TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"...ህወሓት ወደ ሌሎች ክልሎች የሚፈጽመው ጥቃት ግጭቱና የኢትዮጵያን ሕዝብ ሥቃይ ያራዝመዋል"-ሳማንታ ፓወር

#ዶቼቨለ

የአሜሪካ ተራድዖ ድርጅት ዋና አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር ዘጠኝ ወራት ባስቆጠረው የትግራይ ግጭት ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ሳምንት የዕርዳታ ሰራተኞች ለተቸገረው ሕዝብ የሚያቀርቡት ምግብ ተሟጦ እንደሚያልቅ አስታወቁ።

USAIDና አጋሮቹ እንዲሁም ሌሎች ሰብዓዊ ዕርዳታ አቅራቢ ድርጅቶች ትግራይ በሚገኙ መጋዘኖች ያከማቹት የምግብ ዕርዳታ ተሟጦ ማለቁን ገልጸዋል።

በጭነት ተሽከርካሪዎችና በነሐሴ ወር መጀመሪያ በሳምንት በአማካኝ 2 የUN ሰብዓዊ በረራ አገልግሎት ዕርዳታ ቢጓጓዝም "የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦቱ በአስከፊ ሁኔታ አሁንም በቂ አይደለም" ያሉት ሳምንታ ለተፈጠረው ችግር የኢትዮጵያን መንግሥት ወቅሰዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ሰብዓዊ ዕርዳታን፣ የሠራተኞች፣ የተሽከርካሪዎችና የአየር ጉዞዎችን "አስተጓጉሏል" ብለዋል።

አፋር ሰመራ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ ቦታዎች የዕርዳታ ድርጅቶች ምግብ ጭነው በመጠባበቅ ላይ ቢሆኑም ባለፈው ወር ወደ ትግራይ መግባት የተፈቀደላቸው ግማሽ ያክሉ እንደሆኑ ገልፀዋል።

100 ተሽከርካሪዎች በየቀኑ ትግራይ መድረስ ይኖርባቸዋል የሚሉት ሳማንታ ከሰኔ 24 ወዲህ ባሉት ጊዜያት 5ሺ ተሽከርካሪዎች ትግራይ መድረስ ቢኖርባቸውም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ 320 ብቻ ነው የደረሱት ይህ በቂ አይደለም ብለዋል።

ህወሓት ሌሎች ክልሎች የሚፈጽመው ጥቃት ግጭቱንና የኢትዮጵያን ሕዝብ ሥቃይ እንደሚያራዝመው ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል። ህወሓት ጥቃቱን በማቆም ኃይሎቹን ከአማራና ከአፋር ክልሎች እንዲያስወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

የአማራ ክልል መንግስት ከምዕራባዊ ትግራይ፣ የኤርትራ መንግሥት ወታደሮቹን ከኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ እንዲያስወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia
#WHO : "አዲሱ ቫይረስ የኮቪድ-19 ክትባቶችን የመቋቋም አደጋን እያሳየ ነው፤ የበለጠ ለመረዳት ጥናቶች ያስፈልጋሉ"

"ሙ" የተባለ አዲስ ልውጥ የኮሮና ተዋህሲ መከሰቱን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቀ።

ድርጅቱ «ሙ» በሚል በ12 ኛው የግሪክ ፊደል የሰየመውን የአዲሱን ልውጥ ቫይረስ ሁኔታ እየተከታተለ መሆኑን ገልጿል።

ድርጅቱ ፥ አዲሱ ልውጥ ቫይረስ በሳይንሳዊ መጠሪያው B.1.621 በመባል የሚታወቅ መሆኑን በትናንቱ የኮቪድ-19 ሳምንታዊ መግለጫ እመልክቷል።

አዲሱ ቫይረስ የኮቪድ-19 ክትባቶችን የመቋቋም አደጋን እያሳዬ መሆኑን የገለፀው ድርጅቱ፤ የበለጠ ለመረዳት ግን ጥናቶች እንደሚያስፈልጉ አጽንኦት ሰጥቶበታል።

ቫይረሱ ከታወቀበት ጊዜ ጀምሮ በደቡብ አሜሪካ እና በአውሮፓ ሀገራት ተገኝቷል ተብሏል።

ከዚህ ቀደም ለልውጥ ቫይረሱ በግሪክ የመጀመሪያው እና የሁለተኛው ፊደል «አልፋ» እና «ቤታ»የሚል መጠሪያ መሰጠቱም ይታወሳል። #ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የDAS ተሸላሚ ሆነዋል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የዘንድሮው የጀርመን አፍሪካ ፋውንዴሽን (DAS) ተሸላሚ ሆነዋል። ፋውንዴሽኑ በዛሬው ዕለት እንዳስታወቀው ዶ/ር ዳንኤል ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ላበረከቱት የህይወት ዘመን አስተዋፅኦ ከፍተኛውን ሽልማት ለመስጠት መወሰኑን አስታውቋል። ዶ/ር ዳንኤል ከ30 ዕጩዎች መካከል…
ፎቶ : የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆኑት እና በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን በዋና ኮሚሽነርነት እየመሩ የሚገኙት ዶ/ር ዳንኤል በቀለ በርሊን ብራንድቡርግ የ2021 የጀርመን አፍሪካ ሽልማት ተቀብለዋል።

ዶ/ር ዳንኤል ሽልማቱን ያገኙት በህይወት ዘመናቸው ለሰብአዊ መብት መከበር ባደረጉት ከፍተኛ ትግል ነው።

ሽልማቱን የጀርመን አፍሪካ ፋውንዴሽን ፕሬዝዳንት ኡሺ አይድ እና የጀርመን አፍሪቃ ፋዉንዴሽን ዳኞች ፕሬዝዳንት ክላዉስ ሽቴከር በጋራ ለዶ/ር ዳንኤል በቀለ አበርክተዉላቸወዋል።

የጀርመን አፍሪቃ ፋውንዴሽን ፕሬዝዳንት ኡሺ አይድ ፦

" ሽልማቱ ለምሳሌ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ፣ ሶማሌ ወይም አፋር ዉስጥ ያሉና ሳይፈሩ ለሰብአዊ መብት መከበር ለሚቆሙ ሁሉ ማበረታቻ ሊሆን ይገባል። " ብለዋል።

የጀርመን አፍሪቃ ፋዉንዴሽን ዳኞች ፕሬዝዳንት ክላዉስ ሽቴከር ፦

" ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት አስቸጋሪ ሁኔታ የኃላፊነት እና ድፍረት ምሳሌ ናቸው። " ሲሉ አሞግሰዋቸዋል።

ዶ/ር ዳንኤል ምን ያህል በአስቸጋሪ ሁኔታ ዉስጥ ሆነዉ ሥራቸዉን እያከናወኑ እንደሆነም ሽቴከር ተናግረዋል።

ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፦

" ሽልማቱ  ለሰብአዊ መብቶች መከበር በየቀኑ ለሚሰሩ እና በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ እንዲሁም በፖለቲካዊ ተቃውሞ ውስጥ እንኳን ሆነዉ የእኩልነት መርህን ለሚጠብቁ ባልደረቦቻቸዉ ሁሉ ይሁን " ብለዋል።

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
#Ethiopia #UNICEF

ስለምስራቅ አፍሪካ ድርቅ እና በሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ ስላሳደረው ተፅእኖ ምን ያህል እናውቃለን ?

(የተመድ የህጻናት ተራድኦ ድርጅት - UNICEF)

➤ ኢትዮጵያን ጨምሮ ምስራቅ አፍሪቃን የመታው ድርቅ ከ10 ሚሊየን በላይ #ህጻናት ለአስከፊ የምግብ እጥረት ዳርጓል። እስካሁን በርሃም አደጋው የሞተ ሰው አላጋጠመም።

➤ በኢትዮጵያ ባጋጠመው 3 ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች የዝናብ እጥረት በዓመታት አስከፊ የድርቅ ሁኔታ እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል፤ አስከፊው ድርቅ ለበርካታ እንስሳት ሞት ፣ የውኃ ምንጮችም ተሟጠው እንዲደርቁ መንስኤ ሆኗል።

➤ በ4 ክልሎች (ሶማሊ፣ ኦሮሚያ ፣ አፋር፣ ደቡብ ) ድርቅ በሰፊው የተከሰተባት ኢትዮጵያ ከችግሩ ለመላቀቅ ቢያንስ 5 ዓመታት ያስፈልጓታል።

➤ በኢትዮጵያ አራት ክልሎች (ኦሮሚያ፣ ሶማሊ፣ አፋርና ደቡብ) ድርቁ 10 ሚሊየን ህዝብ ላይ ቀጥተኛ ተፅእኖ አሳርፏል። ከዚህ ውስጥ 1.5 ያህሉ ለተመጣጠነ የምግብ እጥረት የተዳረጉ ህጻናት ናቸው፡፡ 

➤ በኢትዮጵያ ያለው ድርቅ 1.75 ሚሊየን ህዝብን ከመኖሪያ ቀዬው አፈናቋል።

➤ በሶማሊ ክልል ከ5 ዓመት በታች የሆኑ 220 ሺ ህጻናት ገደማ የተመጣጠነ ምግብ እጦት አለባቸው፡፡ ከ150 ሺህ በላይ አጥቢና እርጉዝ እናቶች በቂ ምግብ የማያገኙ ናቸው።

➤ ባለፈው ዓመት በችግሩ ሳቢያ ከ400 ሺ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ተቆራርጠዋል፡፡ ይህ ደግሞ ያለዕድሜ ጋብቻን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ ምስቅልቅሎችን አሳርፏል።

➤ በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ሳቢያ የናረው የስንዴና ሌሎች መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች ዋጋ የድርቅ ተፅእኖውን ምላሽ የመስጠት ጥረቶችን አዳጋች አድርጎታል።

#UNICEF #ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
#DireDawa

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ለቀጣይ አምስት ወር በመኖሪያ ቤት ተከራዮች ላይ ጭማሪ ማድረግም ሆነ ተከራዮችን ቤት ማስለቀቅ እንደማይቻል ውሳኔ አሳልፏል።

ከተማ አስተዳደሩ ፤ በመኖርያ ቤት ተከራዮች ላይ ምክንያታዊ ያልሆነ እና አለአግባብ ከፍተኛ ጭማሪ እየተደረገ መሆኑን በተለያየ መንገድ አረጋግጫለሁ ብሏል።

ይህን ተከትሎ ነው ለ 5 ወራት ተከራዮች ላይ ጭማሪ ማድረግ ሆነ ከተከራዩት ቤት ማስወጣት እንደማይቻል ውሳኔ ያሳለፈው።

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
#SNNPRS

አንደኛ በመኸር ዝናብ መዛበት ሁለተኛ በግጭት ምክንያት የሚፈናቀሉ ሰዎች መጨመር በደቡብ ክልል የተረጂዎችን ቁጥር ጨምሯል።

የደቡብ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን እንደሚለው፤ አሁን ላይ በደቡብ ክልል 3.3 ሚሊዮን ሰዎች ለከፋ ረሃብ / የምግብ ዋስትና ችግር ሊጋለጡ ይችላሉ ሲል ተንብዩዋል።

የከፋ ለሆነ የምግብ ችግር ሊጋለጡ ይችላሉ የተባሉት ከዚህ ቀደም የምግብ ችግር ኖሮባቸው በሴፍቲኔት መርሃ ግብር ሲደገፉ የነበሩ (917 ሺህ)፣ በግጭት የተፈናቀሉ (122 ሺ) ፣ በመኸር ዝናብ መጥፋት ምርት ያላገኙ (2.3 ሚሊዮን) ነዋሪዎች ናቸው።

በደቡብ ክልል የከፋ የምግብ እጦት ካለባቸው አካባቢዎች አንዱ የኮንሶ ዞን ህፃናት እና እናቶች ለከፋ ጉዳት መዳረጋቸውን ነዋሪዎች እየተናገሩ ነው።

በዞኑ አብዛኛው አካባቢዎች የእርዳታ አቅርቦት እየደረሰ እንዳለሆነ ነዋሪዎች ይገልፃሉ።

አንድ የኮልሜ ክላስተር ነዋሪ ፦

" ምንም አይነት እየመጣ አይደለም። ምንም አይነት ድጋፍ አላገኘንም። እኛ መጠበቅ ካለብን መንግሥት እንዲደርስልን ነው። ከሞት እንዲታደገን ነው። በገንዘብም ቢሆን መንግሥት እንዲረዳንና ከዚህ ዓመት ቢያሻግረን ብለን ነው የምንማፀነው። "

ሌላ ነዋሪ ፦

" አንደኛ ዝናብ ጠፋ ፣ በዛ ላይ የከብት ሳርም የለም። በመንግስት በኩል የሚደረግ እርዳታም የለም " ብለዋል።

የኮንሶ ዞን የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ከፈኔ ቲጫኖ በዞኑ ካላት ተረጂዎች እስካሁን ድጋፍ ያገኙ ግማሽ እንኳን እንደማይሆኑ ተናግረዋል።

በተለይ ደግሞ ከሀምሌ ወር ጀምሮ የምግብ ድጋፍ ፈላጊው ሊጨምር እንደሚችል ገልፀዋል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/SNNPRS-07-21

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UnitedNation የተመድ ዋና ፀሀፊ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች ትላንት በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተው የነበረ ሲሆን በመግለጫው ላይ የሰሜን ኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይን አንስተው ነበር። ስቴፋን ዱጃሪች ምን አሉ ? - በሰሜን ኢትዮጵያ አሁንም ግጭት መቀጠሉን እና አሁን ላይ ያለድ ሁኔታ ውጥረት የተሞላበት እንደሆነ ገልፀዋል። - የአፋር ክልል ከትግራይ ጋር በሚዋሰንባቸው ቦታዎች ማለትም…
የጃራ ተፈናቃዮች ጉዳይ!

የጃራ ተፈናቃዮች ትናንት ወደ አፋር ጭፍራ ቢሄዱም አትገቡም ተብለው ዛሬ ወደነበሩበት መመለሳቸውን ተናግረዋል።

በጃራ በመጠለያ ጣቢያ የሴቶችና ህፃናት አስተባባሪ ወ/ሮ ዘነበወርቅ ጣውዬ ፥

" በካምፑ ውስጥ ከተለያዩ የራያ፣ ኮረም ቆቦና ሌሎች አካባቢዎች ተፈናቅለው በመጠለያ ጣቢያው የነበሩ ከ30 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች ሰሞኑን ባገረሸው ግጭት በስጋት ሳቢያ ወደ ጭፍራ ተጉዘው አዳራቸውን በዚያው አድርገዋል።

ተፈናቃዮቹ ከማንነት ጋር በተያያዘ ከ 'ህወሓት' ጥቃት ይደርስብናል በሚልና ግጭቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ የውሃና የምግብ እጥረት በመከሰቱ ጭምር የሸሹ ናቸው። "

ከተፈናቃዮች መካከል አቶ ዝናቡ መሰለ ፦

" ሁሉም ተፈናቃይ ለሶስት ቀናት በመጠለያ ጣቢየው ቢቆይም፣ የምግብና የውሀ እጥረት በመከሰቱ እንደገና ለመፈናቀል ተገደናል።

የአማራ ክልልን አቋርጠን አፋር ክልል ብንደርስም ጠብቁ ተብለን እዛው ሜዳ ላይ አድረን ወደመጣቹበት ተመለሱ ተለናል።

በዚህም ምክንያት ዛሬ እየተመለስን ቢሆንም ብዙዎች አቅመደካሞች ህፃናትና እናቶች በየበረሀው ቀርተዋል።

አካባቢው እጅግ ሙቀት በመሆኑ ህፃናትና የሚያጠቡ እናቶች ለከፍተኛ የውሀ ጥምና ርሀብ ተጋልጠዋል። "

ትናንት ከጃራ ጭፍራ ዛሬ እንደገና ከጭፍራ ጃራ ተጉዘው ወደ መጠለያ ጣቢያው ከደረሱት መካከል አንዳንዶቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ቁሳቁሶችና የማብሰያ እቃዎች በመዘረፋቸው፣ የውሀና የምግብ አቅርቦት ባለመኖሩ ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን ገልፀዋል።

የሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዓለሙ ይመር ፦

" መጠለያ ጣቢያውን ሁሉም ተፈናቃዮች አለቀቁም። የሄዱትም ቢሆኑ እተመለሱ ነው ብለዋል፡፡  የእርዳታ እህልና ቁሳቁስ በተመለከተ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ቦታው ይላካል " #ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ገዳዮች ለፍርድ መቅረብ አለባቸው " ከሰሞኑን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ያሳለፈው አዲስ አደረጃጀት በጉጂ ዞን በተለያዩ ቦታዎች ተቃውሞ እንደገጠመው የቲክቫህ አባላት ከየአካባቢው አሳውቀዋል። ትላንት ከዚህ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ በቦሬ ማቲ በፀጥታ ኃይሎች በተወሰደ የኃይል እርምጃ የሰው ህይወት ስለመጥፋቱ ተሰምቷል። አንድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል " መንግስት በሰላማዊ ተቃውሞ…
" ሠልፉ ያልተፈቀደ ነበር " - የቦሬ ሰላምና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት

ትላንት በኦሮሚያ ክልል፣ ጉጂ ዞን ቦሬ ከተማ ከተቃውሞ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ 3 ሰዎች በፀጥታ ኃይሎች መገደላቸው መግለፁ ይታወሳል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቦሬ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት ዛሬ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ በሰጠው ቃል ፤ ትላንት በከተማው ስለደረሰው ጉዳት ማረጋገጫ ሰጥቷል።

የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ቡሌ ትናንት በከተማው በተካሄደው ሠልፍ ጉዳት መድረሱን አረጋግጠው " ሠልፉ ያልተፈቀደ " እንደነበር ገልጸዋል።

ኃላፊው ፤ " አንዳንድ የሠልፉ ተሰታፊዎች በተቋማት ላይ #ድንጋይ በመወርወር እና ገበያ በመበተን ሁከት ለመፍጠር ሞክረዋል " ብለዋል።

" የፀጥታ አባላት የጉዳቱ መጠን ሳይሰፋ ለመቆጣጠር ችለዋል " ሲሉም ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።

Credit : #ዶቼቨለ_ሬድዮ
Photo : Social Media

@tikvahethiopia
#መቐለ

" የተለያዩ በደሎች እየደረሱብን ነው " ያሉ በትግራይ የሚገኙ የጦር ጉዳተኞች ዛሬ በመቐለ ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄዳቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ከመቐለ ዘግቧል።

ፖሊስ ሰልፉ ለመበተን አስለቃሽ ጭስ ተኩሷል ተብሏል።

የጦር ጉዳተኛ ሰልፈኞቹ ከመቐለ ከተማ ወጣ ብሎ ከሚገኘው " መለስ ካምፓስ የጦር ጉዳተኞች ማእከል " በመነሳት እስከ የትግራይ ክልል አስተዳደር መሥርያ ቤት የተለያዩ መፈክሮች እያሰሙ ነበር የተጓዙት።

ሰልፍ የወጡት በአብዛኛው #ወጣቶች የጦር ጉዳተኞች ፦

- «እየደረሰብን ያለውን አስተዳደራዊ በደል ሕዝብ ይስማልን፣ ይወቅልን»

- «በኛ ስም ከሕዝብ የሚሰበሰብ መዋጮ እኛጋ እየደረሰ አይደለም፤ በተደጋጋሚ ጥያቄ ብናቀርብም ምላሽ አጥተናል»

- «በቂ ምግብና ውኃ እንኳን አጥተን የከፋ ሁኔታ ላይ ነን»

- «የታጋዮች ድምፅ ይሰማ»

- «ትኩረት ለጦር ጉዳተኞች»

- «ተክደናል» የሚሉና ሌሎች ብልሹ አሠራሮች የሚያወግዙ መፈክሮችን ያሰሙ እንደነበር ሬድዮ ጣቢያው ዘግቧል።

ሰልፈኞቹ " ድምፃችንን ለማሰማት ወደ ከተማ እንዳንገባ መቐለ ዩኒቨርስቲ አሪድ ካምፓስ አካባቢ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ጭምር እንድንበተን ሙከራ ተደርጓል "  ሲሉም ተናግረዋል።

ዶቼ ቨለ ሬድዮ ፤ የጦር ጉዳተኞቹ ሰልፍ ከፍተኛ የቁጣ ስሜት ይታይበት ነበር ያለ ሲሆን ሁኔታው በሃይማኖት አባቶች ሸምጋይነት እንዲረጋጋ ተደርጓል ብሏል።

ሰልፈኞቹ የክልሉ አስተዳደር መ/ቤት በሆነው ደጀን ቢሮ በር  ቆይታ የነበራቸው ሲሆን የሕወሓት ከፍተኛ አመራር አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ከሌሎች ወታደራዊ መሪዎች ጋር በችግሮቻቸው ዙርያ መወያየታቸውን ሬድዮ ጣቢያው ዘግቧል።

#ዶቼቨለ_ሬድዮ

@tikvahethiopia
" የቡድን እና የነፍስወከፍ መሳሪዎችን የማስፈታቱ ሂደት ዘግይቷል " - የብሔራዊ መልሶ ማቋቋም ኮሚሽን

የፕቶሪያውን የህወሓትና የፌደራል መንግስትን ስምምነት ተከትሎ ህወሓት ታጥቋቸው የነበሩ ከባድ መሳሪያዎችን የማስፈታት ሥራው በተሳካ ሁኔታ ቢፈፀምም፣ የቡድንና የነፍስወከፍ መሳሪዎችን የማስፈታቱ ሁኔታ በተለያዩ ምክንያቶች መዘግየቱን የብሔራዊ መልሶ ማቋቋም ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ ይህን ያስታወቀው ዛሬ በባህር ዳር ከተማ በተዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ነው።

የተሀድሶ ኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ፤ አገራችን ባለፉት ሁለት ዓመታት በጦርነት ውስጥ ማለፏን ጠቅሰው ጦርነቱ ያስከተለውን ጥፋት በማየትና ካለፍንባቸው ችግሮች መማርና ወደ ሰላም መምጣት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያ በበኩላቸው፤ የፕሪቶያውን ስምምነት ተከትሎ የትግራይ ኃይሎች የከባድ መሳሪያ ትጥቅ መፍታታቸውን ጠቁመዋል።

የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን ግን በተለያዩ ምክንያቶች እስካሁን ማስፈታት ሳይቻል መቆየቱን ተናግረዋል፡፡

ለመዘግየቱ ዋነኞቹ ምክንቶች ፦ ኮሚሽኑ የቅድመ ዝግጅት ስራ ስለነበረበት፣  በትግራይ ክልል የሽግግር መንግስት ሳይቋቋም በመቆየቱና ሌሎች አንዳንድ መሰናክሎች እንደነበሩ ነው ያስረዱት፡፡

አሁን ግን ሁኔታዎች እየተስተካከሉ በመሆኑ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ተግባራት ይፈፀማሉ ብለዋል።

በውይይት መድረኩ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርን ዶ/ር ጌታቸው ጀንበርን ጨምሮ ሌሎች የሲቪልና ወታደራዊ ባለስልጣናት ተገኝተው እንደነበር ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
#Oromia

" የልዩ ኃይል ስምሪት አቁመናል ፤ ... በክልሉ ያለውን የፀጥታ ማስከበር ሥራ የአገር መከላከያ ሠራዊት ተረክቧል " - የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የልዩ ኃይል አደረጃጀት ስምሪት ማቆሙን አስታወቀ።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ ከዶይቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ ነው ይህንን ያሳውቁት።

ዋና ኮሚሽነሩ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ፤  የፌዴራሉ መንግሥት ባስተላለፈው መሠረት የልዩ ኃይል አደረጃጀት መዋቅርን በተለያዩ የፀጥታ መዋቅሮች መልሶ የማደራጀቱ ተግባር እየተከናወነ ነው ብለዋል።

በክልሉ ያለውን የፀጥታ ማስከበር ሥራንም #የአገር_መከላከያ_ሠራዊት መረከቡን ገልጸዋል።

" የልዩ ኃይል አደረጃጀት ቀድሞውኑም ለጊዜያዊ የፀጥታ ችግር ያለ ሕገ መንግስታዊ መርህ ነው " የተመሰረተው የሚሉት ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ ለሁሉም ክልሎች በወጥነት ተላልፏል ያሉትን መዋቅሩን በሌላ ፀጥታ ተቋማት የማደራጀቱ ሥራ እየተተገበረ ነው ብለዋል።

" ግንዛቤ ውስጥ መግባት ያለበት የሚፈርስ የሚለው መልሶ ለመገንባት በሚል መወሰድ አለበት። እንደ ወንጀለኛ ፈርሶ የሚሳደድ አካል የለም። አደረጃጀቱ ስህተት ስለነበረበት በዚህ መደራጀት አለበት የሚል ነው መወሰድ ያለበት። አንድ ሕጋዊ ክፍተት መኖሩ ሲሆን ሌላው የሚገዳደር የተለያዩ የፀጥታ መዋቅሮች በአንድ አገር ውስጥ አያስፈልግም በሚል የፀጥታ ችግሮች በመከላከያ፣ በፌዴራል ፖሊስ እና በክልሎች መደበኛ ፖሊስ በየደረጃው እንዲሠራ በሁሉም ውይይት ተደርጎበት የተወሰነው። " ሲሉ ተናግረዋል።

ውሳኔው ሁሉንም ክልሎች የሚመለከት እንደሆነ የገለፁት ኮሚሽነር አራርሳ በተደረገው ውይይትና በተደረሰበት ስምምነትም አተገባበሩም በአንድ ላይ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

ሂደቱን የአገር መከላከያ እንደሚያስፈጽም መወሰኑንም አመልክተዋል።

" የፌዴራል መንግሥት ውሳኔውን ያስተላለፈው ሁሉም ክልሎች ተግባራዊ እንዲያደርጉ ነው። ከዚያ ውስጥ ኦሮሚያ አንዱ እንደመሆኑ መመሪያውን ተቀብለን በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት እያደራጀን ነው። ኦሮሚያ አላፈረሰም ለአንዳንድ ክልል ብቻ የተላለፈ ነው ሚለው እውነት አይደለም ብቻ ሳይሆን በሬ ወለደ እንደ ማለት ነው። ይሄ የሚደበቅም ስላልሆነ ምንም የተለየ ማብራሪያ አያሻውም። ንጹሑ ህዝብ ግን እንዳይደናገር ውሳኔው ማንንም የሚመለከት መሆኑን ቢገነዘሙ መልካም ነው። " ብለዋል።

አሁን በክልሉ የሚሰማራ የልዩ ኃይል አደረጃጀት የለም ያሉት ኮሚሽነር አራርሳ በመከላከያ፣ በፌዴራል ፖሊስ እና በክልል መደበኛ ፖሊስ እንደየሚያስፈልገው መስፈርት እየተደራጁ ለስልጠና እየተሰማሩመሆኑንም ተናግረዋል።

" በሁሉም የፀጥታ መዋቅሮች አልደራጅም ያለ አሊያም በጡረታ መገለልም ያለበት በደንቡ መሰረት የመሸኘቱ ሥራ እየተተገበረ " ነው ብለዋል።

#ዶቼቨለ_ሬድዮ

@tikvahethiopia
" የኢትዮጵያ መንግስት የመገናኛ ዘዴ ባለሙያዎችን ይልቀቅ " - አምንስቲ ኢንተርናሽናል

የኢትዮጵያ መንግስት ተቃዉሞን በሰላማዊ ሰልፍ የመግለፅ መብትን እንዲያከብርና የታሰሩ የመገናኛ ዘዴ ባለሙያዎችን እንዲፈታ አምንስቲ ኢንተርናሽናል ጠየቀ።

ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት ትናንት ባወጣዉ መገለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ባለፈዉ ሳምንት አማራ ክልል በተፈጠረዉ ሁከት ምክንያት ያሰሯቸዉን 7 የመገናኛ ዘዴ ባልደረቦች ባስቸኳይ እንዲፈቱ፣ ከእስረኞቹ ባንዷ ላይ ተፈፀመ የተባለዉን አካላዊ ጥቃት እንዲያጣሩ ጠይቋል።

መግለጫዉ እንዳለዉ  ባለስልጣናቱ " ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትንና ሁሉም ወገን በሰላማዊ መንገድ የመቃወም መብቱን ማስከበር አለባቸዉ። "

ባለፈዉ ሳምንት በአማራ ክልል የመብት ጥሰትና ሁከት መቀስቀሱ እንዳሳሰበዉ የመብት ተሟጋቹ ድርጅት አስታዉቋል።

በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የተኩስ ልዉዉጥ መደረጉ፣ የሰብአዊ ርዳታ አቀባይ ድርጅት ሰራተኞችን ጨምሮ ሰዎች መገደላቸዉ፣ አዲስ አበባ ዉስጥ ሰዎች በጅምላ መታሰራቸዉንም ድርጅቱ «አሳሳቢ» ብሎታል።

የመንግስት ኃይላትም ሆኑ #ሌሎች ታጣቂዎች " የሰብአዊ ርዳታ ሰራተኞችን ያለማጥቃት ኃላፊነት አለባቸዉ። " ብሏል አምነስቲ።

የኢትዮጵያ መንግስት " አስቸኳይ፣ ጥልቅ፣ ገለልተኛና ዉጤታማ ምርመራ አድርጎ ተጠያቂዎችን ለፍርድ ማቅረብ አለበት " እንደ መግለጫዉ።

በምስራቅ አፍሪቃ፣ በአፍሪቃ ቀንድና በታላላቅ ሐይቆች አካባቢ የአምንስቲ ኢንተርናሽናል ምክትል ተጠሪ ፍላቪያ ምዋንጎቭያ «ዘግናኝ» ያሉት የገነት አስማማዉ፣ ጌትነት አረጋዊ፣ አራጋዉ ሲሳይ፣መስከረም አበራ፣ አባይ ዘዉዱ፣ ዳዊት በጋሻዉና ቴዎድሮስ አስፋዉ መታሰር ሐሳብን በነፃነት በመግለጥ መብትና በመገናኛ ዘዴ ነፃነት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ነዉ።

የኢትዮጵያ ባለስልጣናት 7 የመገናኛ ዘዴ ሰራተኞች ባስቸኳይ እንዲለቁና የተመሰረተባቸዉን ክስ እንዲነሱም ምዋንጎቭይ ጠይቀዋል።

በሌለ በኩል ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በተመረጡ የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ የጣለዉን ማዕቀብ እንዲያነሳም ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት ጠይቋል።

አምንስቲ ኢንተርናሽናል እንደሚለዉ የኢትዮጵያ መንግስት እገዳዉን ከጣለ 3ኛ ወሩን ይዟል።

እገዳዉ ሰዎች መረጃ እንዳያገኙ መገደብን ጨምሮ የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን የመጠቀምና ያለመጠቀም የሰብአዊ መብትን የሚጥስ ነዉ።

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #NEBE የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በ1,812 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያስፈጸመውንና 849,896 መራጮች ድምፅ የሰጡበትን የወላይታ ዞን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ  የውጤት ማዳመሩን ሥራ በዞኑ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሲያከናወን መቆየቱን ገልጿል። በዛሬውም ዕለት ቦርዱ የውጤት  የማመሳከሩንና የማዳመሩን ሥራ በማጠናቀቅ በዞን ደረጃ #የጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርጓል።…
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ፦

የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በደቡብ ክልል 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች በአንድ የጋራ ክልል ለመደራጀት ያካሄዱትን የህዝበ ውሳኔ ውጤት በሙሉ ድምፅ አጸድቋል።

ይህም ማለት በኢትዮጵያ 12ኛው ክልል እንዲደራጃ ይሁንታ ሰጥቷል።

በዚህም መሠረት ፦

ላለፉት 30 ዓመታት ገደማ በደቡብ ክልል ሥር ሲተዳደሩ የቆዩት ፦
👉 የዎላይታ ፣
👉 የጋሞ ፣
👉 የጎፋ ፤
👉 የኮንሶ ፣
👉 የደቡብ ኦሞ ፣
👉 የጌዲኦ ዞኖች እንዲሁም
👉 የአማሮ ፣
👉 የቡርጂ ፣
👉 የደራሼ ፣
👉 የአሌ እና የባስኬቶ ልዩ ወረዳዎች የፌዴራል ሪፐብሊኩ 12ኛ ክልል ሆነው " ደቡብ ኢትዮጵያ " በሚል እንዲደራጁ ምክር ቤቱ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

በሌላ በኩል ፦
👉 የሃድያ ፣
👉 የከንባታ ጠንባሮ ፣
👉 የሀላባ ፣
👉 የሥልጤ ፣
👉 የጉራጌ ዞኖችና እና የየም ልዩ ወረዳ ራሳቸውን መልሰው በማደራጀት #በነባሩ ክልል እንዲቀጥሉ ሲል ምክር ቤቱ ወስኗል።

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ታጣቂዎቹ በለሊት ከነ #መሳሪያቸው ወደ ጫካ ገብተዋል " - ከንቲባ አቶ ጊሳ ዙፋህ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፤ ግልገል በለስ " የሰላም ጥሪ ተቀብለው መጡ " የተባሉ ታጣቂዎች ከነትጥቃቸው ወደ ጫካ ተመልሰው ገብተዋል።

ይህን ጉዳይ በተመለከተ የግልገል በለስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጊሳ ዙፋህ ለዶቼ ቨለ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

ከንቲባው ፤ ከሚያዚያ 24 ጀምሮ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው የመጡ የሰላም ተመላሾች በከተማው ለ2 ወራት ያህል መኖራቸውን ገልጸዋል።

ከዛሬ ሁለት ቀን በፊት ወደ ተሀድሶ ስልጠና እንዲገቡ ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ ባለበት ሰዓት ባልታወቀ ምክንያት ታጣቂዎቹ በለሊት ከነ መሳሪያአቸው ወደ ጫካ መግባታቸውን አብራርተዋል፡፡

ታጣቂዎቹ በሰላማዊ መንገድ እንዲመለሱ ለማደረግ ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ በመተከል ዞን ውስጥ የተከሰቱ የጸጥታ ችግሮችን እና የታጣቂዎችን እንቅስቃሴ ከፓርቲው ጋር ለማገናኘት እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን እቃወማለሁ ብሏል።

ፓርቲው ታጥቆ የሚንቀሳቀስ ሀይል እንደሌለው ገልጿል።

በቅርብ " የሰላም ተመላሽ " ተብለድ በመተከል ዞን ግልገል በለስ የነበሩ ታጥቂዎችን የጉህዴን ታጣቂዎች ናቸው በማለት " በድርጅቱ ስም መነገድ የሚፈልጉ " አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ፓርቲው አሳስቧል።

በካምፕ ውስጥ የነበሩ ከአንድ መቶ የሚበልጡ የሰላም ተመላሽ የተባሉ ታጣቂዎች ወደ ጫካ መመለሳቸውን ፓርቲው ገልጿል።
 
ፓርቲው፤ ከጥቅምት 9/2015 ዓ.ም አንስቶ ከመንግስት ጋር በተደረሰው ስምምነት መሰረት በስሙ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎቹን በሰላማዊ መንገድ ትጥቅ እንዲፈቱ ማድረጉን አስረድቷል።

በተቀመጠው ስምምነት መሰረት በተዘጋጁ  ዘርፎች ወደ ስራ መሰማራታቸውንም አመልክቷታ።

በአሁኑ ጊዜ በፓርቲው ስም ታጥቆ የሚንቀሳቀስ ሐይል አለመኖሩን አሳውቋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከፓርቲያቸው ጋር ግንኙነት የሌላቸው በርካታ ታጣቂዎች ከመንግስት ጋር በመስማማት በሰላማዊ መንገድ ወደ ካምፒ መግባታቸውን ያሳወቀው ጉህዴን " በሚያዚያ ወር መጨረሻም ወደ ግልገል በለስ ከተማ የገቡ ታጣቂዎች ከፓርቲው ጋር ግንኙነት የለላቸው እና መንግስት ያደረገላቸውን ሰላማዊ ጥሪ የተቀበሉ  ታጣቂዎች ናቸው " ብሏል።

በዞኑ እና ሌሎች ስፍራዎች የሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮችን ከፓርቲው ጋር ለማገናኘት የሚደረጉ ጥረቶችን ተቀባይነት የላቸውም ያለው ጉህዴን " በታጣቂዎች ለሚደርሱት ጥቃቶችም ድርጅቱ ኃላፊነት አይወስድም " ሲል አስረግጧል።

በግልገል በለስ ከተማ ሰነ 30 ቀን 2015 ዓ.ም በታጣቂዎች በደረሰው ጥቃት ጸጥታ ሐይሎችን ጨምሮ 11 ሰዎች ህይወት ማለፉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል፡፡

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
" ሱተን ዙሪያ ቀበሌ ድረስ ተከታትለው በመምጣት ነው የገደሉት ፤ ... ይሄን ለማን አቤት ልበል ? " - ወላጅ አባት

በኦሮሚያ ክልል፤ ደ/ምዕራብ ሸዋ ዞን  የትራፊክ ፖሊስ አባላት የጠየቁትን ያህል ጉቦ አልሰጥም ያለን አንድ አሽከርካሪ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን የሟች ቤተሰቦችና የሥራ ባልደረቦች መግለፃቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

ድርጊቱ የተፈፀመው ባለፈው ዓርብ ዕለት ሲሆን በትራፊክ ፖሊስ አባላቱ በጥይት የተገደለው እና ትላንት ስርዓተ ቀብሩ ተፈፀመ የተባለው የ33 ዓመት እድሜ ያለው ሳሙኤል መረተ ነው።

ሳሙኤል መረት ነዋሪነቱ በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ውስጥ ነበር፡፡

ጓደኞቹ እንዳሉት ሳሙኤል ከረጅም ጊዜ አንስተቶ የአሽከርካሪነት ሥራውን ሲያከናውን የቆየው ከአዲስ አበባ ቡታጅራ በተዘረጋው መስመር ላይ ነበር።

በመስመሩ በሰበብ አስባቡ ካልቀጣንህ የሚሉትን የትራፊክ ፖሊስ አባላት ለማባበል ዝርዝር የ " ሃምሳ ብር " ኖቶችን በእጃቸው እያስጨበጠ ማለፍ የሁልጊዜ ተግባሩ እንደነበር  ጓደኞቹ ይናገራሉ።

ይህ የሃምሳ ብር ጣጣ ታዲያ  " አንሷል ጨምር አልጨምርም " በሚል ከትራፊክ ፖሊስ አባላት ጋር የገባበት እሰጥ አገባ ለህይወቱ መጥፋት ምክንያት መሆኑን ነው በሥፍራው ነበርን ያሉ ገልጸዋል።

የሳሙኤል ረዳት ምን አለ ?

የሳሙኤል መረተ ረዳት ሆኜ ሥሠራ ነበር የሚለው አንዱዓለም ሁሴን ፦

" መንገደኞችን አሳፍረን ከአዲስ አበባ ቡታጅራ በመጓዝ ላይ እያለን በኦሮሚያ ክልል ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ተሬ ወረዳ ላይ ስንደርስ ሦስት ትራፊኮች ያስቆሙናል።

ሳሙኤል የመውጫ ወረቀት እና ሃምሳ ብር ሲሰጥ ከትራፊኮቹ አንዱ ሀምሳውን ቀይረህ መቶ አድርግ ሲለው ሰምቻለሁ።

ሳሙኤል አሁን የለኝም አልተዘጋጀሁም ሲለው ትራፊኩ አለበለዚያ የተሸከርካሪውን ሠሌዳ እፈታለሁ በማለት በቦክስ መታው፡፡

ይሄኔ በንዴት ተሽከርካሪውን አስነስተን ወደፊት መሄድ ስንጀምር ተከትለው መተኮስ ጀመሩ፡፡

ጥቂት እንደተጓዝን ተሸከርካሪውን በማቆም እኔም ሆንኩ ሌሎች መንገደኞች ደንግጠን ወረደን መሮጥ ጀመርን፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እሱን በጥይት መትተው ጣሉት " ሲል ቃሉን ሰጥቷል።

የሟች ሳሙኤል አባት አቶ መረተ ለማ በበኩላቸው ፤ ከትራፊክ ፖሊስ አባላቱ ጋር አለመግባባቱ የተነሳው በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ተሬ ወረዳ ላይ ቢሆንም ግድያው የተፈጸመው ግን በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ሱተን ዙሪያ ቀበሌ ድረስ ተከታትለው በመምጣት  አንደሆነ ገልጸዋል።

" ይህን ለማን አቤት ልበል ? " ሲሉም ጠይቀዋል ፡፡

በኦሮሚያ ክልል ደ/ምዕራብ ሸዋ ዞን የተሬ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ፈይሳ ደበላን ጉዳዩን በተመለከተ ከሬድዮ ጣቢያው ተጠይቀው ፤ ወንጀሉ የተፈጸመው እሳቸው ከሚመሩበት የተሬ ወረዳ አልፎ ጉራጌ ዞን ውስጥ መሆኑን በመጥቀስ " በዚህ ላይ እኔ የምለው ነገር የለም ፤ ባይሆን የደቡብ ክልል ፖሊስን ጠይቁ " ብለዋል።

የጉራጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር ጠጄ መሀመድ ፤ የወንጀሉ አድራሾች በኦሮሚያ ክልል ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኙ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ናቸው ብለዋል።

አሁን ላይ ድርጊቱን በመፈጸም የተጠረጠሩ ሦስት የትራፊክ ፖሊሶች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ገልጸዋል።

" የተከሰተው ነገር አሳዛኝ ነው " ያሉት ኮማንደር ጠጄ " የወንጀሉ ተጠርጣሪዎች ወዲያው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ጥሩ ነገር ነው፡፡ አሁን ምርመራውን ከኦሮሚያ ክልል የሥራ ሃላፊዎች ጋር አብረን እየሠራን እንገኛለን ፡፡ ወንጀሉ የተፈጸመው በጉራጌ ዞን ውስጥ በመሆኑ ምርመራውን ወደ ዞኑ ለማዛወር በሂደት ላይ ነው ያለነው " ብለዋል፡፡

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ምዕራባውያን በአንድ በኩል የእህልና የማዳበሪያ አቅርቦታችን እያስተጓጎሉ ነው። በሌላ በኩል በዓለም የምግብ ገበያ ለተፈጠረው ቀውስ ግብዝ ሆነው እኛን ይከሱናል " - ፑቲን

የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ኤርትራ እና ሶማሊያን ጨምሮ ለስድስት የአፍሪካ አገሮች ስንዴ በነጻ ለማቅረብ ቃል ገቡ።

ፕሬዝደንቱ ይኸን ቃል የገቡት የአፍሪካ - ሩሲያ ጉባኤ በሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ሲጀመር ባሰሙት ንግግር ላይ ነው።

ፑቲን ፤  " በመጪዎቹ ሦስት እና አራት ወራት ከ25,000 እስከ 50,000 ቶን እህል በነጻ ለቡርኪና ፋሶ፣ ዚምባብዌ፣ ማሊ፣ ሶማሊያ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ እና ኤርትራ ለማቅረብ ዝግጁ እንሆናለን " ብለዋል።

የፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን መንግሥት የዩክሬን የእህል ለዓለም ገበያ እንዲቀርብ ይፈቅድ የነበረው ሥምምነት እንዲያበቃ በመወሰኑ አሜሪካን ጨምሮ ከምዕራባውያን ብርቱ ትችት ሲሰነዘርበት ቆይቷል።

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በቱርክዬ አደራዳሪነት በተፈረመው ሥምምነት መሠረት 32.9 ሚሊዮን ቶን የምግብ እህል ከዩክሬን የእህል ጎተራዎች ለዓለም ገበያ ቀርቧል።

የሩሲያን ውሳኔ ኃላፊነት የጎደለው ሲሉ የሚተቹ የምዕራቡ ዓለም ፖለቲከኞች በደሐ አገሮች የሚኖሩ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ለረሐብ ይጋለጣሉ ሲሉ ያስጠነቅቃሉ።

ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ግን በሴንት ፒተርስበርግ በመካሔድ ላይ በሚገኘው ስብሰባ በሥምምነቱ ከዓለም ገበያ ከቀረበው እህል ከ70 በመቶ በላይ የሚሆነው ከፍተኛ ገቢ ወይም ከአማካኝ በላይ ገቢ ላላቸው አገራት እንደቀረበ ተናግረዋል። 

" ምዕራባውያን አገሮች በአንድ በኩል የእህል እና የማዳበሪያ አቅርቦታችን እያስተጓጎሉ ነው። በሌላ በኩል አሁን በዓለም የምግብ ገበያ ለተፈጠረው ቀውስ ግብዝ ሆነው እኛን ይከሱናል" ሲሉ ተደምጠዋል።

በሴንት ፒተርስበርግ እየተካሄደ ባለው የሩስያ አፍሪካ ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድን ጨምረ የሌሎችም ሀገራት መሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ፕሬዝደንት ፑቲን ትላንት ረቡዕ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ከግብጽ ፕሬዝደንት አብዱል ፋታኅ አል-ሲሲ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
#አማራ

በአማራ ክልል ወቅታዊ የክልሉ የሰላም መደፍረስ በፈጠረው የመንገዶች መዘጋጋት እና መድኃኒቶች በቀላሉ ወደ ጤና ተቋማት መድረስ ባለመቻላቸው ህሙማን ተገቢውን ህክምና እያገኙ እንዳለሆነ የጤና ባለሙያዎች መናገራቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

በደምና በኦክስጅን አቅርቦት ችግር ወላዶች ለሞት እየተዳረጉ እንደሆነም ተገልጧል።

ከሐምሌ 2015 ዓ/ም መጨረሻ ጀምሮ በአማራ ክልል በተቀሰቀሰው ጦርነት በርካታ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ሥራቸው ተስተጓጉሏል።

ችግር ካጋጣማቸው ተቋማት መካከል የፀጥታ ችግሮች ባሉባቸው የምዕራብ አማራ አካባቢ የጤና ተቋማት ይጠቀሳሉ።

ነዋሪዎች እና የጤና ባለሞያዎች ምን ይላሉ ?

በምዕራብ ጎጃም ዞን ፈረስ ቤት ከተማ የሚገኙ አንድ ታካሚ ያጋጠማቸውን የመድኃኒት እጥረት ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል

" ኤሌክትሪክ አደጋ ደርሶብኝ ለመታከም ወደ ሆስፒታል ሄጀ ነበር፣ መድኃኒት በሀኪም ቤቱ ባለመኖሩ ከግል መድኃኒት ቤት መድኃኒት በ12 ሺህ ብር ገዝቻለሁ፣ በግል መድኃኒት ቤት ያሉ መድኃኒቶችም እያለቁ ነው። "

በምዕራብ ጎጃም ዞን የቡሬ ሆስፒታል ባለሙያ ፦

" በመድኃኒትና በደም እጥረት ምክንት  ህሙማን  በተለይ እናቶች እየሞቱ ነው። የደምና የኦክስጅን እጥረት በከፋ ሁኔታ በሆስፒታሉ ይስተዋላል። "

የፍኖተሰላም ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ  አቶ ማናየ ጤናው ፦

" በደምና በኦክስጅን አቅርቦት እጥረት በቅርቡ ሁለት ወላዶች ሕይወታቸው አልፏል። "

በምሥራቅ ጎጃም ዞን የየጁቤ ሆስፒታል ሐኪም፦

" በአካባቢ ከሚገኙ ወረዳዎች በመበደርና በትብብር በመውሰድ የመድኃኒት አገልግሎት ለታማሚዎች እያቀረብን ነበር። አሁን ግን ወረዳዎችም መድኃኒት በመጨረሳቸው ያን ማድረግ አልተቻለም። "

ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ የደብረማርቆስ ሆስፒታል ሐኪም ፦

" የመድኃኒትና የጀነሬተር እጥረቶች፣ እንዲሁም የመብራት መቆራረጥ በተለይ የቀዶ ህክምና አገልግሎት ለመስጠት ፈተና ሆኗል።

ያለ መድኃኒት በሆስፒታሉ ውስጥ መሥራት፣ ያለ ጥይት መሳሪያ ይዞ ጦርሜዳ እንደመዋል ነው። "

የደብረ ማርቆስ የደም ባንክ አስተባባሪ አቶ ከፋለ ገበየሁ ፦

" ወቅታዊ ሁኔታው ደም ለመሰብሰብ አላስቻለንም።

ደም ለመሰብሰብ ሁለት ዓይነት መንገዶች አሉ፤ አንዱ ጊዜያዊ ድንኳኖችን አቁሞ ከፈቃደኞች ደም መውሰድ ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ ወደ ደም ባንክ ማዕከሉ የሚመጡ በጎ ፈቃደኞችን መቀበል ነው። ይሁን እንጂ አሁን ያን ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ የለም።

ናሙናዎችን ወደ ባሕር ዳር ለመውሰድም የመንገዶች በፀጥታ ሁኔታ መዘጋጋት ሌላው አስቸጋሪ ሁኔታ ነው። "

የመድኃኒት አቅርቦትን በተመለከተበኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ምን ይላል ?

የባሕር ዳር ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ አምሳሉ ጫኔ ፦

" የፕሮግራም የሚባሉ መድኃኒቶች ከለጋሽ ድርጅቶች በእርዳታ የሚሰጡ ሲሆን በራሳችን መሥሪያ ቤት በግዥ የሚፈፀሙ ደግሞ አሉ፣ ሁለቱንም ለማጓጓዝ አውሮፕላን እንጠቀማለም ከዚያም መድኃኒቱ ባሕር ዳር ከደረሰ በኋላም አንፃራዋ ሰላም ባለባቸው አካባቢዎች መድኃኒቶቹ ይሰራጫሉ።

የመንገድና የፀጥታ ችግሮች እያሉም ሰሞኑነ የተወሰኑ መድኃኒቶችን ወደ ምሥራቅ ጎጃም ማድረስ ችለናል።

ወደ ምዕራብ ጎጃም አካባቢዎችም ለማድረስ ጥረት እየተደረገ ነው ሆኖም አሁንም የመንገዶች ሁኔታ አስቸጋሪ ነው። "

Credit - #ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዳሬሰላሙ ድርድር ምን ይዞ ይመጣል ? በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ጊዜያት በተፈጠሩ ግጭቶች ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በተለያዩ አከባቢ ያሉ ተፈናቃዮች የኢትዮጵያ መንግስት እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በተለምዶ (ኦነግ ሸኔ) በታንዛንያ ዳሬሰላም እያካሄዱ ያሉት ድርድር ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል። በሰላም እጦቱ ብዙ ነገር ካፈራንበት ቀዬ ተፈናቅለናል የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ዘላቂ ሰላም የሚሰፍን…
ተፈናቃዮች ስለ ዳሬሰላሙ ድርድር ምን አሉ ?

#1 አስተያየት ሰጪ

" ይኸኛው ድርድር ህዝቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ ያስችለዋል።

ለምሳሌ ካለንበት ቡሬ መድረስ አንችልም አይደለም ቡሬ ጊዳ እንኳን ወጥቶ መመመለስ አንችልም። ከዚህ ጉተን ደርሶ መመለስ አይቻልም ከዚህ 12 እና 13 ኪ/ሜ ርቀት ላይ እንኳን ወጥቶ መግባት አይቻልም።

ወደ እርቅ ከተገባ እና ድርድሩ ከተሰራበት ይሄ ህዝብ ከአዲስ አበባ የሚፈልገውን ገዝቶ ፣ የታመመውም ታክሞ ትምህርት የሚማረውም ትምህርቱን እንዲማር ጥሩ እንቅስቃሴ ይኖረዋል።

በተለይ ወላዶች እየሞቱ ነው። እኛ አካባቢ ሰሞኑን ብቻ 4 ወላዶች ሞተዋል በወሊድ ምክንያት ፤ እናቶች እያየናቸው እየሞቱ ነው። ወስደን የምናሳክምበት የለም። የሚያዋልድ የለም። ሆስፒታል ነቀምት፣ ጊዳ ነው ያለው መሃል ላይ ሸኔ ስላለ በየት በኩል አድርገን እንወስዳለን ? እስከዚህ ድረስ የከፋ ስቃይ አለ።

እነሱ ከታረቁ እንዲህ ያለው ነገር ይቀንሳል። "

#2 አስተያየት ሰጪ

" የኦሮሞ ነፃ አውጭ ድርጅት / ኦነግ ሸኔ እና የኢትዮጵያ መንግሥት እያደረጉ ያሉት ድርድር ማኛውም ኢትዮጵያዊ ደስ ብሎታል።

ይሄ ድርድር ዘላቂነት እንዲኖረውና ስር ሰደድ እንዲሆን ምኞታችን ነው። እንዲሁም የአማራ ህዝባዊ ፋኖ እና የኢትዮጵያ መንግሥት ለህዝባዊ ፋኖ ጥሪ ቀርቦ እንዲሁ ድርድር ቢደረግ ሰላሙ ለወደፊት የተጣራና ጥሩ እንዲሆን ያደርገዋል።

ከዚህ በኃላ እነሱ ተደራድረው ሲመለሱ ተፈናቃዩም ተሳታፊ ቢሆንና አብሮ ቢሳተፍና ቢነጋገር በጣም ደስ ይለናል። ምክንያቱም ይሄ ተፈናቃይ ነው ገፈጣ ቀማሹ ፣ ኃላም ሄዶ አደጋ ላይ የሚወድቀው፣ በፊትም የወደቀው ይኸው ተፈናቃይ ነው ስለዚህ ሰላሙ ዘላቂ እንዲሆን ተፈናቃዩ በተግባር በውይይት ላይ ተሳታፊ ቢሆን መልካም ነው። "

#3 አስተያየት ሰጪ

" ድርድር መስማታችን በጣም ጥሩ ነው።

ያ ውይይት ሀገርም ያረጋጋል። እኛ ሰላም በማጣታችን ነው እዛ ካፈራነው ንብረት የወለድናቸውን ልጆችና የተለያየ ነገር አጥተን ዛሬ ቀን በፀሀይ ማታ ለብርድ ሸራ ውስጥ ያለነው።

ሰላሙ በጣም ትልቅ ነገር ነው ግን ይሄ ነገር ሲታሰብ መንግሥት እና ኦነግ ሸኔ መግባባትና ድርድር ብቻ ሳይሆን ኦሮሚያ ክልል ላይ ብሄር ብሄረሰቦች ይኖራሉ በተለይ 4ቱ ወለጋ ላይ ይታወቃል እሱን ታሳቢ ያደረገና ከግምት ያስገባ ድርስር መሆን አለበት።

ሰው እንዴት እንደሚኖር ፣ ተፋቅሮ፣ አንድ ላይ መብቱ ተከብሮ ፣ የሚፈልገውን አግኝቶ ወጥቶ ገብቶ ሰርቶ እንዲኖር ነው ሰላም የሚያስፈልገው። መቼም አንደኛው ገፍቶ አንደኛው ተገፍቶ እንደማይኖር ይታወቃል ስለዚህ ይህን ከግምት ያስገባ ውይይት እና ድርድር ተደርጎ ኦሮሚያን ሰላም ለማድረግ ከሆነ በጣም ጥሩ ነው። ተስፋ ሰጪ ነው።

ሰላም ከራሳቸው ክልል ነው የሚጀምረው ፣ ከኦነግ ሸኔ ጋር ታርቆ የሚፈልጉትን መፍታት ከቻሉ ያለው ነገር ሊፈታ ይችላል። 

እዛ ኪረሙ አካባቢ ያሉ የሁሉም ወገን ነው የተፈናቀለው ይሄንን እውነት በጥልቀት የሚሰራበት ከሆነ መጀመሪያ ህዝብን መመለስ ሳይሆን አካባቢው በአግባቡ ካረጋጋና ሰላሙ ከተጠበቀለት በኃላ የተፈናቀለና የተጎዳ ህዝብ እንዴት መመለስ እንዳለበት ማቀድና ካስገባም በኃላ ምን ይደርስበታል ? ምን ያስፈልገዋል ? የሚለውን ማሰብ ያስፈልጋል። ድርግም ያለ ሀሳብ መሆን የለበትም። "

#4

" ሰላም በውይይት እንጂ በአፈሙዝ እንደማይመጣ እንረዳለን። እኛ ነገ ከነገ በስቲያ ወደ ኦሮሚያ ክልል ሄዶ የመኖር ነገር ያሰጋናል። ለምን ? ቢባል ከዚህ ቀደም በየቦታው ተሰጋስገን ያለነው። አንድነት የለንም ስለዛ ገፈጣ ቀማሽ ሆነናል። አሁን ደግሞ በየቦታው ሄደን መውደቃችን ያሳስበናል፤ ከመጠን በላይ ። ያው በጠረጴዛ ዙሪያ ተወያይቶ ሰላም እንዲመጣ ሙሉ ተስፋ አለን። "

#5 አስተያየት ሰጪ

" ይሄ ተፈናቃይ ከዚህ የሄደው በእኛ ምክንያት ነው ይሄ ሰላም የሆነው በእኛ ምክንያት ነው ተብሎ ልክ ኦነግ ሸኔና የብልፅግናው ኦሮሚያ ላይ ብቻቸው የሚደራደሩት ብቻ ሳይሆን ይሄ ማህበረሰብ ይሄ ብሄር ብሄረሰብ የተፈናቀለውን ከግምት አስገብቶ ለነሱም ሰላም ያመጣል እነሱም እንደዚህ ሆነው መኖር ይችላሉ ተብሎ ያን ሰላም ለመምጣት የመነጨ ከሆነ ለእኛም ለተፈናቃዮቹ እዛም ለሚኖረው ማህበረሰብ ተስፋ አለው ጥሩ ነገር ያመጣል።

ግን የኦነግ ሰራዊት እና የመከላከያ ሰራዊት  ብቻ በመታረቅ ምንም የሚመጣ ፋይዳ አለ ብዬ አላስብም። ሲቪልም ያማከለ ከሆነ ውስጥ ላይ ወርዶ የሚከታተሉ ከሆነ እዚህ ላይ ትልቁን ሚና ይጫወቱታል ብዬ አስባለሁ። "

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት እነ ቀሲስ በላይ መኮንን ፖሊስ ጣቢያ እንዲቆዩ አዟል።

በዋስ ጥያቄያቸው ዛሬም ውድቅ ተደርጓል።

ቀሲስ በላይ መኮንን በችሎቱ ፥ " ፖሊስ ይዞኝ ሳይሆን እራሴ ነው የሄድኩት " ብለዋል፡፡

" #ብዙ_የሀገር_ጉዳይ በእጄ ስላሉ ጥፋ ብባል እንኳ የምጠፋ ስላልሆንኩ ፤ በጤናዬ ላይ በደረሰው እክልና በቤተሰቦቼ ላይ በደረሰው ችግር ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብት ይጠብቅልኝ " ሲሉ ጠይቀዋል።

የብዙ ልጆች አሳዳጊና የቤተሰብ አስተዳዳሪ እንደሆኑ ጠቅሰው በዋስ ከእስር እንዲወጡ ጠይቀው ነበር።

ፍርድ ቤት ግን ሁሉም ተከሳሾች በፖሊስ ጣቢያ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ አዟል።

ቀሲስ በላይ መኮንን በሀሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ላይ #ከ6_ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማውጣት ሙከራ አድርገዋል ተብለው አብረዋቸው ከነበሩት ሰዎች ጭምር መታሰራቸው አይዘነጋም።

ያንብቡ : https://telegra.ph/DW-05-20 #ዶቼቨለ

@tikvahethiopia