TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሁንም ጥንቃቄ📌 ከዝህ በፊት ብያለሁ። አሁንም ደግሜ እላለሁ! ከትናንሽ አጀንዳዎች እንዉጣ። ስለ ምልክት ሳይሆን ስለሀገር ከልብ እናስብ! #ሀገር ካለች #ባንዲራ መስቀል እና #ሀዉልት መገንባት አይከብድም! ሀገር #ከሌለ ግን ባንዲራ ብቻዉን ትርጉም የለዉም! አሁን #ሊቢያ ወይም #የመን ላይ ባንዲራ መያዝ ወይም ሀዉልት መትከል ምን ያደርጋል? ችግራችን በባንዲራ ወይም በሀዉልት አይፈታም። የግጭት ነጋዴዎችን ሴራ እናክሽፍ።

ጆሮ ያለዉ ይስማ!
.
.
Ammas of eeggannoo📌

Kanaan duras jedheera. Ammas irran deebi'a! Ajandaa xixinnoo keessaa haa baanu. Waan mallattoo dhiifnee waan biyyaa onnee irraa haa yaannu! Biyyi yoo jiraatte alaabaa fannisuu fi siidaa dhaabuun hin dhibu. Yoo biyyi hin jirre garuu alaabaan qophaatti hiika hin qabu! Amma #Liibiyaa ykn #Yemen keessatti alaabaaqabatuun ykn siidaa dhaabuun maal godha? Rakkoon keenya alaabaa ykn siidaan hin hiikkatu! Shira diinaa haa fashalsinu!

Dubbii kana qalbisaa!

©አቶ ታዬ ደንደአ (የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሁንም ጥንቃቄ📌 ከዝህ በፊት ብያለሁ። አሁንም ደግሜ እላለሁ! ከትናንሽ አጀንዳዎች እንዉጣ። ስለ ምልክት ሳይሆን ስለሀገር ከልብ እናስብ! #ሀገር ካለች #ባንዲራ መስቀል እና #ሀዉልት መገንባት አይከብድም! ሀገር #ከሌለ ግን ባንዲራ ብቻዉን ትርጉም የለዉም! አሁን #ሊቢያ ወይም #የመን ላይ ባንዲራ መያዝ ወይም ሀዉልት መትከል ምን ያደርጋል? ችግራችን በባንዲራ ወይም በሀዉልት አይፈታም። የግጭት ነጋዴዎችን ሴራ እናክሽፍ።

ጆሮ ያለዉ ይስማ!
.
.
Ammas of eeggannoo📌

Kanaan duras jedheera. Ammas irran deebi'a! Ajandaa xixinnoo keessaa haa baanu. Waan mallattoo dhiifnee waan biyyaa onnee irraa haa yaannu! Biyyi yoo jiraatte alaabaa fannisuu fi siidaa dhaabuun hin dhibu. Yoo biyyi hin jirre garuu alaabaan qophaatti hiika hin qabu! Amma #Liibiyaa ykn #Yemen keessatti alaabaaqabatuun ykn siidaa dhaabuun maal godha? Rakkoon keenya alaabaa ykn siidaan hin hiikkatu! Shira diinaa haa fashalsinu!

Dubbii kana qalbisaa!

©አቶ ታዬ ደንደአ (የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📷የመን ከጦርነት በፊትና ከጦርነት በኃላ! #YEMEN
•መምህራን ለሁለት ዓመት ደሞዝ አልተከፈላቸውም!
•3.7 ሚሊየን ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጭ የመሆን ስጋት ተደቅኖባቸዋል!


#YEMEN

ጦርነት ባልተለያት የመን ውስጥ የሚገኙ ሁለት ሚሊየን ህፃናት ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸውን የተባበሩት መንግሥታት የህፃናት መርጃ ድርጅት(ዩኒሴፍ) አስታውቋል። ከእነዚህም ውስጥ አንድ አራተኛ የሚሆኑት ከፈረንጆቹ 2015 መጋቢት 2 ጀምሮ ትምህርታቸውን ያቋረጡ መሆናቸውን ገልጿል። #ዩኒሴፍ ባወጣው መግለጫ መምህራን ለሁለት ዓመታት ደመወዝ አለማግኘታቸውን ተከትሎ ሌሎች 3.7 ሚሊየን ህጻናትም ከትምህርት ገበታ ውጭ የመሆን ስጋት ተደቅኖባቸዋል።

በትምህርት ቤቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች፣ መፈናቀል እና ግጭቶች ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ ያደረጉ ምክንያቶች ናቸው ሲሉ በየመን የዩኒሴፍ ተወካይ ሳራ ቤይሶሎ ኛታኒ ተናግረዋል። የህጻናቱ ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆን ልጆች ወደ ጦርነት እንዲገቡ መገደድና ለሌሎች ጫና እየተዳረጉ መሆኑንም ነው የጠቆሙት። እንደ ዩኒሴፍ መረጃ እድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ 1.8 ሚሊየን ህፃናት ለተመጣጠነ ምግብ እጥረት ተጋልጠዋል።

ምንጭ፦ አል ጀዚራ/በENA ይቀረበ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#YEMEN

በሰሜናዊ የመን ሳዳ ግዛት በአንድ ገበያ ላይ በተፈጸመ ጥቃት አስራ ሁለት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ጨምሮ አስራ ሰባት ሰዎች መገደላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ። ጥቃቱ የሑቲዎች ጠንካራ ይዞታ በሆነው የሳዳ ግዛት በሚገኝ አል-ራቅው የተባለ ገበያ ላይ የተፈጸመው ባለፈው ማክሰኞ ነበር። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሌሎች አስራ ሁለት ሰዎች ለቆሰሉበት ጥቃት ተጠያቂ ያደረገው ወገን የለም።

(DW)
@tikvahethiopiaBot @tikavhethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Yemen

አዲስ የተመሰረተውን የየመን መንግስት ከሳዑዲ አረቢያ ጭኖ የነበረ አውሮፕላን ካረፋ ከጥቂት ቆይታ በኋላ በኤደን አየር መንግድ ተኩስና ፍንዳታ መከሰቱን ሮይተርስ ዘግቧል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ማአን አብዱልማሊክን ጨምሮ የካቢኔ አባላት ወደ ቤተመንግስት በሰላም መድረሳቸው ተዘግቧል፡፡

በፍንዳታው የደረሰው ጉዳት እስካሁን አለመታወቁን ዘገባው ጠቅሷል፡፡

የመን ውስጥ የእርስ በእርስ ግጭት ከተከሰተ በኋላ በሺዎች የሚቆጠሩ የመናውያን ለስደት እንዲሁም ለሞት ተዳርገዋል፡፡

Via #AlAIN / Reuters / Hesmat Alavi
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#Yemen : የሞት ፍርድ !

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዜዳንት እና የሳውዲው ልዑል በሌሉበት የሞት ፍርድ ተፈረደባቸው።

በየመን የሑቲ ታጣቂዎች ፍርድ ቤት የአሜሪካውን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕንና የሳኡዲውን ልዑል መሐመድ ቢን ሳልማንን በሌሉበት ሞት ፈረደውባቸዋል።

ፍርድ ቤቱ በነዶናልድ ትራምፕ መዝገብ ተከሰው የነበሩ ዘጠኝ ሰዎች ከትናንት በስቲያ በአደባባይ በሞት ቀጥቷቸዋል፡፡

በሞት ከተቀጡት ዘጠኝ ሰዎች መሀል በሚያዝበት ወቅት አዳጊ የነበረ አንድ ልጅ ይገኝበታል፡፡

በሰንዓ አደባባይ ላይ በመቺ ኃይል ከጀርባ እየተተኮሰባቸው እንዲገደሉ የተደረጉት ዘጠኝ የመናዊያን በ2018 አንድ ከፍተኛ የሑቲ አመራርን በሳኡዲ መራሹ ኃይል የአየር ጥቃት እንዲገደል መረጃ አቀብላችኋል በሚል ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው ናቸው፡፡

7ኛው ተከሳሽ የሳኡዲው ልኡል መሐመድ ቢን ሰልማን እና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሌሉበት ሞት ተፈርዶባቸዋል፡፡

9ኙ ሰዎች የተገደሉት በሰንአ ታህሪር አደባባይ ሕዝብ በተሰበሰበበት ነበር፡፡

ተመድ ይህን የአደባባይ ግድያ በጥብቅ ያወገዘ ሲሆን አሜሪካ ፣ ዩኬ ፣ እንዲሁም የአውሮጳ ኅብረት ድርጊቱን ኮንነዋል፡፡

ተመድ የፍርድ ሂደቱ ዓለም አቀፍ ደረጃን የማያሟላ ነበር ሲል ፤ አሜሪካ ደግሞ የተፈፀመድን ድርጊት አሳፋሪ ብላዋለች፤ የአውሮጳ ኅብረት በበኩሉ ቅጣቱ ኢሰብአዊና ነውረኛ ብሎታል፡፡

Credit : BBC

@tikvahethiopia
#Yemen

በአብዛኞቹ #ኢትዮጵያውያን የሆኑ ስደተኞችን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ከየመን የባሕር ዳርቻ አቅራቢያ ተገልብጣ 39 ሰዎች ሞቱ።

እንደ IOM እና ከአደጋው ከተረፉ ሰዎች በተገኘ መረጃ ጀልባዋ 260 የሚጠጉ ሰዎችን አሳፍራ የነበር።

በካባድ ነፋስ ምክንያት መገልበጧ ተጠቁሟል።

መሞታቸው ከታወቀው 39 ሰዎች ውጪ ሌሎች 150 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም። እነሱን ለማግኘት ፍለጋ እየተደረገ ነው።

71 ሰዎች ከአደጋው ተርፈዋል።

የሩደም አካባቢ ባለሥልጣናት ጀልባዋ ላይ ተሳፈረው ከነበሩት 260 ስደተኞች በአብዛኞቹ #ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንደነበሩ አመልክተዋል።

#Reuters #IOMYemen #IOMspokesperson

@tikvahethiopia