉ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።

ህወሓት ግን " ይህ ሙሉ በሙሉ ከእውነት የራቀ ነው " ብሏል።

ህወሓት ፥ " ከብልጽግና ጋር በተከታያይ እየተካሄደ ያለው ውይይት ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ የተፈጠረውን ሰላም ለማስፋት እና ለማጠናከር ያለመ ነው " ሲል ገልጿል።

ከብልጽግና ፓርቲ ጋር #መሰረታዊ የሆነ የዓላማ እና የአስተሳሰብ ልዩነት እንዳለው የገለጸው ህወሓት ፤ " ልዩነቱ እንዳለ ሆኖ ሁለቱ ፓርቲዎች ሊወያዩባቸው የሚገቡ ብዙ አጀንዳዎች አሉ " ብሏል።

" ህወሓት ከብልጽግና ጋር ሊቀላቀል / ሊዋሃድ ንግግሮች ተጀምረዋል " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ሙሉ በሙሉ ከእውነት የራቀ ነው ሲል አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኮሬ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፤ በኮሬ ዞን በተፈጸመ ጥቃት 3 ታዳጊ ልጆችን ጨምሮ 4 ሰዎች ተገደሉ። ጥቃቱ የተፈጸመው ትላንት በጎርካ ወረዳ ፤ " ቆቦ ቀበሌ " ነው ተብሏል። የኮሬ ዞን አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ ለንጹሐን አርሶ አደሮች ሞት ምክንያት ለሆነው ጥቃት " በምዕራብ ጉጂ ዞን ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ እና ፀረ-ሰላም " ሲል የጠራቸውን አካላት ተጠያቂ አድርጓል። እንደ አካባቢው…
“ ባለፈው ሳምንት ብቻ 7 ሰዎች ናቸው የተገደሉት ” - ነዋሪዎች

በኮሬ ዞን ፤ #በታጣቂዎች አማካኝነት ንጹሃን ላይ የሚደርስ ጥቃት በእርቀ ሰላም ተፈቶ ቆሞ የነበረ ቢሆንም ከ4 ወራት ወዲህ በማገርሸቱ የንጹሐን ግድያ፣ የንብረት ዘረፋ እየተፈጸመ መሆኑን የዞኑ ባለስልጣትና ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

መንግሥት መፍትሄ እንዲሰጥም ተጠይቋል።

ባለስልጣናቱና ነዋሪዎቹ ለድርጊቱ  የ " ኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች " ን ተጠያቂ አድርገዋል።

የዞኑ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ተፈራ ቦንደሮ ምን አሉ ?

➡️ “ ከምዕራብ ጉጂ ዞን ጋላና ወረዳ የታጠቁ ኃይሎች በቀጠናው ላይ ገብተው 4 ሰዎችን በአንድ ቀን ገድለዋል። ”

➡️ “ የመንግሥት መዋቅር እዛ አካባቢ ላይ Functional ስላልሆነ ኦነግ ሸኔ በነጻነት ተንቀሳቅሰው በቀጠናው ላይ ጥቃት ይፈጽማሉ። ”

➡️ “ እርቅ ተፈጽሞ ከኀዳር 1 ቀን 2015 ዓ/ም ወዲህ ከጉጂ ዞን ጋ መልካም ግንኙነት ተፈጥሮ እንደነበር፣ ይሁን እንጂ ከ4 ወራት ወዲህ ታጣቂዎቹ እንደገና ጥቃት እያደረሱ ነው። ”

ቃላቸውን የሰጡን የቆቦ ቀበሌ ነዋሪ ምን አሉ ?

👉 “ ባለፈው ሳምንት ብቻ 7 ሰዎች ተገድለዋል። 4ቱ የቆቦ ቀበሌ ነዋሪዎች እሁድ ሚያዚያ 13 ቀን 2016 ዓ/ም ከብት በሚጠብቁበት ነው የተገደሉት። "

👉 “ከዚያ በፊት ዳኖ ቀበሌ 2 ሰዎች ተገድለዋል። ሌላም የሞተ አለ። ”

👉 “ ታጣቂዎቹ #ከ2009 ዓ/ም ጀምሮ ጥቃት ያደርሱ ነበር በዚህም ከ100 በላይ ሰዎች ተገድለዋል። ”

👉 “ በ2015 ዓ/ም እርቅ ተፈጽሞ ጥቃቱ ቆሞ ነበር። ከወራት ወዲህ ጥቃቱ አገርሽቶ በርካታ ሰዎች ተገድለዋል። ”

👉 “ በቆቦ ቀበሌ እርቁ ከተፈጸመ ወዲህ ብቻ 10 ሰዎች ተገድለዋል። ”

ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የኮሬ ዞን ኮሚዩኒኬሽን አካል ምን አሉ ?

▪️ “ በቀን 08/08/2016 የሁለት አርሶ አደሮች ሕይወትም አልፏል። እስከ ሚያዚያ 8/2016 ብቻ 19 ንጹሐን ከህዳር 1/2015 ዕርቅ በኋላ ተገድለዋል። ”

▪️ “ ከ19ኙ ሟቾች በተጨማሪ እሁድ ሚያዚያ 13 በቆቦ ቀበሌ፦
- ተመን እንግዳ ሶልዳንቶ
- ይርጋ ሚትኩ ሶልዳንቶ 
- ነብዩ ቡና
- አባይ ፍቅሬ የተባሉ ሰዎች ተገድለዋል። ”

▪️ “ ንጹሐንን የገደሉ ለሕግ ይቅረቡ። ”

ጉዳዩን በተመለከተ ምላሽ ለማግኘት ወደ ኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ተደጋጋሚ ሙከራ ቢደረግም ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ለጊዜው ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #ሀዋሳ #ክልከላ

በሀዋሳ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰአት በኋላ ባለ ሦሰት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) እና የሁለት እግር ሞተር ሳይክል ማሽከርከር #ተከለከለ

ሰሞኑን በሀዋሳ ከመዝናኛ መልስ እየደረሰ ያለውን የመንገድ ላይ የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ሲባል ከምሽቱ 3:00 በኃላ ባለሦሰት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) እና ባለ ሁለት እግር ሞተር ሳይክል ማሽከርከር የተከለከለ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ ትራፊክ ፖሊስ አስተባባሪው ኢንስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አሳውቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፦
°  ምክንያት ?
°  ክልከላው ለምን አስፈለገ ?
° በማህበረሰቡ የእለት ተእለት ህይወትስ ላይ የሚያሳድረዉ ጫና አይኖርም ? ወይ ስንል ኢንስፔክተሩን ጠይቋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ኢንስፔክተር ተስፋዬ ፤ " ሁሉንም ያደረግነው ለማህበረሰቡ ደህንነት ነው " ብለዋል።

" አሁን ላይ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ የትራፊክ አደጋ እየተስተዋለ ነው " ሲሉ ገልጸው ከአደጋዎቹ አብዛኛዉ በባለሦሰት እግር ባጃጅና በባለሁለት እግር ሞተር ሳይክል የሚደርስ እንደሆነ አስረድተዋል።

" በዚህ አመት ብቻ በምሽት በሞተር ሳይክል የደረሰዉ አደጋ የሚያስገርም ቁጥር ያለው ነው " ያሉት ኢስፓክተር ተስፋዬ በቁጥር ስንት ? የሚለውን ወደፊት ዳታውን አጠናቅረዉ ለማህበረሰቡ የማሳየት እቅድ እንዳለቸዉ ጠቁመዋል።

ከአደጋዎቹ ውስጥ በአብዛኛው የሚከሰቱት በምሽት መሆኑን ጠቅሰው ፤ " ጠጥቶ ሞተር ሳይክል ማሽከርከር  ትልቁ ምክኒያት ሆኖ ተገኝቷል። በተለይም በመንግስት ሞተር ሳይክሎች ሳይቀር ሶስትና ከዚያ በላይ ሆኖ መንቀሳቀስ አደጋ እየፈጠረ ነው ይህን ችግር ለመቀነስ ሲባል #ክልከላው ወጥቷል " ሲሉ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ፤ " የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ከፍተኛ የወንጀል መፈጸሚያ እየሆኑ ነው " ያሉት ኢንስፔክተሩ ፤ " ለአብነት ኮንትራት ተብለዉ በሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ላይ የሚደርሰው አደጋ እና የሌሎችም ወንጀሎች ምንጭ ሆነው ተገኝተዋል " ብለዋል።

" ጥንቃቄ ለራስ በመሆኑ ማህበረሰቡ ለራሱ ሲባል የወጣዉን ክልከላ አክብሮ እንዲንቀሳቀስ " ሲሉ አሳስበዋል።

" እለት ተእለት የሚከሰተው ዘግናኝ የትራፊክ አደጋ እንዲቆም የሁላችንም ትብብር ያስፈልጋል " ብለዋል።

ክልከላው የሚያበቃበትን ጊዜን በተመለከተ ምንም የተባለ ነገር የለም።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
" ሕግ ፊት እናቀርበዋለን " - ፌዴራል ፖሊስ

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ፤ በሃይማኖታዊ ስፍራ ላይ ጥይት ወደ ላይ ሲተኩስ የነበረው አባሉ በቁጥጥር ስር እንደሚኝ ገልጿል።

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ አንድ የፌዴራል ፖሊስ ልብስ የለበሰ ግለሰብ በቤተክርስቲያን ውስጥ እየተዘመረ በነበረበት ሰዓት ወደ መድረክ ወጥቶ በተደጋጋሚ ሲተኩስ የሚያሳይ ቪድዮ ተሰራጭቷል።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አባሉ ምክትል ሳጂን ታመነ ዱባለ እንደሚባል ገልጿል።

ክስተቱ የተፈጸመው ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ አዲስ የፖሊስ አባላትን ለመመልመል ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በተላከበት ወቅት መሆኑን አመልክቷል።

" ጥር 5/2016 ዓ.ም ኬቾ ወዜ ቅዱስ ባለወልድ ቤተክርስቲያን በመገኘት ነው የደንብ ልብሱን እንደለበሰ ሃይማኖታዊ መዝሙር በመዘመር እና በሕዝብ ፊት ጥይት እየተኮሰ የነበረው " ያለው ፖሊስ ይህ ከተቋሙ መተዳደሪያ ህግና አሠራር ውጭ ነው ብሏል።

የፖሊስ አባሉ ይህን ተግባር እንደፈፀመ ወዲያውኑ በቁጥጥር ሥር ውሎ የፈፀመው ድርጊትም በተቋሙ #ሕገ_ደንብ መሠረት በሕግ አግባብ እያጣራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አመልክቷል።

ፖሊስ የሁሉም አገልጋይ ሆኖ ሳላ አባሉ እምነቱን በግል መከተል እየቻለ ነገር ግን መንግስት ፀጥታ እንዲያስከብር ያስታጠቀውን የጦር መሣሪያ ከፍተኛ ሕዝብ በተሰበሰበበት ቦታ ፍፁም የፖሊስን ዲሲፕሊን በጣሰ መልኩ የፈፀመው ተግባር በሕግ የሚያስጠይቅ ስለሆነ ተቋሙ ሕግ ፊት ያቀርበዋል ሲል አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የአሜሪካ #ሴኔት በመላው አሜሪካ " ቲክቶክ" ን ሊያግድ የሚችል አዋጅ ትላንት ለሊት አጽድቋል።

ከቀናት በፊት የተወካዮች ምክር ቤት " ቲክቶክ " እንዲታገድ ረቂቅ ሕግ ማጽደቁ ይታወሳል።

ትላንት ለሊት የአሜሪካ ሴኔት ተሰብስቦ " ቲክቶክ " ከቻይና ካልተፋትና ድርሻው በ9 ወር ውስጥ ለአሜሪካ ኩባንያ የማይሸጥ ከሆነ አሜሪካ ውስጥ አገልግሎት እንዳይሰጥ የሚያግድ አዋጅ አጽድቋል።

ቀጣዩ ሂደት ፕሬዜዳንቱን ይመለከታል።

ይህ አዋጅ ወደ ፕሬዝዳንት ጆ  ባይደን የተመራ ሲሆን እሳቸው ቀደም ሲል " ይህ አዋጅ እኔ ጋር ይድረስ እንጂ ፊርማዬን አኑሬበት ሕግ ሆኖ ይተገበራል " ብለው ነበር።

አሁን በአሜሪካ 170 ሚሊዮን ተጠቃሚዎች ያሉት " ቲክቶክ " የመታገዱ ነገር እውን እየሆነ የመጣ ሲሆን ሂደቱ ረጅም ወራትን ሊወስድ ይችላል።

በሌላ በኩል ፥ ሴኔቱ ለዩክሬን ፣ ለእስራኤል እና ለሌሎች የባህር ማዶ የአሜሪካ አጋሮች የ95 ቢሊዮን ዶላር (5,419,427,000,000 ብር) የእርዳታ ጥቅልን አፅድቆታል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ከየመን የባህር ዳርቻ ልዩ ስሙ " #አራ " ከሚባል ስፍራ 77 #ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ ጅቡቲ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ መገልበጧ መገለጹ ይታወሳል።

በዚህም አደጋ የ5 ዓመት #ሕጻናት እና #ሴቶችን ጨምሮ 16 ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ መገለጹ አይዘነጋም።

የIOM የጅቡቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ታንጃ ፓሲፊክ ፤ የሟቾች ቁጥር ቀደም ሲል ከሰጠው መረጃ ማለትም 16 ከፍ ማለቱንና 21 መድረሱን ተናግረዋል።

የሞቱት ሁሉም #ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ገልጸዋል።

23 ሰዎች አሁንም ድረስ የት እንደገቡ እንኳን አይታወቅም ብለዋል።

33 ሰዎች ከአደጋው እንደተረፉ ገልጸዋል።

ይህ አደጋ #38_ኢትዮጵያውን ከሞቱበት አደጋ ከሁለት ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የተከሰተ ነው።

በርካታ ሰዎች በተለይም ወጣቶች ህይወታቸውን ለመቀረ ሲሉ በአደገኛው እና ህገወጥ በሆነው መንገድ ሀገራቸውን ጥለው ይሰደዳሉ ፤ በዚህም ህይወታቸውን ባህር ላይ ያጣሉ ፣ ይታሰራሉ፣ በየበረሃው ይንገላታሉ ፣ በደላሎች ታግተው ይሰቃያሉ ።

ሀገር ጥለው በህወጥ መንገድ የሚሰደዱ ሰዎች ቁጥር ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አይታይም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ፖሊስ ተጨማሪ 8 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ተፈቀደለት።

ቀሲስ በላይ መኮንን በሃሰተኛ ሰነድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማዘዋወር ሲሞክሩ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ይታወሳል።

በተጠረጠሩበት ወንጀል ዛሬ ለ2ኛ ጊዜ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።

ከእሳቸው ጋር ሌሎች 2 ግለሰቦች ያሬድ ፍስሃ እና ጣባ ገናና የተባሉ ቀርበዋል።

ከዚህ ቀደም ለፌዴራል መርማሪ ፖሊስ 7 ቀን መሰጠቱ ይታወሳል።

በዚህ ጊዜ መርማሪ ፖሊስ ምን እንደሰራ ለችሎቱ አስረድቷል።

ፖሊስ ምን አለ ?

- " የምስክሮችን ቃል ተቀብያለሁ። "
- " በተጠርጣሪዎች እጅ ላይ የተገኘ ኤሌክትሮኒክስ ምርመራ እንዲደረግ ለሚመለከተው ተቋም ጠይቂያለሁ። "
- " የቴክኒክ ምርመራ እንዲሰጠኝ በደብዳቤ ጠይቂያለሁ። "
- " ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ለአፍሪካ ህብረት የሰነድ ማስረጃዎች እንዲሰጠኝ ጠይቂያለሁ። "
- " ተጠርጣሪዎቹ በስማቸው የሚገኙ ሂሳቦችን ለማጣራት ማረጋገጫ እንዲሰጠኝ በደብዳቤ ጠይቂያለሁ። "
- " በወቅቱ የነበረ የካሜራ ቅጂ ጠይቂያለሁ። "
- " ለወንጀል ተግባር የዋለ ተሽከርካሪ ማረጋገጫ ከሚመለከተው ተቋም ጠይቂየለሁ። "
- " በቀሲስ በላይ ሁለት መኖሪያ ቤቶች ላይ ብርበራ አድርጌ በብርበራ የተገኘ የጦር መሳሪያ ህጋዊነት የማረጋገጥ ስራ እየሰራሁ ነው። " ... ብሏል።

የቀሩ ስራዎች ፦
- " ከተለያዩ ተቋማት የሰነድ ማስረጃ መሰብሰብ። "
- " ተጨማሪ ምስክሮችን ቃል መቀበል። "
- " ግብረአበሮችን ተከታትሎ መያዝ። "
- " ተጨማሪ ሀብት የማፍራት ተግባሮች ላይ የማጣራት ስራ መስራት ሌላም ሰፊ የምርመራ ስራ ስለሚያስፈልግ ተጨማሪ የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ይሰጠኝ " ብሏል።

የተፈጸመው ድርጊት " ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያለንን መልካም ግንኙነት ጥላሸት የሚቀባ ተግባር ነው " ብሏል።

ተጠርጣሪው ቀሲስ በላይ መኮንንን ጨምሮ ሌሎቹም ተጠርጣሪዎች በ6 ጠበቆች ተወክለው ነው የቀረቡት።

ጠበቆቻቸው ምን አሉ ?

° " የቀረበው የጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያ ምክንያቶች ደንበኞቻችን ተጨማሪ በእስር ለማቆየት የሚያስችል አይደለም " ብለዋል።

° " ቀሲስ በላይ የተገኘው የጦር መሳሪያ ህጋዊ ነው። ሀብት ማፍራት ከተጠረጠሩበት ወንጀል ጋር ሊገናኝ አይገባም " ብለዋል።

° " የሃይማኖት አባት መሆናቸው ፣ የልማት ስራ አስተባባሪ በመሆናቸው ፣ ቋሚ አድራሻ ያላቸው በመሆኑ ቢወጡ ከመንግስት ተቋማት የሚመጡ ማስረጃዎችን የማጥፋት አቅም የላቸውም " ብለዋል።

ስለሆነም የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

ቀሲስ በላይ መኮንን ምን አሉ ?

ወንጀል አለመፈጸማቸውን ገልጸዋል።

ለሀገር እንዲሁም ፖሊስ ተባባሪ መሆናቸውን ተናግረዋል።

➡️ " ምሽት ላይ #እቤቴ_እየሄድኩ ጠዋት ላይ ልምጣላችሁ " በማለት ፖሊስን መጠየቃቸውን ለችሎቱ አስረድተዋል።

ከእሳቸው ጋር አብረው የታሰሩት #ሹፌራቸው እና #አጃቢያቸው እንደሆኑ ገልጸው ምንም የወንጀል ተሳትፎ በሌለበት ሁኔታ ከኔ ጋር ተጨማሪ ጊዜ በእስር ማቆየት ተገቢ አይደለም በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ቢወጡ ማስረጃ ሊሰወር ይችላል በማለት የዋስትና ጥያቄያቸውን ተቃውሟል።

የግራ ቀኝ ክርክሩን የተመለከተው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪው ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ለጊዜው በማለፍ ለፖሊስ የ8 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ ፥ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት (#ኤፍቢሲ) መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia