TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" 41 የጸጥታ አካላት ከኃላፊነታቸው #ተነስተዋል " - አቶ ሀሚድ አህመድ

ከሰሞኑን በሲዳማ ክልል ፤ የጸጥታ አካላት የግምገማ መድረክ ሲካሄድ መሰንበቱ ተነግሯል።

ይህን ተከትሎ " ለህዝብ ሳይሆን ለራሳቸዉ ቆመዋል " የተባሉ አመራሮች ከስልጣን መነሳታቸው ተገልጿል።

የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሀሚድ አህመድ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " የተጣለባቸውን የስራ ኃላፊነት በአግባቡ ያልተወጡ በተለይ ህዝብን #ሲያማርሩ እና #ሲያሰቃዩ እንዲሁም የሀገርን ሀብት ሲዘርፉ የነበሩ 41 የፀጥታ አካላት ተነስተዋል " ብለዋል።

በቀጣይ ለፍርድ እንደሚቀርቡ ገልጸዋል።

#በታችኛው_እርከን ላይ ያሉ የጸጥታ አመራሮች ላይም አስተዳደራዊ እርምጃ ይቀጥላል ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ 291 ከፍተኛ አመራሮች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸዉ ገልጸዋል።

ለመሆኑ እነማን ናቸው ከኃላፊነት የተነሱት ? በማለት ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ ዳይሬክተሩ ፤ " አሁን ላይ መግለጽ የምችለው ብዛታቸዉን ብቻ ነው። " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

" በቀጣይ ቀናት ማንነታቸውን እናሳውቃችኋለን " ሲሉ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
" ... ወንዶች በትምህርት ሰአት ሁሉ የቀን ስራ በመስራት ርሀባቸውን ለማስታገስ በጥረት ላይ ሲሆኑ ሴቶችም ላልተገባ ችግር ተጋልጠዉ መማር አልቻሉም " - የደቡብ ኢትዮጵያ መምህራን ማህበር

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር አደረኩት ባለው ማጣራት በክልሉ ውስጥ ባሉት የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ለመማር የተመደቡ ዕጩ መምህራን ሁሉም በሚባል መልኩ  ትምህርታቸውን በፋይናንስ እጥረት በአግባቡ እየተማሩ አይደለም።

ዕጩ መምህራን በ2015 ዓ/ም ወደ ኮሌጆች ሲገቡ ከመንግስት የሚሰጣቸዉ 450 ብር በቂ እንዳልሆነ እየታወቀ ቢጀመርም እስካሁን ሊስተካከልላቸው አልቻለም።

ይህን ችግር በተመለከተ ኮሌጆቹ በቦርድ ደረጃ ያመኑበት ከመሆኑ ባለፈ ማስተካከያ እንዲደረግ ለክልሉ መንግስት ጥያቄ ሲያቀርቡ ቆይተዋል።

ይሁንና የክልሉ መንግስት ለጥያቄው ተገቢ ምላሽ ባለመስጠቱ በክልሉ በተለያዬ ደረጃ የመምህራንነት ስልጠና ለመዉሰድ ወደኮሌጆች ገብተዉ በትምህርት ላይ የሚገኙ በርካታ ዕጩ መምህራን በችግር እየተጠበሱና ትምህርታቸዉን ትተዉ ወደመጡበት እየተመለሱ መሆናቸዉን የክልሉ መምህራን ማህበር አውቂያለሁ ብሏል።

የመምህራን ማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ አማኑኤል ጳዉሎስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ፤ " ከነዚህ ተማሪዎች መካከል አብዛኛዉ ወንዶች በትምህርት ሰአት ሁሉ የቀን ስራ በመስራት ርሀባቸውን ለማስታገስ በጥረት ላይ ሲሆኑ  ሴቶችም ላልተገባ ችግር ተጋልጠዉ መማር አልቻሉም " ብለዋል።

" በመሆኑም ተማሪዎች በ450 ብር በልተዉና ጠጥተዉ እንዲሁም ሌሎች ወጭዎችን ሸፍነዉ  መማር አይችሉምና የክልሉ መንግስት በተለይም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ባስቸኳይ ችግራቸዉን ይፈታላቸዉ ዘንድ ማህበሩ በደብዳቤ ሁሉ ጠይቋል " ሲሉ ተናግረዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ስለምን ተማሪዎቹ በዚህ ልክ እስኪሰቃዩ ድረስ መፍትሄ አልተፈለገም ? በማለት ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነዉ ጥረት አልተሳካም።

ምላሽ ሲሰጥ ምላሹን የምናካትት ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
" እጆቼን ማዘዝ ችዬ እኔን ለማገዝ የሚደክሙትን ሁሉ ከድካማቸዉ ባሳርፋቸዉ  ደስ ይለኝ ነበር " - ጠንካራው የይቅርታ ሰዉ ዳግማዊ አሰፋ (ዳጊ)

የህግ ባለሞያና ደራሲ ዳግማዊ አሰፋ ከዓመታት በፊት በሀዋሳ ከተማ በእሱ እና በጓደኛው እጅ ላይ ከነበረ የፍትህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ " ጉቦ አንቀበልም !! " በማለቱ በአንድ ግለሰብ በጥይት ተመቶ መጎዳቱ ይታወሳል።

በዚህ አደጋ ጠንካራ የወጣት እጆቹ አልታዘዝልህ ብለዉታል። በአከርካሪዉ ዙሪያ ያሉ ነርቮች መጎዳትም ቆሞ እንዳይሄድ እንቅፋት ሆነዉበታል።

በዚህ ምክኒያት በሰው እጅ መብላቱ መልበሱ እና መንቀሳቀሱ ፈተና ቢሆንበትም ዛሬም ተስፋው ከሱ አልፎ ለሰዎች ይደርሳል።

ያልተሰበረው መንፈሱ የተሰበሩትን ይጠግናል ፤ ያልወደቀው ምራሉም የወደቁትን ያነሳል።

በዚህ ትጋቱ ያልተገታዉ ዳግማዊ ከህመሙ ጋር እየታገለ ስቃዩን እየተሰቃዬም ቢሆን አርፎ መቀመጥን አልወደደም ሁለት መጽሀፍት ለተደራሲያን አብቅቶ ለብዙዎች ህይዎት መቃናት ምክኒያት ሆኗል።

በዚህ ዓመትም ሌላ መጽሀፍ ሊያስመርቅ እየሰራ ነው። የቀደሙ ሁለቱ መጽሀፍትም በአፋን ኦሮሞ ታትመዉ ለመዉጣት ጫፍ መድረሳቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ከምንም በላይ ለሰዎች መትረፍ ሲችል የሰዎችን ድጋፍ ይፈልግ ዘንድ ብርቱ ክንዶቹ ዝለው ስራዎቹን መከወን ያቅታቸው ዘንድ ምክኒያት የሆነውን ሰው " ይቅር ብየሀለሁ " ማለቱ ለትንንሽ ጥፋት ይቅርታ ማድረግ ለከበዳቸዉ ሁሉ ታላቅ ትምህርት የሰጠ ሰው ነው።

ጠንካራው ዳግማዊ ከሁለት ዓመት በፊት ውጭ ወጥቶ መታከም ከቻለ መዳን እንደሚችል ሀኪሞች ማብሰራቸውን ተከትሎ በርካታ ወዳጆቹ ተደስተዉ ጎ ፈንድሚ ቢያቋቁሙም ወቅቱ ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዘ ሀገራችን ችግር ላይ የነበረችበት ወቅት  በመሆኑ እንዳስቆመው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበረው ቆይታ ተናግሯል።

" አሁን ላይ  ' ጎፈንድሚውን እንጀምር  ዘንድ ፈቃድህን ብቻ ስጠን 'ላሉኝ ጓደኞቼ ፈቃዴን ሰጥቻለሁ "  ብሏል።

ድኖ ለብዙዎች መትረፍ ሲችል ' ሀገሬ ችግር ላይ ናት " ብሎ የዘገየዉ ዳግማዊ ምንም እንኳን ብዙ ችግሮቹን " ወዳጆቼን አላስጨንቅም " ብሎ ቢደብቅም በቶሎ መታከም እንዳለበት ግን አሁን ላይ ብዙ ምልክቶችን አሳይቷል።

ይህ ተከትሎም ሁሉም ደጋግ ኢትዮጵያውያን እገዛ እንዲያደርግለት ወዳጆቹ እየተረባረቡ ይገኛሉ።

ዳግማዊ ፥ " ' 2 ሺህ የፌስቡክ ጓደኞቻችን ሁለት ሁለት መቶ ሰው ይዘዉ የአንድ ማኪያቶ የሚሆን 57 ብር በማዉጣት ያሳክሙሀል ' ብሎ ወዳጄ መምህር ወሌ ሀሳቡን ጀምሮታል " ብሏል።

" ዳግማዊ ገንዘቡ ተሰብስቦልህ ታክመህ ስትድን በእጆችህ ቀድመህ ልትሰራ የምታስበዉ ምንድን ነው ? " በማለት የቲክቫህ ሀዋሳ ቤተሰብ አባል ጥያቄ አቅርቧል።

ከረዥም ዝምታ በኋላ ፦

" አይገርምህም አስቤዉ አላዉቅም ... ግን እጆቼን ማዘዝ ችዬ እኔን ለማገዝ የሚደክሙትን ሁሉ ከድካማቸዉ ባሳርፋቸዉ  ደስ ይለኝ ነበር። "

ዳግማዊ አሰፋን ማገዝ የምትፈልጉ በሀገር ውስጥ ሆነ በውጭ ያላችሁ ደጋግ ኢትዮጵያዉያን ፦
በጎፈንድሚ 👉 https://gofund.me/d93d0840
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 👉1000310977938
በዳሽን ባንክ 👉 5016527877077
በአቢሲንያ ባንክ 👉 39796821 በኩል ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ።

ስልክ እንፈልጋለን ለምትሉም ፦ 0909888857 ላይ መደወል ትችላላችሁ።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
“ ባለፈው ሳምንት ብቻ 7 ሰዎች ናቸው የተገደሉት ” - ነዋሪዎች በኮሬ ዞን ፤ #በታጣቂዎች አማካኝነት ንጹሃን ላይ የሚደርስ ጥቃት በእርቀ ሰላም ተፈቶ ቆሞ የነበረ ቢሆንም ከ4 ወራት ወዲህ በማገርሸቱ የንጹሐን ግድያ፣ የንብረት ዘረፋ እየተፈጸመ መሆኑን የዞኑ ባለስልጣትና ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። መንግሥት መፍትሄ እንዲሰጥም ተጠይቋል። ባለስልጣናቱና ነዋሪዎቹ ለድርጊቱ  የ " ኦነግ…
#ኮሬ

° " የንጹሀን ሞት ይቁም፤ገዳዮች ለፍትህ ይቅረቡልን !! " - የዳኖ ቀበሌ ነዋሪዎች

° " በግጭቱ ሁለት ሰዎች ሲጎዱ የአንደኛው ህይዎቱ አልፏል " - የኮሬ ዞን የሰላምና ጸጥታ ሀላፊዉ ተፈራ ቦንዶሮ

በኮሬ ዞን ፤ ዳኖ ቀበሌ ከትናንት ጀምሮ የደረሰ በቆሎ ታጥቀው በመጡ አካላት በመጨፍጨፉ ምክንያት በተነሳው ግጭት የሰው ህይወት አልፏል።

የአካባቢው ነዋሪዎች ይህ ድርጊት ታጥቀው ከምዕራብ ጉጂ ዞን ጋላናና ሱሮ ባርጉዳ ወረዳ ቀበሌያት ወደ ኮሬ ዞን ዘልቀው በገቡ አካላት ነው የተፈጸመው ብለዋል።

እነዚሁ ታጣቂዎች " ከዚህ ቀደምም ከብቶች ሲነዱብን አርሶአደሮች ሲገደሉብን ቆይተዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

በዚህ አመት ብቻ #ከ20_በላይ ሰዎች መሞታቸውን አስረድተዋል።

በመሆኑም " እነዚህን አካላት መንግስት አስታግሶ ለህግ / ለፍትህ ያቅርብልን ፤ የንጹሀን ሞት ይቁም ፤ ሰሚ በማጣታችን እሄዉ ዛሬም ግጭቱ ቀጥሏል " ብለዋል።

በአካባቢው ያለዉ ተኩስም የታጠቁ አካላትን ወሰን አልፈዉና ወደመንደሩ ተጠግተዉ የጀመሩት ነው ሲሉ አስረድተዋል።

ይህን ጉዳይ በተመለከተ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የኮሬ ዞን የሰላምና ጸጥታ ሀላፊዉ ተፈራ ቦንዶሮ ፥ (ቃላቸውን በሰጡበት ሰዓት / ከሰዓት ) አካባቢው ላይ ከባድ ተኩስ እንደነበር ገልጸዋል።

ግጭቱን ለማርገብ ርብርብ ላይ በመሆናቸዉ ምላሽ ለመስጠት አይመችም ቢሉም ቆይተዉ የተብራራ ምላሽ ሰጥተዋል።

ከምዕራብ ጉጂ ዞን የመጡ ታጣቂ ሀይሎች አካባቢው በመመንጠርና የበቆሎ ማሳዎችን በመጨፍጨፋቸው ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር ግጭት ውስጥ መግባታቸውን ገልጸዋል።

በግጭቱ አንድ ሰው #ሲሞት ፤ አንድ ሰው ቆስሏል ብለወል።

ግጭቱን በቀሰቀሱት በኩል የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ የሚያዉቁት ነገር እንደሌለ ገልጸው አሁን ላይ አካባቢዉ መረጋጋቱን ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለዘላቂ ሰላም ምን ታስቧል ? ሲል ጠይቋል።

እሳቸውም ፤ ከአካባቢው በተወሰነ ርቀት ላይ የሀገር መከላከያ ሀይሎች እንደሚኖሩና ከሚቆጣጠሩት ቦታ በተጨማሪ የታጠቁ ሀይሎች የሚመጡበትን መንገድ እንዲቆጣጠሩ ለመነጋገር ማሰባቸዉን ገልጸዉ ይህ ግን በመከላከያው ፈቃድና የስምሪት ሁኔታ የሚወሰን ነው ብለዋል።

ግጭቱ ያለበት የኮሬና ጉጂ ማህበረሰብ መሀከል በአካባቢዉ ባህል መሰረት የእርቅ ስርዓት በተደጋጋሚ ቢካሄድም ዕርቁ ውጤታማ ሳይሆን መቅረቱን ለማወቅ ችለናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ በምዕራብ ጉጂ ዞን በኩል ምላሽ ለማግኘት ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካም ፤ ከዚህ ቀደምም ሙከራ ቢደረግም ምላሽ ሰጪ አልተገኘም። አሁንም ምላሽ አለኝ የሚል ምላሹን መስጠት ይችላል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ... ወንዶች በትምህርት ሰአት ሁሉ የቀን ስራ በመስራት ርሀባቸውን ለማስታገስ በጥረት ላይ ሲሆኑ ሴቶችም ላልተገባ ችግር ተጋልጠዉ መማር አልቻሉም " - የደቡብ ኢትዮጵያ መምህራን ማህበር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር አደረኩት ባለው ማጣራት በክልሉ ውስጥ ባሉት የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ለመማር የተመደቡ ዕጩ መምህራን ሁሉም በሚባል መልኩ  ትምህርታቸውን በፋይናንስ እጥረት በአግባቡ እየተማሩ…
" ችግሩ በሚባለዉ ደረጃ የተጋነነ ባይሆንም ጊዜያዊ እርምጃ ለመዉሰድ እንቅስቃሴ ጀምሬያለሁ " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ

ከሰሞኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባሉ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ለመማር የተመደቡ ዕጩ መምህራን ሁሉም በሚባል መልኩ ትምህርታቸዉን በፋይናንስ እጥረት እየተማሩ አለመሆኑን የደቡብ ኢትዬጵያ ክልል መምህራን ማህበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል።

ወንዶች ትምህርት መማር ሲገባቸው የቀን ስራ እየሰሩ እንደሆነና ሴቶችም ላልተፈለገ ችግር መጋለጣቸውን ጠቁሞ ነበር።

ተማሪዎቹ በ2015 ዓ/ም ወደ ኮሌጆች ሲገቡ ከመንግስት የሚሰጣቸዉ 450 ብር በቂ እንዳልሆነ እየታወቀ ቢጀመርም እስካሁን አለመስተካከሉንና ለዚህም በተከታታይ ደብዳቤ መጠየቁን ማህበሩ መግለጹ አይዘነጋም።

ጉዳዩን በተመለከተ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስተያየቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥቷል።

የቢሮው ምክትል ሀላፊ ዶ/ር ታምራት ይገዙ ፤ " ጉዳዩ በተባለዉ ልክ የተጋነነ ባይሆንም የተወሰነ ችግር መኖሩን አውቀን እየሰራንበት ነው " ብለዋል።

" ለችግሩ የአጭር ጊዜ መፍትሄ ለመስጠት እንቅስቃሴ ጀምረናል " ያሉት ሀላፊው " አሁን ላይ ተማሪዎቹ ያለባቸዉን የቤት ኪራይ ችግር ለማቅለል ከዲላ እና ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መነጋገር ጀምረናል " ብለዋል።

ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ጋር ጥሩ መግባባት ላይ መደረሱን የገለጹት ዶ/ር ታምራት ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋርም ሂደቱ ጥሩ መሆኑን አመልክተዋል።

" በቋሚነት ችግሩን ለማስተካከል እየሰራን ነው። ምናልባትም ለሚቀጥለዉ አመት ሲመጡ የሚከፈላቸዉ ገንዘብም ይጨምራል ብዬ አስባለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
#Hawassa

➡️ " ንፋስ በመጣ ቁጥር ጉዳት እየደረሰ ነው። እሮብ የአንድ ሰው ህይወት አልፏል " - የሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል

➡️ " ጉዳት የደረሰበት የካፌ አስተናጋጅ ነው። በወቅቱ ወደህክምና ተወስዶ የህክምና እርዳታ ቢደረግለትም ህይወቱ ግን ሊተርፍ አልቻልም " - የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ

በሀዋሳ ከተማ ፤ ፒያሳ በሚገኘው ንብ ባንክ ህንጻ ላይ የወደቀ መስታወት የአንድ ወጣት ህይወት ቀጥፏል።

ህንጻው በዝናብና ንፋስ ወቅት እቃ ሲወድቅበት የመጀመሪያው እንዳልሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሀዋሳ የቤተሰብ አባላቱ ጥቆማ ደርሶታል።

በቅርቡ የተመረቀዉ የንብ ህንጻ ከዘጠነኛ ፎቅ ላይ የወደቀ መስታወት የህንጻው ወለል ላይ ስራ ላይ የነበረ ሰራተኛ ላይ ማረፉን ተከትሎ ሰራተኛው ህይወቱ አልፏል።

በሀዋሳ እሮብ ከ9 ሰአት በኋላ የነበረው ከባድ ዝናብና ውሽንፍር ባስከተለዉ ነፋስ ከህንጻዉ ላይ የወደቀ መስታወት የሰዉ ህይወት ማጥፋቱን ለማረጋገጥ ችለናል።

አንድ የሀዋሳ የቤተሰባች አባል ፤ " ንፋስ በመጣ ቁጥር ከህንጻው ላይ በሚወድቅ ቁስ ተደጋጋሚ ጉዳት በግለሰቦች ላይ ሰራተኞች ላይ እየደረሰ ነው። እሮብ አንድ ሰራተኛ መስታወት ወድቆበት እጁ የመቆረጥ ፣ አናቱ ላይ የመጎዳት በኃላም ህይወቱ አልፏል። ህንጸው ግልጽ የሆነ የግንባታ ጉድለት ይታይበታል " ሲል ቃሉን ሰጥቷል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የሰጡት የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ ወንድማገኝ ቶርባ ፤ ጉዳት የደረሰበት ወጣት የካፌ አስተናጋጅ መሆኑንና በወቅቱ ወደህክምና ተወስዶ የህክምና እርዳታ ቢደረግለትም ህይወቱ ግን ሊተርፍ እንዳልቻለ ገልጸዋል።

ይሁንና " ህንጻው ላይ ተደጋጋሚ ችግር ተስተውሏል " ለሚባለዉ ቅሬታ ካሁን በፊት የደረሰ አደጋን የተመለከተ ሪፖርት የለም ሲሉ ገልጸዋል።

በወቅቱ በዚህ ህንጻ ውስጥ ከደረሰዉ አደጋ  ውጭ በከተማዉ የተከሰተዉ ነፋስ በርካታ የንብረት ጉዳት ማስከተሉንም አስታውሰዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የህንጻዉን አስተዳዳሪዎች በጉዳዩ ዙሪያ ለማነጋገር ያደረገዉ ሙከራ አልተሳካም። ምላሽ አለም ካሉ መስተናገድ ይችላሉ።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#SouthEthiopiaRegion በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፤ የሶዶ ዙሪያ ወረዳ የመንግሥት ሠራተኞች ለወራት ያልተከፈለ ውዝፍ ደሞዛቸዉ እንዲሰጣቸዉ በአደባባይ ሠልፍ ጠይቀዋል። በዎላይታ ሶዶ ከተማ በሚገኘው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና የብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የግቢ በሮች ላይ የተሰበሰቡት ሠራተኞች እንደገለጹት እስከ 3 ወራት የሚደርስ ደሞዝ አልተከፈላቸዉም። ሠራተኞቹ ደሞዝ ሥላልተከፈላቸዉ እራሳቸዉንና…
#SouthEthiopiaRegion

➡️ " ... በረሀብ ከምንሞት መብታችን እየጠየቅን አደባባይ ላይ መሞት መርጠን ነው ወደ ርእሰ መስተዳድሩ ቢሮ የሄድነው " - የሶዶ ዙሪያ የመንግስት ሰራተኞች

➡️" ማንም መብቱን በነጻነት የመጠየቅ መብት አለው " - የደቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃፊዉ አቶ ወገኔ ብዙነህ

የ2 ወራት ደሞዛችን ይከፈለን ያሉ የወላይታ ዞን የመንግስት ሰራተኞች አደባባይ መውጣታቸዉን ተከትሎ  በርካታ ያልጠበቋቸዉ ጉዳዮች እንደገጠሟቸዉ ገልጸዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ሰራተኞች ፥ " ጥያቄያችን ለመጠየቅ የተገደድነዉ ረሀቡ ስለጠናብን ነው " በማለት ላለፉት ወራት ከፍተኛ ችግር ውስጥ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

አሁን ላይ ደሞዝ ከወሰድን 2 ወራችን ነዉ የሚሉት ሰራተኞቹ ከዚያ በፊትም በፐርሰንት እየተቆራረጠ ይሰጥ የነበረው ደሞዝ የማንወጣው እዳ ውስጥ አስገብቶን ነበር ብለዋል።

" በፐርሰንት ሲከፈለን በነበረበት ወቅት ችግሩን ለመቋቋም አበዳሪ ተቋማት ጋር ሂደን የምንበደረው ገንዘብ ወለዱ አሰቸጋሪ መሆኑ ሳያንስ ደሞዝ ሲቀርብን ደግሞ ሌላ ጣጣ ውስጥ ገባን " በማለት የችግራቸዉን ውስብስብነት አስረድተዋል።

" በዚህ ምክንያት በረሀብ ከምንሞት መብታችን እየጠየቅን አደባባይ ላይ መሞት መርጠን ነው ወደ ርእሰ መስተዳድሩ ቢሮ የሄድነዉ " በማለት ተናግረዋል።

ሰራተኞቹ " እስካሁን በየደረጃዉ የነበሩ የመንግስት አካላትን ስንጠይቅ ውክቢያና ማስፈራራት ነበር የሚገጥመን በተለይም መጀመሪያ ወደ ዞን አስተዳዳሪ ስናመራ ፖሊስ በትኖን መልሰን መሰባሰብ ሁሉ ከብዶን ነበር " ብለዋል።

" በመጨረሻ ወደ ርእሰ መስተዳድሩ ቢሮ ስንሄድ ሌላዉ ቢቀር ሀሳባችን ሰምተዉ አካሄዱን በማስረዳት ሀሳባችን በደብዳቤ እንድንገልጽ ፈቅደዉልናል " ብለዋል።

" ይሁንና አሁንም ጥያቄያችን ምላሽ አላገኘም " የሚሉት ሰራተኞቹ ተመልሰን ጥያቄያችን የት ደረሰ እንዳንልም ስላልተደራጀን በየጊዜዉ መሰባሰቡ ከበደን ብለዋል።

በመጀመሪያዉ ቀን የሰላማዊ ሰልፍ ሙከራ "  ፖሊስ ሰራተኛዉን በትኗል " መባሉን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊዉ አቶ ወገኔ ብዙነህ በጉዳዩ ሰራተኛዉ ጥያቄ መጠየቁን እንጅ ከፖሊስ ጋር ግጭት እንደገባ መረጃ እንደሌላቸዉ ገልጸዋል።

ያም ሆኖ " ማንም መብቱን በነጻነት የመጠየቅ መብት አለው " ሲሉ ገልጸው " ችግሮች ተከስተዉ ከሆነ ወደፊት መረጃ እንሰጣችኋለን " ሲሉ ቃል ገብተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" እኛም በተፈጠረው በጣም አዝናል ፤ ነገር ግን ተደጋጋሚ የሚባለው ፍፁም ትክክል አይደለም " - ሀዋሳ የሚገኘው የንብ ባንክ ህንጻ

ረቡዕ በሀዋሳ ከተማ በነበረው ንፋስ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ ወቅት ፒያሳ ከሚገኘው የንብ ባንክ ህንጻ ላይ ወደታች የወደቀ መስታወት የአንድ ወጣት የካፌ አስተናጋጅን ህይወት ቀጥፏል።

ጉዳዩን በተመለከተ ጥቆማ እየሰጡ አንድ የሀዋሳ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ፤ ችግሩ ተደጋጋሞ ይከሰታል የሚል ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

የሀዋሳ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፥ እሮብ ከህንጻው በወደቀ መስታወት አንድ ወጣት የካፌ አስተናጋጅ ተጎድቶ ሆስፒታል ቢወሰድም ህይወቱ ሊተርፍ እንዳልቻለ አረጋግጦ ነበር።

ነገር ግን " ተደጋጋሚ ችግር አለ " ለሚባለው ቅሬታ " ምንም አይነት የደረሰ አደጋን የሚመለከት ሪፖርት ከዚህ ቀደም እንዳልመጣለት አሳውቋል።

ዛሬ ህንጻው አስተዳደር ክፍል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ ሰጥቷል።

አንድ ቃላቸውን የሰጡ አካል ፤ እሮብ የተፈጠረው ትክክል ስለመሆኑ ማረጋገጫ ሰጥተው በተፈጠረው ነገር ሁሉም እጅግ ማዘኑን ገልጸዋል።

ነገር ግን " ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ ችግር ተስተውሏል " የሚለው ፍጹም ትክክል እንዳልሆነ እና ህንጻው ጉድለት እንደሌለበት አስገንዝበዋል።

" ተደጋጋሚ ችግር " ተብሎ የተሰጠው ጥቆማ ምናልባትም ከወር በፊት ከጎን ካለ #የአዋሽ_ባንክ ህንጻ በንፋስ ምክንያት ወደ ታች የወደቀ ቁስ በንብ ህንጻ ስር ባለ ካፌ የመኪና ማቆሚያ ላይ ያደረሰውን ጉዳት ዋቢ ተደርጎ ሊሆን ይችላል እንጂ ህንጻው ከዚህ ቀደም ምንም ችግር ገጥሞት አያውቅም ብለዋል።

የሀዋሳ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ የሰጠው መረጃም ትክክለኛ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
#ሀላባ

- " ባለቤቴ ከወንድሙና እህቱ ጋር በመሆን ፊቴ እስኪበላሽ ደበደቡኝ " - ተበዳይ

- " እንዲህ አይነቱን የሴት ልጅ ጉዳት አንታገስም " - የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊዉ አቶ ሙደሲር ጉታጎ

በሀላባ ከተማ " ባለቤቴ ከእህትና ወንድሙ ጋር በመሆን አደጋ አድርሶብኛል " ያለች ተበዳይ የህግ ድጋፍ ስጡኝ ስትል በማህበራዊ ሚዲያ ጥያቄ አቅርባለች።

ጉዳዩን የተመለከተው የሀዋሳ የቲኪቫህ ቤተሰብ አባል ባደረገዉ ማጣራት ፥ ተጎጅዋ ፊቷ ላይ ጉዳት መደረሱን በተጨማሪ የሷና የመጀመሪያ ልጇ ሰዉነት ትክሻቸዉ አካባቢ ' ጥርስ ንክሻ ' እንደደረሰባቸዉ ለማወቅ ችሏል።

የግል ተበዳዩዋ እናት ለቲክቫ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ ልጃቸዉና የልጅ ልጃቸዉ በደም ተዘፍቀዉ በምሽት ወደቤት እንደመጡና በወቅቱ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገንተው እንደነበር ገልጸዋል።

የግል ተበዳዩዋ ወ/ሮ አበባ ቦረና ፤ " ምንም እንኳን የጋራ አራት ልጆች ቢኖሩንም ካሁን በፊት በመካከላችን በነበረ ግጭት ምክኒያት በፍርድ ቤት ለመለያየት ጫፍ ከደርሰን በኋላ  በሽማግሌ ተመልሰን አንድ ላይ መኖር ከጀመርን 3 ወር አልሆነም " ብላለች።

" ምንም እንኳን ቀን ላይ ቀላል ጭቅጭቅ ውስጥ ብንገባም ከቤተሰቡ ጋር ሆኖ እንዲህ ያደርጋል ብዬ ፍጹም አልጠበኩም " ስትል ተናግራለች።

" በተለይ ተሰብስበዉ ሲደበድቡኝ ለመገላገል የገባዉን የመጀመሪያ ልጃችን ላይ ላይ በዚህ ልክ ይጨክናል ብዬ አላሰብኩም ነበር "  ብላለች።

ጉዳዩን በተመለከተ የጸጥታ አካላት ምን እየሰሩ ነዉ ? በማለት የጠየቅናቸው የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ ሀላፊ አቶ ሙደሲር ጉታጎ ፤ " እንዲህ አይነቱን የሴት ልጅ ጉዳት አንታገስም " ብለዋል።

ጉዳዩን በሰሙ ቅጽበት የከተማው ፖሊስ በፍጥነት ችግር ፈጣሪዎችን  ይዞ እንዲያጣራ ማዘዛቸዉንም ነግረዉናል።

አቶ ሙደሲር  ጉዳዩ ተጣርቶ የሚደረስበትን ውጤት እንደሚያጋሩን ቃል ገብተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ጥቃት አድራሾቹ #ባልና #ወንድም በቁጥጥር ስር ውለዋል " - የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ

ትላንት በባለቤቷ እንዲሁም በባለቤቷ እህት እና ወንድም  ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈጸመባት ገልጻ የህግ ድጋፍ ስለጠየቀችው ወይዘሮ አበባ ቦረና መረጃ ማጋራታችን ይታወሳል።

ጥቃት የደረሰባት ግለሰብ በሀላባ ከተማ ነዋሪ ስትሆን ጥቃት ካደረሰባት ባለቤቷ ጋር 4 ልጆች አፍርታለች።

ወ/ሮ አበባ " ተሰብስበዉ ሲደበድቡኝ ለመገላገል የገባዉን የመጀመሪያ ልጃችንም የጥቃቱ ሰለባ ሆኗል " ማለቷ አይዘነጋም።

በጉዳዩ ላይ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የሀላባ ዞን ጸጥታ መምሪያ ሀላፊ  አቶ ሙደሲር ጉታጎ ፥ " የሴት ልጅን ጥቃት አንታገስም " በማለት ከሀላባ ከተማ ፖሊስ ጋር በመተባበር ሁኔታውን መመልከት እንደጀመሩ ገልጸው ነበር ።

ዛሬ አቶ ሙደሲር ባደረሱን መረጃ ጉዳቱን ካደረሱ በኋላ ተደብቀዉ የነበሩት ወንድማማች ጥቃት አድራሾች ፖሊስ ባደረገዉ ጥረት ተገኝተው በቁጥጥር ስር ውለዋል።

አቶ ሙደሲር የግል ተበዳዩዋን በስልክ ደውለዉ ማነጋገራቸውን ገልጸውልናል።

" አሁን ላይ ሰዎቹ በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል " ያሉት ኃላፊው " ህጋዊ ምርመራ እንዲካሄድ ተበዳይ ሰኞ በአካል ቀርባ ክስ መመስረት ትችላለች " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia