TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
🏷የ12ኛ ክፍል የፈተና #ዉጤት አስመልክቶ በተለያዩ ማህበረዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ መረጃዎች #ሀሰት መሆናቸውን የፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ እንዳስታወቀዉ የ12ኛ ክፍል ዉጤት #በቅርቡ ይለቃቃል የሚለዉ መረጃ መሰረተ ቢስ ነዉ ብሏል። የኤጀንሲዉ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ረዲ ሺፋ ለኢትዮኤፍኤም እንዳረጋገጡት ኤጀንሲዉ የፈተናዎቹ ዉጤት ይፋ የሚሆንበትን ቀን አልወሰነም ብለዋል፡፡

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ዉጤቱ ተለቋል በዚህ ቀን ይለቀቃልና ሌሎች መሰል መረጃዎች ሀሰት እንደሆኑ አቶ ረዲ ተናግረዋል፡፡ ተማሪዎቹም ሆነ ህብረተሰቡ ከተሳሳተ መረጃ እራሱን እንዲጠብቅ ሃላፊዉ ጠይቀዋል፡፡ በቀጣይ ኤጀንሲዉ የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል የፈተና ዉጤት ይፋ የሚሆንበትን ቀን ለመገናኛ ብዙሃን በይፋ ያሳውቃል ብለዋል፡፡

Via #ኢትዮኤፍኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሀሰት_ነው !

" ከሱዳን ጋር #በቅርቡ በድንበር ጉዳይ የተደረሰ ስምምነት የለም " - በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ

ሰሞኑን አንዳንድ ሚዲያዎች በሱዳን የሚገኙትን የኢትዮጵያ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በመጥቀስ የኢትዮጵያንና የሱዳንን ድንበር በተመለከተ ስምምነት እንደተደረሰ ሲዘግቡ ተስተውሏል።

በተለይ Alsharq AL-awsat English ጋዜጣ በድህረ ገፁ “Addis Ababa, Khartoum Reach Deal on Border Dispute” በሚል ርዕስ እ.ኤ.አ ፌብርዋሪ 13 ቀን 2022 ያስነበበው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ ጋዜጣው የመረጃውን ምንጭ ሳይጠቅስ ያቀረበው ሲሆን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ከዚህ ጋዜጣ ጋር ግንኙነት እንዳላደረጉ እና መረጃ እንዳልሰጡ ኤምባሲው ገልጿል።

@tikvahethiopia
#ሀገራዊ_ምክክር 🇪🇹

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰብሳቢ ፕ/ር መስፍን አርአያ ለኤፍ ቢ ሲ በሰጡት ቃል የተናገሩት ፦

" በሀገራዊ ምክክሩ #ሁሉም ኢትዮጵያዊ አጀንዳ የሚያስይዝበት አሰራር ይዘረጋል።

የውይይት ሃሳቦች ከታች ወደ ላይ ነው የሚሰበሰቡት።

በውይይቱ ይህ ይነሳ ያ አይነሳ የሚባል ነገር የለም ። ኮሚሽኑ በአጀንዳዎች ላይ ጣልቃ አይገባም።

ምክክሩ ልሂቁ ላይ ብቻ የተንጠለጠለ ባለመሆኑ ሁሉም ዜጋ ሐሳቡ በጥቂቶች እንዳይጨናገፍ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ እናቀርባለን።

በቀጣይ በየክልሉ እንደ አመቺነቱ ጽሕፈት ቤቶች ይቋቋማሉ ፤ የኮሚሽኑ ምክር ቤት መርሃ ግብር ያዘጋጀ ሲሆን ስትራቴጂክ ዕቅዱን ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ ግብዓት ይሰበሰባል።

አጀንዳ የመሰብሰብ ሥራ በገጽ ለገጽ ማህበረሰቡ በሚረዳው ቋንቋ ስለ ኮሚሽኑ በማስረዳት ሃሳቡን እንዲገልጽ ይደረጋል። በሌሎች አማራጮችም በስልክ፣ ኢሜይል እና ፖስታ በመሳሰሉት ማቅረብም ይቻላል።

ማሕበረሰቡ ሃሳቡን ከማቅረብ በተጨማሪ በማዕከል ደረጃ ለሚደረገው ምክክር ወኪሎቹን እንዲመርጥ ይደረጋል።

የአጀንዳ ሃሳቦች መሰብሰብ የሚጀመርበት ጊዜ #በቅርቡ_ይፋ ይደረጋል። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥያቄ #የጋራመኖሪያ_ቤቶች ብዙ ሲባልለት የነበረው የ20/80 እና የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ከብዙ መናጋገሪያ ጉዳዮች በኃላ ሙሉ በሙሉ መሰረዙ ይታወሳል። በቀጣይ ዕጣው መቼ ይወጣል ? የሚለው ለጊዜው ባይታወቅም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ " ከገጠመን ችግር ተነስተን ተገቢውን ሁሉ ጥንቃቄ በማድረግ በፍጥነት ዳግም እጣ በማውጣት በፍትሀዊነት ተደራሽ ለማድረግ እንሰራለን "…
" ለጥያቄቻችን መልስ እንፈልጋለን " - የ2005 የ20/80 ባለ3 መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች

ጥያቄ አለን ያሉን ከ2005 ጀምሮ ለ9 ዓመት እየቆጠቡ ያሉ የባለ 3 መኝታ ቤት (20/80) ተመዝጋቢዎች የአዲስ አበባ አስተዳደር እነሱን በተመለከተ ግልፅ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው እንዲሁም በቀጣይ እጣ ላይ እንዲካተቱ እየጠየቁ ይገኛሉ።

እነዚሁ ጥያቄ አለን ያሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በቴሌግራም ግሩፕ በመሰበሰብ መፍትሄ ለመፈለግ ካለፉት ሳምንታት ጀምሮ እየተነጋገሩ ይገኛሉ።

በ2005 የባለ ሶስት መኝታ ቤት ተመዝጋቢዎች አለን ያሉትን ጥያቄ አሳውቀናችሁ ነበር። አሁንም ለጥያቄቸው መልስ ባለማግኝታቸው ጥያቄያቸውን ማቅረባቸውን ቀጥለዋል።

ተመዝጋቢዎቹ ፤ " በ20/80 በባለ 3 መኝታ ተመዝግበን መንግስት ቃሉን አክብሮ የቤት ባለቤት እንደሚያደርገን ተማምነን " ነበር ሲሉ ገልፀዋል።

" ከልጆቻችን ዳቦ ቀንሰን ተጎሳቁለን በቤት ክራይ እየተንገበገብን ላለፉት 9 አመታት በተስፋ ተሞልተን ቁጠባችንን ሳናቋርጥ በመቆጠብ ላይ እንገኛለን " ም ብለዋል።

ነገር ግን በ13ኛው ዙር ተጀምሮ በ14ኛው ዙር ላይ በዕጣው አለመካተታቸው ከፍተኛ ቅሬታ እንዳሳደረባቸው እና እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል።

ላለፉት 9 ዓመታ እየቆጠቡ የሚገኙት ወገኖች በ13ኛው ዙር የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ወቅት በብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በ1997 ለባለ3 መኝታ የተመዘገበ የለም ሁሉም በ2005 የተመዘገቡ ስለሆነ ወደእነሱ ይተላለፋል ተብሎ ነበር ነገር ግን በ14ኛው ዙር አለመካከተቱ ግልፅ ማብራሪያ የሚያስፈልገው መሆኑን ገልፀዋል።

ምንም እንኳን ትክክለኛ ቀኑንም ሆነ ሳምንቱ ባይታወቅም #በቅርቡ የተሰረዘው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ በሌላ ሶፍትዌር ይወጣል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update • ዓዲ አርቃይ እና አካባቢው ኔትዎርክ ጀምሯል ፤ አላማጣና ኮረም በሰዓታት ውስጥ አገልግሎት ያገኛሉ። ዓዲ አርቃይ እና አካባቢው የኔትዎርክ አገልግሎት ጀመረ። የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ፤ የኔትዎርክ አገልግሎት ተቋርጦባቸው የነበሩት ዓዲ አርቃይ እና አካባቢው ዳግም የኔትዎርክ አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን ዛሬ ገልፀዋል። የጄኔሬተር ነዳጅ ወደ አካባቢው በመላክ…
በየትኞቹ አካባቢዎች የቴሌኮም አገልግሎት ጀመረ ?

ኢትዮ ቴሌኮም ፤ የቴሌኮም አገልግሎት ተቋርጦባቸው የነበሩና ዳግም ያስጀመረባቸውን አካባቢዎችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

የቴሌኮም አገልግሎት የጀመረባቸው አካባቢዎች ፦

- አላማጣ፣
- ኮረም፣
- ዓዲ አርቃይ፣
- ጸለምት፣
- ጪሮ ለና፣
- ጎብዬ ቆቦ፣
- ቆቦ ሮቢጥ፣
- ዞብል
- ዋጃ ናቸው።

#በሌሎችም የቴሌኮም አገልግሎት በተቋረጠባቸው አካባቢዎች #በቅርቡ አገልግሎት ለማስጀመር እየሠራ እንደሚገኝ ኢትዮ ቴሌኮም አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በየትኞቹ አካባቢዎች የቴሌኮም አገልግሎት ጀመረ ? ኢትዮ ቴሌኮም ፤ የቴሌኮም አገልግሎት ተቋርጦባቸው የነበሩና ዳግም ያስጀመረባቸውን አካባቢዎችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል። የቴሌኮም አገልግሎት የጀመረባቸው አካባቢዎች ፦ - አላማጣ፣ - ኮረም፣ - ዓዲ አርቃይ፣ - ጸለምት፣ - ጪሮ ለና፣ - ጎብዬ ቆቦ፣ - ቆቦ ሮቢጥ፣ - ዞብል - ዋጃ ናቸው። #በሌሎችም የቴሌኮም አገልግሎት በተቋረጠባቸው…
#Tigray #EthioTelecom

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ፦

" ሽረ የሚገኘውን ኮር ሳይት አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ የሚያስችል ቅኝት ተደርጓል። ሳይቱ ለሁለት ዓመት አግልግሎት ሳይሰጥ እንደመቆየቱ የጎደሉ እቃዎችን ማሟላትን ጨምሮ ሌሎች ስራዎች ሲሰሩ ቆይቷል።

በርብርብ በተከናወነ ስራ 266 ኪሎ ሜትር የፋይበር ጥገና ማከናወን ተችሏል። ጥገናውን ለማጠናቀቅ 6 ኪሎ ሜትር ይቀረናል።

የጥገና ስራው ሲጠናቀቅ ከአስቸኳይ (Emergency) የቴሌኮም አገልግሎት በዘለለ ሰፊው ማህበረሰብ አገልግሎት እንዲያገኝ ያስችላል።

ከሽረ ቀጥሎ አክሱም እና አድዋም አገልግሎት እንዲያገኙ የማስተላለፊያ መስመር ፍተሻ ጀምረናል። #በቅርቡ በርካታ ከተሞች (ትግራይ ክልል ውስጥ) የቴሌኮም አገልግሎት ያገኛሉ። "

Credit : ኤፍ ቢ ሲ

@tikvahethiopia
ከ / ወደ ትግራይ  የየብስ ትራንስፖርት መቼ ይጀምራል ?

ከትግራይ ክልል ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች #በቅርቡ የየብስ ትራንስፖርት እንደሚጀምር ከሰሞኑን ተገልጿል።

ከአየር ትራንስፖርት በተጨማሪ የየብስ ትራንስፖርት በቅርብ ቀን ለማስጀመር ከፌዴራል መንግስት ጋር በመነጋገር ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን የክልል የኮንድትራክሽንና መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል።

ከሰላም ስምምነቱ በኃላ በህጋዊ መንገድ የህዝብ የየብስ ትራንስፖርት እንዳልተጀመረ የገለፀው ቢሮው ሸቀጦች፣ ሰብዓዊ እርዳታ እየገባ ስለመሆኑ አመልክቷል።

ወደ ትግራይ ክልል ለሁለት ዓመት ትራንስፖርት ተዘግቶ ስለቆየ አሁን ላይ ያለው የአየር ትራንስፖርት በገንዘብ ውድም ስለሆነ ብቻውን የህዝቡን ችግር አይፈታም ያለው ቢሮው የኢኮኖሚ ውስንነት ያለበት፣ ህዝቡም በብዛት መንቀሳቀስ እንዲችል የመንገድ ትራንስፖርት ማስጀመር አስፈላጊ ስለሆነ በኛ በኩል አስፈላጊ ዝግጅት እያደረግን ነው ብሏል ለክልሉ ቴሌቪዥን በሰጠው ቃል።

በቅርብ ለሚጀመረው ለየብስ ትራንስፖርት ሀገር አቋራጭ ተሽከርካሪዎች በማህበራቸው በኩል አስፈላጊ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል።

ከ/ወደ ትግራይ የየብስ ትራንስፖርት በቅርብ የጀመራል ይባል እንጂ ቁርጥ ያለው ትክክለኛ ቀን አልታወቀም።

የአየር ትራንስፖርት ውድ በመሆኑና ወረፋውም እጅግ ከፍተኛ ስለሆነ በትግራይ ክልል ነዋሪ የሆኑ እጅግ በርካታ ዜጎች ለተለያዩ የማህበራዊ ጉዳዮቻቸው፣ ለስራ እንቅስቃሴ የየብስ ትራንስፖርት እስኪጀመር እየተጠባበቁ ይገኛሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከ / ወደ ትግራይ  የየብስ ትራንስፖርት መቼ ይጀምራል ? ከትግራይ ክልል ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች #በቅርቡ የየብስ ትራንስፖርት እንደሚጀምር ከሰሞኑን ተገልጿል። ከአየር ትራንስፖርት በተጨማሪ የየብስ ትራንስፖርት በቅርብ ቀን ለማስጀመር ከፌዴራል መንግስት ጋር በመነጋገር ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን የክልል የኮንድትራክሽንና መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል። ከሰላም ስምምነቱ በኃላ በህጋዊ…
#Update

ከ/ወደ ትግራይ የየብስ ትራንስፖርት ለመጀመር የአገር አቋራጭ የሕዝብ ትራንስፖርት ማመላለሻ ማህበራት ዝግጁ እንዲሆኑ መመሪያ መተላለፉ ተሰምቷል።

ሪፖርተር ጋዜጣ ከአገር አቋራጭ የሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት ማኅበራት ያገኘሁት ባለው መረጀ ፤ የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ወደ ትግራይ የተለያዩ ከተሞች የሕዝብ ማመላለሻ የትራንስፖርት አገልግሎትን ዳግም ለመጀመር ዝግጁ ሆነው እንዲጠብቁ መመርያ ተላልፎላቸዋል፡፡

በዚሁ የሚኒስቴሩ መመርያ መሠረት ማኅበራቱ ለአባሎቻቸው አገልግሎቱን መልሶ ለማስቀጠል ዝግጁ እንዲሆኑ ያሳወቁ ሲሆን አሁን እየጠበቁ ያሉትም የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱን የመጨረሻ ውሳኔ እንደሆነ ለማወቅ መቻሉን #ሪፖርተር_ጋዜጣ ዘግቧል።

ከጥቂት ቀናት በፊት የትግራይ ክልል የኮንስትራክሽንና መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ  ከትግራይ ክልል ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች #በቅርቡ የየብስ ትራንስፖርት እንደሚጀምር ማሳወቁ አይዘነጋም።

ቢሮው ከአየር ትራንስፖርት በተጨማሪ የየብስ ትራንስፖርት በቅርብ ቀን ለማስጀመር ከፌዴራል መንግስት ጋር በመነጋገር ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#EOTC

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፤ የ " ቤተክርስቲያን ችግሮች እና ዘለቄታዊ መፍትሔ ጥናትና ትግበራ ኮሚቴ " በሚል ስያሜ እንደተቋቋመ የገለፀችውና ከሁሉም የሞያ ዘርፎች የተውጣጡ የቤተክርስቲያኗን ልጆች ያቀፈው ቡድን ወደ ትግበራ ሊገባ መሆኑን አስታወቀች።

ኮሚቴው የጥናታዊ ጽሑፍ በማቅረብ አላማውን እና የአሰራር ሂደቱን ያብራራ ሲሆን ሰፊ ውይይት አካሂዷል ተባቧል።

በቅድስት ቤተክርስቲያኗ መዋቅር ውስጥ #ከዶግማ_በስተቀር ከላይ ጀምሮ እስከ ታች ድረስ ያሉ ችግሮችን ለማስተካከል እንደሠራም ተገልጿል።

ውጤቱን በተመለከተ ቤተክርስቲያን የራሷ #መንፈሳዊ_ፍርድ_ቤት እንዲኖራት ማድረግን ጨምሮ 25 ዝርዝር ነጥቦች ላይ ማተኮሩ ተመላክቷል።

#ከ90_በላይ አባላትን በጥናት ያሳተፈው ኮሚቴ በ14 ቡድኖች ተዋቅሮ ስራውን #በቅርቡ እንደሚጀምር ቤተክርስቲያኗ አሳውቃለች።

#EOTC_TV

@tikvahethiopia
#Tigray

ትግራይ ውስጥ ተቀስቅሶ ወደሌሎች ክልሎች በተስፋፋው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት " በሺዎች የሚቆጠሩ " የትግራይ ተዋጊዎች መሞታቸው፣ ሌሎች በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ከባድ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸውና ዘላቂ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸዉ የክልሉ ባለስልጣናት ማስታወቃቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር እንዳስታወቀዉ በጦርነቱ ለሞቱ የቀድሞ የትግራይ ሐይሎች አባላት፣ ቤተሰቦቻቸው #በቅርቡ በይፋ መርዶ ይነገራቸዋል።

ዛሬ በመቐለ ከተማ የትግራይ የጦር ጉዳተኞች ማእከል ስራ ባስጀመሩበት ወቅት ንግግር ያደረጉ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ፥ ቁጥሩን በትክክል ባይጠቅሱም " በሺዎች የሚቆጠሩ " ያልዋቸው የቀድሞ የትግራይ ሐይሎች አባላት በሁለት ዓመቱ ጦርነት መሞታቸውን አረጋግጠዋል።

የሟች ቤተሰቦችን ከማርዳት በተጨማሪ መስተዳድራቸዉ ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።

መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአማራ ክልል የሚገኙ የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዜዳንቶች በቅርቡ ከክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ አኳያ የመማር ማስተማር ሂደትን ማስቀጠል ይቻል እንደሆነ ውይይት እንዳደረጉ ቪኦኤ ዘግቧል። የክልሉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ዋና ፀሀፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ የዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዜዳንቶች ባደረጉት ውይይት ወቅታዊው የክልሉ የፀጥታ ችግር በቅርቡ ተማሪዎችን ተቀብሎ…
#Amhara

በአማራ ክልል የሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ዋና ጸሐፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን፤ የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎችን አቋም በተመለከተ በማኅበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር የነበረው መረጃ " #የተሳሳተ ነው " አሉ።

ከሰሞኑን በአማራ ክልል ስላሉ ዩኒቨርሲቲዎች ምንድነው የተባለው ?

ከቀናት በፊት ቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ የፎረሙን ዋና ጸሐፊ የሆኑትን ዶ/ር አስማረ ደጀንን ዋቢ በማድረግ ባወጣውና ቲክቫህ ኢትዮጵያም ባጋራው ዘገባ ፤ በአማራ ክልል የሚገኙ የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶች ከክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ አኳያ የመማር ማስተማር ሂደትን ማስቀጠል ይቻል እንደሆነ ውይይት ካደረጉ በኃላ ሁኔታው #በቅርቡ ተማሪዎችን ተቀብሎ የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማስቀጠል የሚያስችል እንዳልሆነ የጋራ መግባባት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።

በተጨማሪ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል፤
*  ተማሪዎች ገብተው ግጭቶች በሚመጡበት ጊዜ ዩኒቨርሲቲዎች ኃላፊነት እንደማይወስዱ፤

* ዩኒቨርሲቲዎች ለ2016 የሚሆን የምግብ አቅርቦት ማዘጋጀት የነበረባቸው ቢሆንም አቅራቢዎቹ ከቦታ ቦታ ፤ ምርት ካለበት ቦታ ሄደው ተዘዋውረው መግዛት ስላልቻሉ የምግብ ግብአቶች በጠቅላላው ተማሪን ሊያስጠራ የሚችል እንዳልሆነ ገልፀዋል።

ፎረሙ ትምህርት ሚኒስቴር " ለ2016 ትምህርት በአሁን ሰዓት ተማሪዎችን ጥሩ እያለ ነው " ብሎ ለፀጥታው ኃላፊነት የሚወስድ አካል ከሌለ ይህን ማድረግ #እንደሚያስቸግር ነው የገለፀው።

ከዚህ ባለፈ የፎረሙ አባልና የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ታፈረ መላኩ፤ በአካባቢው የቀጠለው አለመረጋጋት ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ እንደማያስችል ከተስማሙት የፎረሙ አባላት እንደሆኑ ገልጸዋል።

ያለው ሁኔታ ካልተሻሻለ በስተቀር አሁን ባለው ሀገራዊ ሁኔታ ላይ ግቢ ውስጥ ተማሪ ማስገባት በእጅጉ ፈታኝ እንደሚሆንና ለልጆችም ደህንነት በጣም አስጊ መሆኑን ፕሬዜዳንቱ ለጣቢያው ተናግረዋል።

ይህ መረጃ ከተሰራጨ ከቀናት በኃላ የፎረሙ ዋና ጸሐፊ ዶ/ር አስማረ ደጀን ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዛሬ በሰጡት ቃል " ሰሞኑን የተሰራጨው መረጃ በአማራ ክልል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ያልተባለና ስህተት ነው " ብለዋል።

በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን ለመቀበል አመች ሁኔታዎችን እየተጠባበቁ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በክልሉ የሚገኙ አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን መጥራት መጀመራቸውንም ገልጸው፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ጥሪ ማስተላለፉን ለአብነት አንስተዋል፡፡

"አብዛኞቹ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሁለተኛ እና የሦስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን እየጠሩ ነው" ያሉ ሲሆን " ብዙ ተማሪዎችን በአንድ ጊዜ ለመጥራት ግን የግብዓት ችግር ለተቋማቱ እንቅፋት ሆኗል " ብለዋል።

ዶ/ር አስማረ፤ በክልሉ በተፈጠረው የሰላም እጦት ግብዓት አቅራቢዎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው ለማቅረብ የተቸገሩ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲዎች የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየሠሩ መሆኑን አሳውቀዋል። በየአካባቢው ያሉ አቅራቢዎች ግብዓት እንዲያቀርቡ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎችን ተቀበሉ በሚልበት ጊዜ የማይቀበሉበት ምክንያት እንደሌለም ገልጸዋል።

" ክልሉ ያጋጠመው የጸጥታ ችግር እየተሻሻለ ከመጣ ተቋማቱ ተማሪዎቻቸውን ወዲያው ይጠራሉ፤ ተማሪዎችን አይጠሩም የተባለው ስህተት ነው፤ አልተባለምም " ሲሉ ተናግረዋል።

አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ግብዓት ለማግኘት ከመቸገራቸው ውጭ የመማሪያ ክፍሎችን አጽድተዋል፣እድሳት የሚያስፈልጋቸውንም አድሰው ለትምህርት ዘመኑ የመማር ማስተማር ዝግጁ ሆነዋል ሲሉ ለክልሉ ሚዲያ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ራስ ገዟ ሶማሊላንድ የሶማሊያ መንግሥትን አስጠነቀቀች። ከኢትዮጵያ ጋር የተፈረመውን የመግባቢያ ስምምነት ለማደናቀፍም ይሁን ለመቃረን የሚሞክር ማንኛውም ግለሰብ ይሁን አካል ላይ እርምጃ ወስዳለሁ ብላለች። የራስ ገዟ ሶማሌላንድ" የሚኒስትሮች ምክር ቤት " ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባ አድርጎ ነበር። ከስብሰባው በኃላ ባወጣው ባለ 8 ነጥብ የአቋም መግለጫ ፦ - ምክር ቤቱ እ.ኤ.አ. ጥር 1/2024…
#ሀርጌሳ

" ሀገራችንን አልሸጥንም " - ሙሴ ባሂ አብዲ

ባለፉት ቀናት ኢትዮጵያ የነበሩት የራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት ዛሬ ሐሙስ ዕለት ወደ ሀርጌሳ ተመልሰዋል።

ፕሬዚዳንቱ ሀርጌሳ ሲገቡ ህዝቡ ወደ አደባባይ ወጥቶ ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል።

አደባባይ ወጥቶ ለተቀበላቸው ህዝብ ባሰሙት ንግግር ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ትልቅ ዋጋ ያለው መሆኑ ገልጸዋል።

ፕሬዜዳንቱ " ሀገራችንን አልሸጥንም " ያሉ ሲሆን " ኢትዮጵያ የባህር ሃይል ጦር ሰፈር #በሊዝ ነው የምትከራየው " ብለዋል።

" ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ እውቅና ለመስጠትም ተስማምታለች " ሲሉ ተናግረዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ መቼ እንደሆነ ቀኑን በግልፅ ባይናገሩም የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት #በቅርቡ ለሶማሌላንድ እውቅና እንደሚሰጥ በድጋሚ ለህዝባቸው ገልጸዋል።

" ይህ የሶማሌላንድ ህዝብ ላለፉት ሶስት አስርት አመታት የደረሰበት ትልቅ ስኬት ነው " ሲሉም ገልጸዋል።

ስምምነቱ በሁለቱም ወገን በኩል ፍላጎትና ጥቅማቸውን መሰረት ያደረገ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።

በሌላ በኩል ፤ ሶማሌላንድን እንደ ራሷ አንድ ግዛት የምትቆጥራትና የተፈረመው ስምምነት ሉዓላዊነቴን ጥሷል በሚል የተቃወመችው ሶማሊያ ውስጥ ዛሬ የተቃውሞ የአደባባይ ሰልፎች ሲደረጉ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።

ፎቶ / ቪድዮ ፦ ሶማሌላንድ፣ ሀርጌሳ (ዛሬ ታህሳስ 25 ቀን 206 ዓ/ም)

@tikvahethiopia