TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ATTENTION

ዳባት !

የዳባት ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ም/ቤት በወቅታዊ ጉዳይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል።

ምክር ቤቱ ካሳለፋቸው ውሳኔዎች መካከል ፦

- በከተማዉ ውስጥ ማንኛዉም ሰዉ ከምሽቱ 2:00 ሰዓት በኃላ እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ውሳኔ ተላልፋል።

- ማንኛዉም መጠጥ ቤቶችና ምግብ ቤቶች ከምሽቱ 2:00 በኃላ አገልግሎት እንዳይሰጡ ተከልክለዋል።

- በከተማው ማንኛውም ተሽከርካሪ ባጃጅን ጨምሮ ከምሽቱ 12:00 በኋላ እና ጧት ከ12:00 ስዓት በፊት ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ተክልክሏል።

- በከተማው የሚገኙ አልጋ ቤቶች ፣ቤት አከራዮች እና ሆቴሎች ማንነቱ ያልታወቀን ሰው ማንነቱን በመለየት በመረጃ ፎርም ሞልተው ማከራየት እና አጠራጣሪ ሁኔታ ሲያጋጥም ለህግ አካላት እንዲያሳውቁ ተብለዋል።

- የባጃጅ አሽከርካሪዎች ከዳባት ዳራ እና ከዳባት ወቅን ብቻ እንዲያሽከረክሩ የተወሰነ ሲሆን ከዳባት ወደ አጅሬ መስመርና ከዳራ ገደብየ ማሽከርከር ተከልክሏል።

- የዳባት ከተማ ፈቃድ የሌለዉ ባጃጅ ከዳባት ወደ ሌላና ከሌላ ቦታ ወደ ዳባት ማሽከርከር ተከልክሏል።

- ለፀጥታ ስራ ከተሰማሩት ዉጭ ማንኛዉም ግለሰብ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

ከዚህም በተጨማሪ የፀጥታ ም/ቤቱ ፤ ማንኛውም ሰው የህዝብን ስነልቦና የሚጎዳ ማንኛውም ሀሰተኛ ወሬ ሆነ አሉባልታ ከማሰራጨት እንዲቆጠብ እና መላው የከተማው ማህበረሰብ በአደረጃጀቶቹ አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፏል።

በሌላ በኩል በከተማው ተከራይተዉ የሚኖሩ ኤርትራዊያን ስደተኞች ወደ ካፕ የሚመለሱበት ምቹ ሁኔታ እንዲመቻች ከሚመለከታቸዉ አካለት ጋር ስራ እየተሰራ መሆኑ ምክር ቤቱ ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ATTENTION

ሰቆጣ !

የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የፀጥታ  ሁኔታ በማስመልከት ውሳኔዎችን አሳልፏል።

- ማንኛውም እግረኛ ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ በጥብቅ ተከልክሏል።

- ለጸጥታ ስራ ስምሪት ከተሰጣቸው ተሸከርካሪዎች ውጭ ማንኛውም ተሸከርካሪ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

- ከጸጥታ መዋቅሩ ውጭ በየትኛውም ሰዓትና ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

- ማህበረሰቡን የሚያውኩ የሃሰት አሉባልታዎች / የሃሰት መረጃዎችን ማሰራጨት ተከልክሏል።

- ተፈናቃዮች ከተሰጣቸው የመጠለያ ካምፕ ውጭ መንቀሳቀስ በብቅ ተከልክሏል።

- ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ባንክ ቤቶች፣ ሱቆች፣ ሆቴል እና መስል የመንግስትና የግል ድርጅቶችን መዝጋት በጥብቅ ተከልክሏል።

- በከተማው የሚገኙ የመንግስትና የግል ታጣቂዎች መንግስት በሚያሰማራው የፀጥታ ስራ ላይ ተሳታፊ የመሆን ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

- ማንኛውም ማህበራዊ ሚዲያ  ተጠቃሚ ግለሰብ ሆነ ድርጅት የትኛውንም  ሚዲያ ተጠቅሞ የሃሰት መረጃዎችን ማሰራጨት፣ በተለይ ስለጦርነቱ አሉቧልታ መዘገብ ሆነ መግለጫ መስጠት በጥብቅ ተከልክሏል።

- ማንኛውም የቤት አከራይ ወይም አልጋ ቤቶች ተከራዮቻቸውን የመለየትና የገለሰቦቹን ማንነት የሚለይ ህጋዊ መታወቂያ ስለመያዛቸው የማረጋገጥ ግደታ አለባቸው።

- ማንኛውም የከተማው ማህበረሰብ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር የመቀናጀትና የመተባበር  ግዴታ አለበት።

እንዚህ በማይከብር ላይ የፀጥታ መዋቅሩ አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ ታዟል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ሰቆጣ ! የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የፀጥታ  ሁኔታ በማስመልከት ውሳኔዎችን አሳልፏል። - ማንኛውም እግረኛ ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ በጥብቅ ተከልክሏል። - ለጸጥታ ስራ ስምሪት ከተሰጣቸው ተሸከርካሪዎች ውጭ ማንኛውም ተሸከርካሪ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።…
#ATTENTION

ኮምቦልቻ !

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ምክር ቤት የከተማድን ሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ከመከረ በኋላ ውሳኔዎችን አሳልፏል።

ከውሳኔዎቹ መካከል ፦

- ከዛሬ ነሀሴ 24/2014ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውም የከተማው ነዋሪ ከ11 ጀምሮ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

- በማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም አላስፈላጊ ህዝብን ወደ አለመረጋጋት የሚወስዱ የተዛቡ መረጃዎችን መልቀቅ በህግ ያስጠይቃል።

- በከተማው አሉባልታ ማናፈስ በህብረተሰብ መካከል ሽብርና ውዥንብር የሚነዙ የተሳሳተ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት በህግ እንዲጠየቁ ተወስኗል።

- በከተማ ደረጃ  አገልግሎት የሚሰጡ  ታክሲዎች እስከ 11 ሰዓት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ  ተወስኗል።

- ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ተንተርሶ የከተማችን ነዋሪ ላይ ያለ አግባብ ዋጋ ጭማሪ በማድረግ እና ሸቀጦችን በመከዘን በገበያ ላይ እጥረትን  በመፍጠር ነዋሪውን ለተጨማሪ ወጭና የኑሮ ጫና የሚጥሉ አካላት ላይ ህጋዊ እረምጃ  እንዲወሰድ ታዟል።

- በምግብ ቤቶች ፣ መጠጥ ቤቶች፣ ካፌዎችና ግረሶሪዎች ከ11 ስዓት ጀምሮ ማንኛውም አገልግሎት መሰጠት ተከልክሏል።

- DSTV ማሳያ ቤቶች ፣የቡና መሸጫ ቤቶች ፣የሺሻና የጫት ማስቃሚያ ቤቶች ውስጥ ተሰብስቦ  ጫት መቃም በህግ ያስጠይቃል።

- የአልጋ አከራ ሆቴሎች፣ የመኖሪያ እና መደብ አከራዮችን አገልግሎት ሲሰጡ የተገልጋዩን ማንነት የሚገልፅ መረጃ በመያዝ አገልግሎት እንዲሰጡና መታወቂያ ኮፒ ማድረግ እንዳይዘነጉ ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

ለመረጃ እና ጥቆማ፦ በስልክ ቁጥሮች 0335510005
0335510945
0921038804 ላይ መደወል ይቻላል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ኮምቦልቻ ! የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ምክር ቤት የከተማድን ሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ከመከረ በኋላ ውሳኔዎችን አሳልፏል። ከውሳኔዎቹ መካከል ፦ - ከዛሬ ነሀሴ 24/2014ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውም የከተማው ነዋሪ ከ11 ጀምሮ መንቀሳቀስ ተከልክሏል። - በማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም አላስፈላጊ ህዝብን ወደ አለመረጋጋት የሚወስዱ የተዛቡ መረጃዎችን መልቀቅ በህግ ያስጠይቃል።…
#ATTENTION

ደብረ ብርሃን !

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ የፀጥታ ስጋትን አስመልክቶ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል።

- በከተማው አስተዳደር በተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚኖር ተፈናቃይ ከምሽቱ 12:00  ሰዓት በኋላ ወደ መጠለያ ጣቢያውም ሆነ ወደ ከተማው መግባት ተከልክሏል።

- ሁሉም አይነት ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

- መጠጥ ቤቶች ፣ ምግብ ቤቶች ምሽት ጭፈራ ቤት እስከ ምሸት 2:00 ሰአት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ተወስኗል።

- የንግድ ቤቶች የምርት የዋጋ ጭማሪ ማድረግ በጥብቅ ተከልክሏል።

- ከተፈቀደላቸው የፀጥታ ሀይሎች ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈፅሞ ተከልክሏል።

- ከመንግስት ዕውቅና ውጭ ማናቸውም አይነት ውይይቶችና ስብሰባ ማድረግ ተከልክሏል።

- አዳር የሚሰሩ በከተማው ያሉ ፋብሪካዎችና ድርጅቶች ድርጁቱ በሚሰጣቸው ህጋዊ  መረጃ እና በፀጥታ መዋቅሩ የተረጋገጠ የይለፍ ከያዛ ብቻ መንቀሳቀስ ይችላሉ።

- ህብረተሰቡን ለማሸብር አሉባልታ መንዛት፣ ወሬ ማሰራጨት በጥብቅ የተከለከለ ነው ፤ መላው ማህበረሰብም አካባቢውን ቀንና ሌሊት በንቃት መጠበቅ አለበት።

- የሆቴል አልጋ አከራዮች ማንነቱ ያልታወቀ የታጠቀ ገለሰብ በድርጅታቸው ውስጥ ሲያጋጥም ለህግ አካላት እንዲያሳውቁ ፤ በሌላ በኩል ፤ የቤት አከራዮች የሚያከራዩትን ግለሰብ መታወቂያ በመጠየቅ፣ ፎርምም በመሙላት ሰላም እና ፀጥታ መምሪያ እንዲያሳውቁ ተብሏል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ደብረ ብርሃን ! የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ የፀጥታ ስጋትን አስመልክቶ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል። - በከተማው አስተዳደር በተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚኖር ተፈናቃይ ከምሽቱ 12:00  ሰዓት በኋላ ወደ መጠለያ ጣቢያውም ሆነ ወደ ከተማው መግባት ተከልክሏል። - ሁሉም አይነት ተሽከርካሪዎች ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።…
#ATTENTION

ላሊበላ !

የላሊበላ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ ሁኔታን መነሻ በማድረግ የሰዓት ዕላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ውሳኔዎችን አሳልፏል።

ውሳኔዎቹ ፦

- ከምሽቱ 1:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ወደ ከተማዋ መግባትም ሆነ መውጣት አይቻልም።

- ማንኛውም ተሽከርካሪ ከምሽቱ 1:00 ሰዓት በኋላ እስከ ንጋቱ 12:00 ድረስ መንቀሳቀስ አይቻልም።

- ከተፈቀደለት አካል ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ ተከልክሏል።

- በመንግስት ዕውቅና ካለው የፀጥታ አካል ውጭ የፀጥታ አካላትን የደንብ ልብስ ለብሶ መንቀሳቀስ በፍፁም አይቻልም።

የላሊበላ ከተማ አስተዳደር ህዝቡ በሀሰተኛ ወሬ እና አሉባልታ ሳይደናገር አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ATTENTION

ሰንበቴ !

የሰንበቴ ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 26/ 2014 ዓ/ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሰዓት እላፊ ገደብ አውጇል።

በዚህም መሰረት ፦

- የከተማ ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጆች) ከምሽቱ 12 ሰአት ጀምሮ በከተማው ውስጥ ማሽከርከር ተከልክለዋል።

- ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ #ማንኛውም_ሰው መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

የተጠቀሰው የሰአት እላፊ ገደብ ጥሶ የተገኘ ግለሰብ ላይ አስፈላጊው የህግ እርምጃ እንዲወሰድ ታዟል ሲል የከተማ አስተዳደሩ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ሰንበቴ ! የሰንበቴ ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 26/ 2014 ዓ/ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሰዓት እላፊ ገደብ አውጇል። በዚህም መሰረት ፦ - የከተማ ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጆች) ከምሽቱ 12 ሰአት ጀምሮ በከተማው ውስጥ ማሽከርከር ተከልክለዋል። - ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት…
#ATTENTION

የጎንደር ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት ወቅታዊ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።

ከውሳኔዎቹ መካከል ፦

- ከተፈቀደላቸው የፀጥታ አካላት ውጭ የተለያዩ የፀጥታ አካላት አልባሳትን መልበስ ተከልክሏል።

- ከፀጥታ መዋቅሩ ውጭ፣ በከተማው በብሎክ አደረጃጀት አካባቢን እንዲጠብቅ በተሰጠው ተራው ከተሰማራው ውጭ በየትኛውም ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው፡፡

- ማህበረሰቡን የሚያውኩ አሉባልታዎች ወይም የሃሰት መረጃዎችን በተለያዩ ሚዲያዎች፣ በመጠጥ ቤቶች ወዘተ ማሰራጨት ህዝቡን ማወዛገብ፣ ማሰጨነቅ በጥብቅ ተከልክሏል።

- በከተማው ያሉ ተፈናቃዮች ከተሰጣቸው መጠለያ ካምፕ ውጭ መንቀሳቀስ የተከለከለ ሲሆን ለገበያ፣ ለህክምና፣ ለአንገብጋቢ ጉዳዮች፣ ለተለያዩ ስራዎች ከመጠለያው መውጣት ያለበት ተፈናቃይ በሚመለከታቸው የካምፕ አስተባባሪዎችና በክ/ከተማው የፀጥታ መዋቅር እውቅና እና የመውጫና የመግቢያ ፈቃድ መለያ ካርድ ይዞ ተመዝግቦ ተፈቅዶለት የሚንቀሳቀስ ይሆናል፡፡

- በአሉባልታ ወሬዎችና ስበብ በመፈለግ ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ እንደ ባንክ ቤት፣ ሱቆችና ሆቴሎች፣ የገበያ ማዕከሎች እና የመሳሰሉትን መዝጋት ተከልክሏል።

- ከነሀሴ 27 ጀምሮ የቀበሌ መታወቂያ መስጠት ተከልክሏል። አስቸኳይ የሆነ ለምሳሌ ለህክምና፣ ወደ ዩኒቨርስቲ ለመሄድ፣ ወደ ውጭ አገር ለሚደረግ ጉዞ ከገጠሙ የክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚና የክ/ከተማው ሰላምና ደህንነት በጋራ በማየት መታወቂያ ሊሰጡ ይችላሉ።

- አግባብነት የሌለው የዋጋ ንረት የሚፈጥሩ በሸቀጦች በግብርና ምርቶች ላይ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ጨምሮ ህዝቡን ማስቃየት በጥብቅ ተከልክሏል።

- በጫት ቤቶች ተሰብስቦ በመቃም አሉባልታና ሽብር መንዛት ተከልክሏል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ወልድያ ! የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን አካባቢ ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 22 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ የሰዓት እላፊ ገደብ አስቀምጧል። በዚህም ፦ • ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ማንኛውም ሰው መንቀሳቀስ #ተከልክሏል። • ለጸጥታ ስራ ስምሪት ከተሰጠው ተሽከርካሪ ውጭ ማንኛውም ተሽከርካሪ…
#ATTENTION

ወልድያ !

በዛሬው ዕለት የወልድያ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ም/ ቤት ከዚህ ቀደም ካሳለፈው ውሳኔ ተጨማሪ ውሳኔዎችን አሳልፏል።

የከተማውን አሁናዊ ሁኔታ መነሻ ከተማ በማድረግ የሰዓት እላፊ ገደብ መውጣቱ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች ክልከላዎችን ማስቀመጥ አስፈልጓል ተብሏል።

ከተላለፉ ውሳኔዎች መካከል ፦

- ከፀጥታ መዋቅሩ ውጭ በየትኛውም ቦታ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም ተከልክሏል።

- ከተፈቀደላቸው የመንግስት የፀጥታ አባላት ውጭ የሰራዊቱን አልባሳትን መልበስ በጥብቅ ተከልክሏል።

- በከተማው የሚገኙ የራያና ቆቦ ከተማ ተፈናቃዮች ውጭ ሌላው አካል ወደ መጣበት አካባቢ እንዲመለስ በጥብቅ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

- ሀሰተኛ ወሬ በመልቀቅ የከተማውን ማህበረሰብ የሚያውኩ አሉባልታዎችን በሚዲያዎችና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት በማሰራጨት ህዝቡን ማዋከብ በጥብቅ ተክልሏል።

- በከተማ  የህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ባንክ ቤት፣ ሱቆች፣ ሆቴሎች፣ ካፌና ሬስቶራንቶች፣ የንግድ ተቋማት እና የመሳሰሉትን መዝጋት ፍጹም ተከልክሏል።

- ከነሀሴ 29/2014 ዓ.ም ጀምሮ የቀበሌ መታወቂያ መስጠት ተከልክሏል።

- አግባብነት የሌለው የዋጋ ንረት መፍጠር፣ በሸቀጦችና በግብርና ምርቶች ላይ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ጨምሮ ህዝቡን ማስቃየት፣ በማንኛውም ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ውስጥ መገኘት በህግ ያስጠይቃል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ወልድያ ! የወልድያ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት የሰዓት እላፊ ገደብ ላይ የማሻሻያ ውሳኔ ዛሬ መስከረም 4 ቀን 2015 ዓ/ም አሳልፏል። ሌሎች ክልከላዎች እንደቀጠሉ ሆኖ በሰዓት እላፊ ገደብ ላይ የተደረገው ማሻሻያ ፦ - ከቀኑ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የነበረው የተሽከርካሪ የሰዓት እላፊ ወደ ምሽቱ 1:00 ሰዓት፤ - ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ የነበረው የሰዎች እንቅስቃሴ የሰዓት…
#ATTENTION

ወልድያ !

የወልድያ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ም/ቤት ነባራዊ ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ ተጨማሪ ክልክለዎችን አስተላለፈ።

የፀጥታ ምክር ቤቱ ከዚህ ቀደም የከተማውን ወቅታዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ  ክልከላዎችን ማስቀመጡ ይታወሳል።

ሆኖም ነባራዊ ሁኔታ በማየት ተጨማሪ ክልከላዎች በማስፈለጉ ከነገ መስከረም 22 / 2015 ዓ.ም ጀምሮ  የሚተገበሩ ተጨማሪ ዉሳኔዎችን ማሳለፉን ገልጿል።

በዚህ መሰረት :-

1. ከነገ መስከረም 22  ቀን ጀምሮ ጫት ወደ ከተማዋ ማስገባት በጥብቅ ተከልክሏል።

2. ከነገ ጀምሮ ጫት መቃም ሆነ ማስቃም በጥብቅ ተከልክሏል።

3. ከነገ ጀምሮ የጎዳና ላይ ቁማር (ቢንጎ የመሳሰሉትን) መጫወት ተከልክሏል።

ከላይ የተዘረዘሩትን ውሳኔዎች ጨምሮ ከዚህ በፊት የተላለፉ ዉሳኔዎችን ማንኛውም አካል የማክበርና ኃላፊነቱን የመወጣት ግዴታ አለበት የተባለ ሲሆን ውሳኔዎቹን የማያከበር ግለሰብም ሆነ ድርጅት ላይ የፀጥታ መዋቅሩ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

መረጃው ከከተማው ኮሚኒኬሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ATTENTION

" ለሕዝቡ አስቸኳይ ዕርዳታ ካልደረሰለት አደጋው ከአሁኑ ሊብስ ይችላል "

በሶማሌ ክልል ዳዋ ዞን አስተዳደር ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ ሀቢቻ ለሪፖርተር የሰጡት ቃል ፦

" ሕዝቡ የሚኖረው በከብቶቹ ላይ ተመሥርቶ ነው፡፡ ድርቁ እስከ መቼ እንደሚቀጥል አይታወቅም፡፡

ለሕዝቡ አስቸኳይ ዕርዳታ ካልደረሰለት አደጋው ከአሁኑ ሊብስ ይችላል።

የሞተውን የእንስሳት ሀብት ቁጥር ገና እየተጠና ነው፤ በሰዎች ላይ የደረሰውንም ጉዳት እየተገመገመ ነው።

ስለጉዳቱ የተጣራ አኃዝ ባይኖረንም በምግብ እጥረት ችግር ወደ ሆስፒታል የገቡ ሰዎች መረጃ አለን። "

NB. አምና በሶማሌ ክልል ካሉ 11 ዞኖች በአሥሩ ከባድ የድርቅ አደጋ ደርሶ #ከአንድ_ሚሊዮን ያላነሱ እንስሳትን ገድሏል። የዳዋ ዞን ገና ከዚህ አደጋ ያላገገመ ሲሆን ዘንድሮም ከባድ አደጋ ገጥሞታል።

Credit : #Reporter

@tikvahethiopia
#ATTENTION

በሶማሌ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ ቀረበ።

በሶማሌ ክልል በተከሰተው ድርቅ ከ3 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ዜጎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚፈልጉ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

ኮሚሽኑ ይህን ያሳወቀው ለፋና ብሮድካስት ኮርፖሬሽን በሰጠው ቃል ነው።

በሶማሌ ክልል ከሚገኙ 11 ዞኖች ውስጥ በዘጠኙ ላይ ድርቅ የተከሰተ ሲሆን ድርቁ በሰዎች እና እንስሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ብሏል ኮሚሽኑ።

አሁን ላይ ድርቁን ተከትሎ በሶማሌ ክልሉ አዲሱን ጥናት ሳይጨምር ከ3 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ዜጎች አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ተገልጿል።

በክልሉ እየተካሄደ ያለው አዲስ ጥናት ሲጠናቀቅ የተረጂዎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተመላክቷል።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም በክልሉ በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ያሳወቀው ኮሚሽኑ የተረጂዎች ቁጥር ከፍተኛ እና ከቀን ወደ ቀን እያሻቀበ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞም ተጨማሪ አስቸኳይ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥቷል።

ስለሆነም ፦
- መንግስታዊ ተቋማት፣
- የግል ድርጅቶች፣
- አጋር አካላት፣
- ታዋቂ ሰዎች እና ዳያስፖራዎች በክልሉ በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች ድጋፍ እንዲያደርጉ ኮሚሽኑ ለፋና ብሮድካስት ኮርፖሬሽን በሰጠው ቃል ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#ATTENTION

" በድርቅ እና ለረጅም ጊዜ በተከሰተ የፀጥታ ችግር ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ በርካት ሰዎች ለአደጋ ተጋልጠዋል " - የአማሮ ልዩ ወረዳ

• " ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ህፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ለረሀብ፣ ለበሽታ እና ለሞት እየተዳረጉ ነው " - የቡርጂ ልዩ ወረዳ

በደቡብ ክልል አማሮ እና ቡርጂ ልዩ ወረዳዎች በተከሰተ ድርቅ ምክንያት ከ136 ሺህ በላይ ሰዎች አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተገልጿል።

#አማሮ

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የአማሮ ልዩ ወረዳን ዋቢ አድርጎ ባሰራጨው መረጃ ፤ በልዩ ወረዳው ለረጅም ጊዜ ዝናብ ባለመጣሉ በ22 ቀበሌዎች ድርቅ ተከስቷል፡፡

በተከሰተው ድርቅ ምክንያት በልዩ ወረዳው ከ96 ሺህ በላይ ሰዎች አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።

በድርቁ ከ3 ሺህ 500 በላይ የቤት እንስሳት በድርቁ ምክንያት መሞታቸው ተገልጿል።

በልዩ ወረዳው የተከሰቱ የፀጥታ ችግሮች የህብረተሰቡን ተጋላጭነት እንዳባባሱት ልዩ ወረዳው አመልክቷል።

በድርቁ እና ለረጅም ጊዜ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ በርካት ሰዎች ለአደጋ መጋለጣቸው ተገልጿል።

የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በተለያየ ጊዜ እርዳታ ቢያደርግም በልዩ ወረዳው ከከተከሰተው ጉዳት አንፃር ድጋፉ በቂ አለመሆኑን ልዩ ወረዳው አሳውቋል።

#ቡርጂ

የቡርጂ ሶያማ ልዩ ወረዳ በበኩሉ በልዩ ወረዳው በተከሰተው ድርቅ 83 ሺህ 528 ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አሳውቋል።

በልዩ ወረዳው ከ30 ሺህ በላይ እንስሳት መሞታቸውም ተጠቁሟል።

ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ህፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ለረሀብ፣ ለበሽታ እና ለሞት እየተዳረጉ መሆኑ ተገልጿል።

ከክልሉ መንግስት በተጫማሪ የአካባቢው ተወላጆች እና ግለሰቦች እርዳታ ቢያደርጉም በልዩ ወረዳው ከተከሰተው ድርቅ አንፃር የተጎዱ ዜጎችን ለመርዳት በቂ አለመሆኑ ተመላክቷል።

በድርቅ የተጎዱ ዜጎችን ለመርዳት እና መልሶ ለማቋቋም ረጂ ድርጅቶችን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረታቸውን ወደ ልዩ ወረዳው እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

#ኮንሶ

በኮንሶ ዞን በተከሰተ ድርቅ ከ800 ሺህ በላይ ዜጎች ለአስቸኳይ ድጋፍ መዳረጋቸውን ዞኑ አሳውቋል።

ለተከታታይ 5 ዓመት የተከሰተው የዝናብ መዘግየት እና እጥረት ባስከተለው ድርቅ ለአስቸኳይ ድጋፍ የተዳረጉት 822 ሺ 526 ዜጎቻችን ናቸው።
 
የተከሰተው ድርቅ ዜጎች ላይ አስከፊ ጉዳት ከማድረሱ በፊት በችግር ውስጥ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ ሊደረግ ይገባል ተብሏል።

Credit : #FBC #SRTA

@tikvahethiopia
#ATTENTION

በአማራ ክልል ፤ የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን አስተዳደር ጥብቅ ክልከላዎች ተጣሉ።

የኦሮሞ ዞን ኮማንድ ፖስት ምን ክልከላዎችን ጣለ ?

- የሰአት እላፊ ገደብ (ባጃጅ 1:00፤ የሰው እንደ አካባቢና እንደ ሚፈጠር ችግር ይወሰን ፆም በመሆኑ ተብሏል) ።

- ስምሪት ከተሰጠው ሃይል ውጭ ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ እንደማይቻል ተገልጿል።

- በማንኛውም ሆቴል መሳሪያ ይዞ መግባት የተከለከለ ሲሆን ፤ በሁሉም ሆቴሎች ፍተሻ እንዲጠናከር ታዟል።

- የፀጥታ ሃይሉን መጠርነፍና ለግዳጅ ዝግጁ ማድረግ ፖሊስና ሚሊሻ ፤ ከፌደራልና መከላከያ ጋር በቅንጅት መስራት አለባቸው ተብሏል።

- የኬላ ላይ ፍተሻ እንዲጠናከር ታዟል።

- የህዝብ ግንኙነት ስራ በተደጋጋሚ እንዲሰራ ታዟል ፤ በዋናነት በመስመር መዝጋት እየተጎዳ ያለው ህዝብ መሆኑ ተመላክቷል።

- ህብረተሰቡ በቀበሌ፣ በመንደር፣ በሰፈር፣ በኬላ፣ በተቋማት ጥበቃ ላይ ተደራጅቶ አካባቢውን የመጠበቅና ለሰላም ለሚከፈል ዋጋ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ታዟል።

- የተሳሳተ መረጃ የሚነዙ፣ በአሉቧልታ ህዝብን የሚያሸብሩ፣ ወንጀለኞችን ለመንግስት አጋልጦ እንዲሰጥ ሁሉም በጥብቅ ተማምኖ መንቀሳቀስ አለበት ተብሏል።

- ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እንዲደረግ ፤ በየደረጃው ያለው አመራርና ህዝቡ ከፀጥታ ማዋቅሩ ጋር መረጃ መለዋወጥ እንዳለበት ታዟል።

- የመንግስት ተቋማት፣ ባንኮችን ፣ የሀይማኖት ተቋማትን የጥበቃ ሁኔታን እንዲጠናከር ታዟል።

- የአካባቢውን ሁኔታና የዞኑን ክልከላ በማይጣረስ መንገድ ተጨማሪ ክለከላዎችን በወረዳና ከተማ አስተዳደር ኮ/ፖስት ማወጅ እንደሚቻል ተገልጿል።

መረጃው የኦሮሞ ዞን ኮማንድ ፖስት ነው።

@tikvahethiopia
#ATTENTION🔊

በዳሰነች ወረዳ የኦሞ ወንዝ በመሙላቱ / ከመደበኛ ፍሰቱ ወጥቶ ሞልቶ በመፍሰሱ ዜጎቻችን እየተጎዱ ነው።

እንደ ዳሰነች ወረዳ አስተዳደር መረጃ ፦

- በ34 ቀበሌያትና በ7 ደሴቶች የሚኖሩ 79,828 ቤተሰብ አባላት በወንዙ ሙላት የተጎዱ ተጎድተዋል።

- በወረዳው ካሉ 40 ቀበሌያቶች 34ቱ ቀበሌያት  በውሃ የመዋጥና የመከበብ አደጋ ያጋጠማቸው ሲሆን ከዚህ ውስጥ 27ቱ ቀበሌያት ሙሉ በሙሉ በውሃ ሙላት ተውጠዋል ፤ 7ቱ ቀበሌያት ደግሞ በቀጣይ ስጋት ውስጥ ናቸው።

- በኦሞ ወንዝ ሙላት ሳቢያ 1,435.75 ሄ/ር በመስኖ የተዘራ ሰብልና 123,000 ሄ/ር የእንስሳት የግጦሽ መሬት ሙሉ በሙሉ በውሃ ተሸፍኗል።

- በደሴቶች ውስጥ የነበሩና በውሃ ሙላት የተከበቡ እንስሳት ብዛት 2,993,135 ሲሆን ከዚህ ውስጥ አስካሁን ከውኃ ሙላት የወጡ 889,454 እንስሶች ናቸው።

- በውሃ መጥለቅለቁ 8 የሰው ጤና ኬላዎች፣ 1 ጤና ጣቢያ፣ 6 ትምህርት ቤቶች፣ 6 የእንስሳት ጤና ኬላ፣ 5 የአርብቶ አደር ማሰልጠኛ ጣቢያ ፣ 4 የመኖ ቤል እስቶር እና በ14 ቀበሌያት በስራ እድል ፈጠራ በማህበራት ተደራጅተው ከተለያዩ አበዳሪ ተቋማት ተበድረው ወደ ስራ የገቡ እና በፕሮጀክት የታቀፉ 32 ማህበራትና 15 ሼዶች ሙሉ ለሙሉ በውሃ ሙላት ተውጠዋል፤ ስራም አቁመዋል።

በአደጋው ለተጎዱ ወገኖች ሁሉም ባለድርሻ አካላት በመተባበርና በመቀናጀት አፋጣኝ ምላሽ ሊሰጡ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
#Attention

የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት ፤ ከዛሬ ጀምሮ የትኛውም አይነት የትራንስፖርት አገልግሎት ከደሴ - ሸዋሮቢት_ ደ/ብረሀን እንዲሁም ከደ/ብረሀን -ሸዋሮቢት - ደሴ እንዲቆም ውሳኔ መተላለፉን አሳውቋል።

የትራንስፖርት እንቅስቃሴው እንዲቆመ የተደረገው ኮማንድ ፖስቱ " ፅንፈኛ " ባላቸው ታጣቂዎች ላይ ኦፕሬሽን በመጀመሩና ቀጠናውን ነፃ ለማድረግ እርምጃ መውሰድ በመጀመሩ እንደሆነ ተገልጿል።

በመሆኑም በቀጠናው የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቆም የተወሰነው ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ መሆኑን ያሳወቀው ኮማንድ ፖስቱ ውሳኔው ለጊዜው ነው ብሏል።

ህብረተሰቡ ከዛሬ ጀምሮ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ #እንዲቆም የተወሰነ መሆኑ እንዲያውቅና አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ፤ የፀጥታ ሀይሉም ውሳኔው እንዲፈፀም ክትትል እንዲያደርግ ትዕዛዝ መሰጡቱ ታውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢፍጧር የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆነዋል። በነገው ዕለት በአዲስ አበባ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በመስቀል አደባባይ ከሚካሄደው ታላቁ የኢፍጣር መርኃ ግብር  ጋር ተያይዞ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት፡- - ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን - ከወሎ ሰፈር ወደ መስቀል አደባባይ   ኦሎምፒያ…
#ATTENTION

ሁሉም ምዕመናን ወደ ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጧር በኢትዮጵያ-4 ሲመጡ ሊከተሏቸው የሚገቡ ደንቦች የሚከተሉት ናቸው።

1ኛ. ለጸጥታ አካላትና ለበጎ ፍቃድ አስተባባሪዎች #ለፍተሻ ትብብር ማድረግ ይገባል።

2ኛ. የሰላት መስገጃ እና ጥላ ይዘው መምጣት እንዳይዘነጉ።

3ኛ. ለማፍጠሪያ የሚሆንና ሙስሊም እህትና ወንድሞችን በማካፈል ኢፍጣርን ለሌሎች በማጋርት የሚገኘውን አጅር ተቋዳሽ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል። ምግቦቹ እንደ ፦
- ቴምር፣
- ውሃ
- የታሸጉ ምግቦች መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

4ኛ. ማንኛውም ለደህንነት አጠራጣሪ ሁኔታዎች ከተመለከቱ ለበጎ ፍቃደኛ አስተባባሪዎችና ለጸጥታ አካላት በአፋጣኝ ማሳወቅ ይገባል።

5ኛ. ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ዝግጅት ዋናው ዓላማ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከሌሎች ጋር ኢፍጣርን በማጋራት የሚገኘውን አጅርና ደስታ እንዲያጣጥም ከማስቻል ባሻገር ሙስሊሞች ምንም ዓይነት ልዩነት ሳይገድባቸው ህብር ብሄራዊ  አንድነታቸውን በማሳየት ለሃገር ሰላምና ዕድገት በጋራ አላህን የሚማፀኑበት ዝግጅት ስለሆነ ከዝግጅቱ ዓላማ ውጪ ከሆኑ ድርጊቶች በመቆጠብ ኢስላማዊ ስነምግባርን ለሌሎች ዓርኣያ በመሆን ማሳየት ይገባል።

6ኛ. በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ለተፈናቀሉ ወገኖችን ድጋፍ ስለሚሰበሰብ ከወዲሁ በረመዳን ለተቸገሩ ድጋፍ በማድረግ የሚገኘውን ታላቅ አጅር እንዲሸምቱ ጥሪ ተላልፏል።

7ኛ. የዝግጅቱ አላማ መዓድ መጋራት እንደመሆኑ ከአላሰፈላጊ የምግብ ብክነት በመቆጠብ ምዕመኑ ሃይማኖታዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

8ኛ. ንፅህና የሙስሊም መገለጫ እንደመሆኑ ሁሉም ምዕመን የተጠቀመባቸው እቃዎች በአግባቡ እንዲያስወግዱ።

(ከአዘጋጆቹ ሀላል ፕሮሞሽን እና ነጃሺ በጎ አድራጎት ድርጅት)

ከ5:00 ሰዓት ጀምሮ የሚዘጉ መንገዶች 👇
https://t.me/tikvahethiopia/86345

@tikvahethiopia
#Ethiopia #Attention🚨

የትራፊክ አደጋ የበርካቶች ህይወት እየቀጠፈ ይገኛል።

በዚህ ወር ብቻ ፦

- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 2 ሰዎች ሲሞቱ 5 ሰዎች ተጎድተዋል።

- በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ ከኔጌሌ ወደ ዶዶላ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ መኪና 'አላንቱ' ላይ ከ " ሲኖትራክ " የጭነት መኪና ጋር ተጋጭቶ የ15 ሰዎች ህይወት አልፏል። ሌሎችም ተጎድተዋል።

- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በካፋ ዞን ጨና ወረዳ ፤ ከዋቻ ወደ ቦንጋ ሲጓዝ የነበረ ዶልፊን ተሸከርካሪ እና ከሚዛን ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ #ሲኖ_ትራክ ተሸከርካሪ በጨና ወረዳ ቦባ በላ ቀበሌ ተጋጭተው 5 ሰዎች ሲሞቱ 13 ሰዎች ተጎድተዋል።

-  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን በእዣ ወረዳ ወርት በተባለች ቀበሌ እንጨት ጭኖ ሲጓዝ የነበረ #ሲኖ_ትራክ የጭነት ተሽከርካሪ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ   የ6 ወጣቶች ህይወት ወዲያዉ ሲያልፍ በ10 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷል። አደጋዉን የከፋ ያደረገው ሲኖ ትራኩ  ወጣቶችን እንጨት ላይ አሳፍሮ እየተጓዘ ባለበት ወቅት አደጋው በመድረሱ ነው።

ከላይ በተጠቀሰው እና በይፋ በታወቀው ብቻ 28 ዜጎች በትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን አጥተዋል። በርካቶች የአካል ጉዳተኛ ሆነው።

እባካችሁ ጥንቃቄ አይለያችሁ !

@tikvahethiopia
#ATTENTION🚨

“ የካንሰር ሕመም እየጨመረ ነው ” - ዶክተር አስቻለው ወርቁ

በኢትዮጵያ የካንሰር ተጠቂዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን፣ በተለይም ማኀበረሰቡ ትንቦሆ፣  አልኮል ነክ ነገሮችን ከመጠቀም እንዲታቀብ ጥሪ ቀረበ።

ለካንሰር ሕሙማን የሕክምና አገልግሎት እየተሰጠ ቢሆንም በተለይ በኢትዮጵያ በኩል የፋይናንስ እጥረት ችግር እንደፈተነው ማቲዎስ ወንዱ ካንሰር ሶሳይቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ተቋሙ የ20ኛ ዓመት ምስረታውን በማስመልከት መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ካንሰር #በኢትዮጵያ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ? በበሽታው የተጠቂ ሰዎች ቁጥር ቀነሰ ወይስ ጨመረ ? ሲል ጥያቄ አቅርቧል።

የተቋሙ የቦርድ አባልና የውስጥ ደዌ ባለሙያው ዶክተር አስቻለው ወርቁ ምን አሉ ?

“ በጣም እየጨመረ ነው ያለው። ለመጨመሩ የተለያዩ ምክንያቶች ይኖራሉ። በአጠቃላይ ተላላፊ ያልሆኑ በሽዎች እየጨመሩ ነው። የካንሰር ህመምም እየጨመረ ነው።

ለምሳሌ፦ የሳንባ ካንሰርን ብናዬው ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ነው ያለው። የምንመረምረው ጥቂት ሰዎችን ስለሆነ በዚያችው ዳታ ተመርኩዘን ነው የምንገልጸው። ማኀበረሰቡን ያማከለ የዳሰሳ ጥናት ካልሰራን ቁጥሩን በትክክል መግለጽ ከባድ ነው።

10 ሰዎችን መርምሮ 5 ሕሙማን ቢገኝ 50 በመቶ ማለት አይቻልም። ምክንያቱም ያልተመረመሩ ብዙ ስለሚኖሩ። እንደ አጠቃላይ ካየነው ግን ፦
- የሳንባ፣
- የአንጀት፣
- የጉበት፣
- የማህፀን፣
- የደም ሴል ካንሰር ታማሚሞች ቁጥራቸው እጅግ ባጣም እየጨመረ ነው ያለው። ” ብለዋል።

ካንሰር ዋነኛ የሞት እና የስቃይ ምክንያት እየሆነ መምጣቱን ቁጥሮች እንደሚያመላክቱ ተገልጿል።

ለአብነት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከሞቱ ሰዎች ካንሰር የመገኘት እድሉ ከፍ ብሏል። ምክንያቱም የሳንባ ካንሰር ካሉት የካንሰር ዝርዝሮች ወደ 6ኛ ደረጃ ላይ ነው ያለው ተብሏል።

የማቲዎስ ወንዱ ካንሰር ሶሳይቲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንዱ በቀለ ምን አሉ ?

“ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትንባሆ መሸጥም መግዛትም እንዳይችል የሚነገርበት ጊዜ መቼ ነው ?

ትንባሆ ነክ ነገሮች፣ አልኮል በሽታውን እያስፋፉት ነው።
 
ከ3,000 በላይ የካንሰር ሕሙማንና ቤተሰባቸውን እረድተናል። በአሁኑ ወቅት 175 ለካንሰር ሕሙማንና ለቤተሰባቦቸው፦

° ከአገራቸው የሚመጡበት ሙሉ የትራንስፖርት፣
° ከውጪ የሚገዙ መድኃኒቶች፣ 
° በሆስፒታል ውጪ በግል ተቋማት ለሚሰሩ የላብራቶሪ ምርመራ፣ 
° ሆስፒታል ለተኙት ሕሙማን ለአንዳንድ ነገር መሸፈኛ በወር 1,000 ብር፣
° እየታከሙ ለሚማሩ ተማሪዎች በወር 1,000 ብር፣
° 24 አልጋ ባለው የካንሰር ሕክምና ማዕከል በየዕለቱ ለቁርስ፣ ምሳ፣ በክሰስና እራት ወጪዎችን እየሸፈንን ነው። ”

NB. ማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሰር ሶሳይቲ የአቶ ወንዱ በቀለ የ4 ዓመት ጨቅላ ልጃቸው በካንሰር በሽታ ሕይወቱ ማለፉን ተከትሎ ቤተሰቦቹ የደረሰባቸውን መሪር ሀዘን “ ማቲዎስ ቢሞትም ብዙ ማቲዎሶችን ማዳን እንችላለን ” በሚል መልካም አስተሳሰብ በመቀየር በ15 መስራች አባሎች ሚያዚያ 9 ቀን 1996 ዓ/ም የተመሠረተ ለካንሰር ሕሙማን የሕክምና አገልግሎት የሚሰጥ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ATTENTION🚨

" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ #እርግዝናን_ይፈራሉ "

ስለኤች አይቪ/ኤድስ ስርጭት የሚሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ከጊዜ ወደጊዜ እየተቀዛቀዘ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ገልጿል።

ችግሮች ከመባባሳቸው በፊት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ አሳስቧል።

ቫይረሱ ኢትዮጵያ መግባቱ ከተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶ በተሰራው እንቅስቃሴ ብዙ ለውጦች መመዝገባቸውን አስታውሷል።

ይሁን እንጂ የተመዘገቡት ለውጦች በተወሰነ ደረጃም ቢሆን መዘናጋት እንደፈጠሩ ፤ የሚዲያዎች ተሳትፎም መቀዛቀዙን ጠቁሟል።

በአሁኑ ወቅት ኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ትኩረት የሚሹና በይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ ብቻ ትኩረት ያደረጉ ናቸው ብሏል።

እነዚህም ፦
- ሴተኛ አዳሪዎች፣
- አደንዛዥ እፅ የሚጠቀሙ ሰዎች፣
- የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች፣
- አፍላ ወጣቶች በተለይ (ከማኅበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ)፣
- የቀን ሠራተኞች፣
- ከማኅበራዊ ችግሮች ጋር ተያይዞ ተጋላጭ የሆኑት እንደሆኑ አመልክቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የስርጭት መጠኑ ከ1 በመቶ በላይ ቢሆንም ከቦታ ቦታ በፆታ፣ በኅብረተሰብ ክፍል፣ በገጠርና በከተማ ከፍተኛ ልዩነት አለው ብሏል።

በከተሞች ያለው ስርጭት በገጠር ካለው በሰባት እጥፍ እንደሚበልጥም ጠቁሟል።

ይህንን ልዩነት መሠረት ያደረገ አጠቃላይ ማኅበረሰቡን ተደራሽ የሚያደርግ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ እየተከናወነ አይደለም ብሏል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፦
° የመጠጥ ቤቶች ፣
° የጫት ቤቶች
° በሺሻ ቤቶች መስፋፋት ሌላ ተግዳሮቶች እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጿል።

" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ እርግዝናን ይፈራሉ። የወጣቶች አዲስ የመያዝ ምጣኔ ጨመረ ባይባልም እየቀነሰ አይደለም፤ ይህ በራሱ ችግር ለመኖሩ አመላካች ነው "ም ብሏል።

በተለይ በወጣቶች በኩል ሁሉን አቀፍ ሥራ ባለመሠራቱ እንደ ሀገር ዋጋ ሊያስከፍሉ የሚችሉ አጋላጭ ባሕሪያት እየተስተዋሉ መሆኑን አመልክቷል።

የኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ ጠንካራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እንደሀገር ማከናወን እንደሚጠበቅ አሳስቧል። #ኢፕድ

@tikvahethiopia