TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.1K photos
1.4K videos
202 files
3.8K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጥቆማ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተለያዩ የሥራ መደቦች ሰልጣኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

✓ ሰልጣኝ አብራሪ/ፓይለት (Trainee Pilot)

✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ቴክኒሽያን
(Trainee Aircraft Maintenance Technician)

✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ሜካኒክ (Trainee Aircraft Mechanic)

✓ ሰልጣኝ የበረራ አስተናጋጅ (Trainee Cabin Cors)

✓ ሰልጣኝ የመንገደኛ አገልግሎት ኢጀንት (Trainee Customer Service Agent)

አመልካቾች ለምዝገባ ሊያሟሉ የሚገባቸው፦

የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውንና ኮፒው፣ የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ፣ የልደት ካርድ፣ የታደሰ የቀበሌ የነዋሪነት ማረጋገጫ ካርድ እና አንድ ጉርድ ፎቶግራፍ

አመልካቾች ከተዘረዘሩት የሥራ መደቦች ውስጥ ማመልከት የሚችሉት በአንዱ ብቻ ነው።

የምዝገባ ጊዜ፦

ከነሐሴ 15 እስከ 19/2015 ዓ.ም

የምዝገባ ቦታ፡-

➤ አዲስ አበባ በኦንላይን፣
➤ አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ደብረ ማርቆስኦኒቨርሲቲ፣
➤ ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ሮቤ ቲቺንግ ኮሌጅ፣
➤ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣
➤ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ

(ዕድሜ ፣ ቁመት እና ሌሎች ተያያዥ መረጀዎችን ከላይ በተያያዘው የተቋሙ ማስታወቂያ ይመልከቱ)

@tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች መታሰራቸው ተሰምቷል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ሰዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው መታሰራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሰሞኑን መሆኑንና አቶ ታምሩ ገምበታ ግን ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል።…
#Update

42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች መታሰራቸው ተገለፀ።

እንዚህ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ሊውሉ የቻሉት ፦
- ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣
- ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ
- ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተውጣጣ ግብረ-ኃይል ከሙስናና ሕገወጥ ተግባር ጋር በተያያዘ ክትትልና ምርመራ ሲያደርግ ከቆየ በኃላ ነው ተብሏል።

ተጠርጣሪዎቹ ፤ ተገልጋዮች በመደበኛ የመንግሥት ስርዓት የሚፈልጉትን የፓስፖርትና መሰል አገልግሎቶችን በአፋጣኝና በአነስተኛ ዋጋ ማግኘት ሲችሉ የፈጠሯቸው የተንዛዙና እና የተወሳሰቡ አሠራሮች ዜጎችን ለከፋ እንግልት ዳርገዋል ተብሏል። በተጨማሪ ላልተገባ ወጪ እንደዳረጉ ተመላክቷል።

ከፍተኛ ገንዘብ በመጠየቅ በሙስና ተግባር ተሰማርተው የግል ጥቅማቸውን ሲያሳድዱ ነበር ተብሏል።

የተሰጣቸውን ስልጣንና ኃላፊነት በመተው  ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ፦

- በዜግነት ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ የውጭ ሀገራት ዜጎች፣

- በወንጀል ተከሰው የጉዞ ሰነዳቸው ለታገደባቸውና ሐሰተኛ የማንነት መገለጫ ላላቸው ሕገወጦች ጭምር የፓስፖርት፣ ሊሴፓሴና ቪዛ አየር በአየር በመሸጥና በማስተላለፍ መንገደኞች በሌሉበት ጉዞ እንዳላቸው በማስመሰል እንዲሁም የጉዞ ሰነድ በማዘጋጀት ወደ ተለያዩ ሀገራት እንደተዘዋወሩ የሚገለፅ ማሕተም በማዘጋጀት ተግባር ተሰማርተው መገኘታቸው ተገልጿል።

በተጨማሪም ከሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ተመልምለው ያለፉ እንደሆኑ በማስመሰል ግለሰቦች ባልተገባ መንገድ ለሥራ ወደ ተለያዩ የዓረብ ሀገራት እንዲወጡ በማድረግ እንዲሁም የሕጋዊ ግለሰብን ፓስፖርት ፎቶግራፍ በመቀየር ከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀል ሲፈጽሙ ተደርሶባቸዋል ተብሏል።

እነዚህ ተጠርጣሪዎች ከአዲስ አበባ እስከ ክልሎች የጥቅም ትስስር  በመዘርጋት ሙስና  ሲፈጽሙ እንደቆዩ ተገልጿል።

ሐሰተኛ የማንነት መታወቂያዎችን በማዘጋጀትም ተግባር ላይ ተሰማርተው ከነበሩ የውጭ ሀገር ዜጎች ጋርም ግንኙነት በመፍጠር የወንጀል ተግባር ሲፈፅሙ ቆይተዋል ተብሏል።

ይህን ተከትሎም በተደረገ ክትትል ከ200 በላይ የሚሆኑ በሕገወጥ መንገድ የተዘጋጁ #ፓስፖርቶች እንዲመክኑ መደረጉና የወንጀል ድርጊቱም መንግሥትን በሚሊየን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሪ እንዳሳጣው ተገልጿል።

በዚህም ፦
- በአዲስ አበባ ከተማ፣
- ኦሮሚያ፣
- አማራ፣
- ሲዳማ፣
- ሶማሌ፣
- ጋምቤላ እና ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልሎች በወንጀሉ የተሳተፉ  በኢሚግሬሽንና ዜግነት  አገልግሎት ሲያገለግሉ የነበሩ ከከፍተኛ አመራርነት እስከ ባለሙያ ያሉ 42 ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል።

በወንጀል ድርጊቱ ተሰማርተው ከተገኙና በሕግ ቁጥጥር ስር ከዋሉ ተጠርጣሪዎች መካከል ፦

- የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ታምሩ ግንበቶ አዋልሶ
- ዘመድኩን ጌታቸው፣
- ከድር ሰዒድ ስሩር፣
- አስቻለው እዘዘው፣
- አብዱላሂ አሊ መሀመድ (አብዱላሂ ጃርሶ)፣
- ቴዎድሮስ ቦጋለ፣
- ጌትነት አየለ፣
-  ጀማል ገዳ፣
- ሙላት ደስታ፣
- ጅላሎ በድሩ፣
- ገነት ኃ/ማርያም፣
- ደገፋ ቤኩማ ፣
- ወንድይፍራው ሽመልስ ገ/ሰንበት እና ሌሎችም ይገኙበታል።

በተያዙት ተጠርጣሪዎች ዙሪያ ምርመራ ይቀጥላል የተባለ ሲሆን  በግለሰቦቹ ዙሪያ ተጨማሪ  መረጃ ያላቸው ዜጎች ለፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ #ጥቆማ_መስጠት ይችላሉ ተብሏል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፤ በ2014 ዓ.ም እና 2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን የዩኒቨርስቲ መግቢያ መቁረጫ ውጤት ያመጡ እና በፖሊስ የሙያ ዘርፍ ሀገራቸውን ለማገልገል #የሚፈልጉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደሚፈልግ አሳውቋል።

ተቋሙ ለ4  አመታት በ " ፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ " አስተምሮ በመኮንንነት (ረዳት ኢንስፔክተር ማዕረግ) በማስመረቅ በተለያዩ የፌደራል ፖሊስ የስራ ክፍሎች አስመድቦ ለማሰራት እንደሚፈልግ ነው የገለፀው።

በተጨማሪ በ "ፎረንሲክ ሳይንስ ዲግሪ" አስተምሮ በመኮንንነት (ረዳት ኢንስፔክተር ማዕረግ) በማስመረቅ በፎረሲክ ምርመራ የላብራቶሪ ሙያተኝነት (ኤክስፐርት) በማስመደብ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡

በተቋሙ በ  " ፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ " ለመማር የሚያስፈልጉ የመመልመያ መስፈርቶች ከላይ በምስሉ የተዘረዘሩ ሲሆን ከነሱም ውስጥ ፦

- አመልካቾች ከማንኛውም ወንጀል ነፃ ስለ መሆኑ ከሚኖርበት ወረዳ ፖሊስ ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው።

- ለፖሊስ አካል ብቃት ስልጠና ብቁ የሆነ አካላዊ አቋምና አዕምሮ ጤንነት ያላቸው ሊሆኑ ይገባል።

- በ2014 ዓ/ም እና 2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባ የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስተር መቁረጫ ውጤት ያላቸው  የትምህርት ማስረጃቸውንም ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።

- የ #ሪሚዳል_ትምህርት ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡ ከሆነም ማስረጃ ማቅረብ አባቸው።

- አመልካቾች እድሜያቸው ከ18 እስከ 28 ዓመት መሆን አለበት።

- ቁመት ለወንድ 1.65 እና ከዚያ በላይ፣ ለሴት 1.55 እና ከዚያ በላይ፣
ሲሆን የተስተካከለ የሰውነት ክብደት 18.5-24.9 kg/m) ያለቸው ሊሆኑ ይገባል።

- ከተመረቁ በኋላ 7/ሰባት/ አመት በተማረበት የፖሊስ ሙያ በየትኛውም የአገሪቱ ክልልና የፖሊስ የስራ መደቦች ላይ ተመድቦ ለመስራት ፍቃደኛ መሆን አለበት።

- ሴት አመለካቾች ከእርግዝና ነፃ መሆን አለባቸው።

- ሁሉም አመልካቾች ከዚህ በፊት የፖሊስ ወይም የመከላከያ ሰራዊት ስልጠና ያልወሰዱ መሆን ያለባቸው ሊሆኑ ይገባል።

ለ " ፎረንሲክ ሳይንስ ዲግሪ " ከላይ ያሉት አብዛኛው መስፈርቶች እንደተጠበቁ ሆነው ፦
- ዜግነት #ኢትዮጵያዊ
- የ12ኛ ክፍል #በተፈጥሮ_ሳይንስ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በ2014 ዓ/ም እና በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን መቁረጫ ውጤት ያላቸው
- በተፈጥሮ ሳይንስ የሪሚዳል ትምህርት ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል።

በሁለቱም የዲግሪ ትምህርት ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን የሚቀላቀሉት በራሱ በተቋሙ የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና ማለፍ ሲችሉ ብቻ ነው።

የት እና እስከመቼ መመዝገብ ይቻላል ?

ማመልከት የሚቻለው እስከ ጥቅምት 22/2016 ዓ/ም ድረስ ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት ነው።

ተማሪዎች በአካባቢያቸው በሚገኝ በሁሉም የክልል እና የከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽኖች በአካል በመገኘት መመዝገብ ይችላሉ።

ለመዝገባው የትምህርት ማስረጃቸውን የ8ኛ ፣ የ10ኛና 12ኛ ክፍል ካርድ እና ትራንስክርፕት ኦርጅናል ከማይመለስ አንድ ፎቶ ኮፒ ጋር ይዘው መቅረብ አለባቸው።

#ደመወዝ / #ክፍያን በተመለከተ

ዕጩ መኮንኖች በትምህርት ላይ በሚቆዩበት ጊዜያት ከ3 ወር የሙከራ (recruit) ጊዜ ቆይታ በኋላ እስከሚመረቁ ድረስ የኪስ ገንዘብ/ደመወዝ ታስቦ ይከፈላቸዋል ተብሏል።

ስልክ ካስፈለጋችሁ ፡ 0116735564

(ተጨማሪ ዝርዝር ጉዳዮችን ከላይ በምስሉ ያንብቡ)

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የኢሰመኮ 3ኛ ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፎች እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር ላይ ተሳተፉ !

መኖሪያ ቤት/ቦታ ማለት ለአንድ ሰው ወይም ለአንድ ቤተሰብ ምን ማለት ነው ?

ሕይወት፣ ትርጉም ያለው ሕይወት፣ ምንድን ነው ? የአንድ ኢትዮጵያዊት ሴት፣ ወይም የአካል ጉዳተኛ ወይም የተፈናቃይ ወይም የአረጋዊ ሕይወት ምን ይመስላል ?

በሕይወት እና በመኖሪያ ቤት ዙርያ እነዚህን እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች ለኪነጥበብ አፍቃሪዎች፣ ለኪነጥበብ ሙያ ተማሪዎች፣ ባለሞያዎች እና አማተሮች እንዲሁም ለመገናኛ ብዙኃን አባላት እና ሌሎችም በኪነጥበብ እና በሰብአዊ መብቶች መካከል ያለውን ትስስር ማሳየት ለሚፈልጉ ሁሉ፣ በኢሰመኮ አዘጋጅነት በሚካሄደው የ3ኛው ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር የቀረቡ ናቸው።

ኑ፣ ተሳተፉ፣ አብረን እንድናሰላስል የሚረዱ የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልም ሥራዎቻችሁን ለዕይታ አቅርቡ!
በውድድሩ ለመሳተፍ እና ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ዝርዝሩን በዚህ ይመልከቱ - https://bit.ly/46sReAw
#ጥቆማ

የኢሰመኮ 3ኛ ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፎች እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር ላይ ተሳተፉ !

መኖሪያ ቤት/ቦታ ማለት ለአንድ ሰው ወይም ለአንድ ቤተሰብ ምን ማለት ነው ?

ሕይወት፣ ትርጉም ያለው ሕይወት፣ ምንድን ነው ? የአንድ ኢትዮጵያዊት ሴት፣ ወይም የአካል ጉዳተኛ ወይም የተፈናቃይ ወይም የአረጋዊ ሕይወት ምን ይመስላል ?

በሕይወት እና በመኖሪያ ቤት ዙርያ እነዚህን እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች ለኪነጥበብ አፍቃሪዎች፣ ለኪነጥበብ ሙያ ተማሪዎች፣ ባለሞያዎች እና አማተሮች እንዲሁም ለመገናኛ ብዙኃን አባላት እና ሌሎችም በኪነጥበብ እና በሰብአዊ መብቶች መካከል ያለውን ትስስር ማሳየት ለሚፈልጉ ሁሉ፣ በኢሰመኮ አዘጋጅነት በሚካሄደው የ3ኛው ዙር የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር የቀረቡ ናቸው።

ኑ፣ ተሳተፉ፣ አብረን እንድናሰላስል የሚረዱ የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልም ሥራዎቻችሁን ለዕይታ አቅርቡ!
በውድድሩ ለመሳተፍ እና ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ዝርዝሩን በዚህ ይመልከቱ - https://bit.ly/46sReAw
#ጥቆማ #ከጠቀማችሁ

የአዳማ ጉምሩክ ኮሚሽን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ተወርሰው የሚገኙ 171 ተሽከርካሪዎችን በግልፅ ጨረታ ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። ተጨራቾች የጨረታ ሰንድ በመግዛት በጨረታው ላይ የሚወጡትን ተሽከርካሪዎች በአካል በመመልከት መጫረት ትችላላችሁ ተብሏል። ጨረታው በ26/02/2016 ዓ/ም ጥዋት 4 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4:15 ላይ የጨረታ ሳጥኑ ይከፈታል። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ 0221118429 ላይ መወደል ይቻላል።

አዲስ አበባ ቃሊት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የተተው፣ የተወረሱ እና በኮንትሮባንድ ተይዘው የሚገኙ የተለያዩ የቤትና የጭነት ተሸከርካሪዎች ፦
- DUMP TRUCK፣
- IVECO FIAT፣
- TOYOTA HAILUX፣
- TOYOTA COROLLA፣
- TOYOTA  VITZ፣
- TOYOTA HAICE፣
- TOYOTA YARIS፣
- TOYOTA CHR፣
- HYUNDAI፣
- SUZUKI፣
- MISTUBUSHI ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችን፣ የሞባይል ክፍሎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን፣ የተለያዩ የተዘጋጁ አልባሳትና ጫማዎች፣ የውብት መጠበቂያ ዕቃዎች እና ሌሎች የተለያዩ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅና በሃራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። የተጠቀሱት ተሸከርካሪዎች የጨረታ ሰነድ ከቀን 20/02/2016 ዓ.ም ጀምሮ ማግኘት ይቻላል።

(ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ በምስሉ ይመልከቱ)

  የገቢዎች ሚኒስቴር በታክስ ዕዳ የያዛቸውን ተሽከርካሪዎችና ሌሎች የተለያዩ ንብረቶች ለመሸጥ ይፈልጋል።

ከፎኔክስ ኢንደስትሪ ኃ/የ/የግ/ማህበር የተያዘ፦
- የኘላስቲክ ወንበር ማምረቻ ማሽን፣  የማሽኑ ማቀዝቀዣ (cooler)፣ የማሽኑ ጥሬ ዕቃዎችና ሌሎች ተጓዳኝ ዕቃዎች፣

ከተክለብርሃን አምባየ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተያዙ ፦
- የተለያዩ መጠን ያላቸው የመብራት አምፖሎች፣
- ፍሎረሰንቶች፣
- ፖውዛዎች እና የውሃ ተቀባሪና ተንጠልጣይ የተለያዩ ቧንቧዎች፣

🚘 ከቲ.አይ.ቢ ኬተሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህ እና ኦክስፎርድ አማልጌትድ ኃ/የተ/ የግ/ማህበር የተያዙ የተለያየ ሞዴል ያላቸውን 3 ተሽከርካሪዎች ናቸው።

(ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ በምስሉ ይመልከቱ)

#ጉምሩክኮሚሽን #አዲስዘመን #ገቢዎችሚኒስቴር

* ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በጥቆማ መልክ የቀረበ።

@tikvahethiopia
#NEBE

በገዛ ፍቃዳቸው ከኃላፊነታቸው በለቀቁት ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ምትክ አዲስ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ለመተካት 8 አባላት ያሉት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴ ዛሬ ተሰይሟል።

ይኸው ኮሚቴ የተሰየመው በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ነው።

የኢፌዴሪ ህገ መንግሥት አንቀጽ 102 እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ 1133/2011 አንቀፅ 5/1 ላይ በሰፈረው መሰረት #ጠቅላይ_ሚኒስትሩ ዕጩ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የሚመለምል ገለልተኛ ኮሚቴ እንደሚሰይሙ ይደነግጋል።

የተቋቋመው መልማይ ኮሚቴ ወደ ስራ መግባቱ የተነገረ ሲሆን በቅርቡ #ጥቆማ መቀበል እንደሚጀምር ተገልጿል።

የምርጫ ቦርድ ሰብሰቢ መልማይ ኮሚቴው ፦
- ቀሲስ ታጋይ ታደለ (ሰብሳቢ)
- ፕ/ር ተከተል ዮሐንስ (አባል)
- አቶ ባዩህ በዛብህ (አባል)
- ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ (አባል)
- አቶ ካሳሁን ፎሎ (አባል)
- ወይዘሮ ርግበ ገብረሃዋርያ (አባል)
- ወይዘሮ እንግዳዬ እሸቴ (አባል)
- ኢ/ር መላኩ እዘዘው (አባል)

መረጃው ከጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤት የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
#TOYOTA

ቶዮታ / Toyota ዓለም አቀፍ የመኪና አምራች ኩባንያ በዓለም ገበያ በዋነኝነት #በአሜሪካ የተሸጡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎቹን  ከገበያ ላይ እንዲሰበሰቡ አዟል።

ቶዮታ እንዲሰብሰቡ ያዘዘው ከ2020 እስከ 2022 ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የተመረቱ ተሽከርካሪዎችን ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ የ " ኤርባግ " ደህንነት ችግር አለባቸው ተብሏል።

ከ2020 እስከ 2022 ወደ ገበያ የቀረቡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎች (በዋነኝነት #አሜሪካ) ከ " ኤርባግ " ጋር በተያያዘ ችግር እንዳለባቸው ተደርሶበታል።

ችግሩ በፊት ለፊት ተሳፋሪ መቀመጫ በኩል በስህተት ከተሰራ የ " ኤርባግ ሴንሰር " ጋር የሚያያዝ ሲሆን ምናልባትም በአደጋ ጊዜ " ኤርባጉ " አገልግሎት ላይሰጥ ይችላል። ይህ አደጋ በሚፈጠር ጊዜ ኩዳቱ እንዲጨምር ያደርጋል።

ቶዮታ የትኞቹ ሞዴሎች ይሰብሰቡ አለ ?

#ቶዮታ

ኮሮላ (2020 - 2021)
ራቭ4 ፣ ራቭ4 ሃይብሪድ (2020 - 2021)
ሃይላንደር፣ ሃይላንደር ሃብሪድ (2020 - 2021)
አቫሎን ፣  አቫሎን ሃይብሪድ (2020 - 2021)
ካምሪ፣ ካምሪ ሃብሪድ (2020 - 2021)
ሴና ሀይብሪድ (2021)

#ሌክሰስ

ES250 (2021)
ES300H (2020-2022)
ES350 (2020-2021)
RX350 (2020-2021)
RX450H (2020-2021) የተሰኙ ከ2020 እስከ 2022 ላይ የተመረቱት የ " ኤርባግ " ችግር ስላለባቸው ይሰብሰቡ ብሏል።

ከላይ የተጠቀሱት ተሽከርካሪዎች ያላቸው ሰዎች ኤርባጋቸውን #እንዲያረጋግጡ እና ችግር ካጋጠማቸው እስከ ቀጣዩ የካቲት ወር ድረስ እንዲመልሱለት ቶዮታ ጥሪ አቅርቧል።

የቶዮታ ተሽከርካሪዎች ችግር እንዳለባቸው የታወቀው የጃፓን ትራንስፖርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ ተሽከርካሪ እምራች ኩባንያዎች ላይ ባደረገው #ምርመራ ላይ እንደሆነ ተገልጿል።

ይህን ተከትሎ የቶዮታ ኩባንያ አክስዮን ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል።

ምርመራው ከቶዮታ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ ዳይሀትሱ በተሰኘው ኩባንያ ላይም ተመሳሳይ ችግር መታየቱን ገልጿል።

ከ87 ዓመት በፊት ኪቺሮ ቶዮታ በተባለ ግለሰብ የተመሰረተው ቶዮታ የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ አሁን ላይ በዓመት 10 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎችን በማምረት ላይ ይገኛል።

ከ360 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያሉት ቶዮታ ኩባንያ 300 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ሀብት እንዳለው የኩባንያው ዓመታዊ ሪፖርት ያስረዳል።

#ጥቆማ ፦ ከደህንነት ጋር በተያይዘ በተለይም በአሜሪካ እንዲሰበሰቡ የታዘዙ ተሽከርካሪዎችን ቼክ ለማድረግ https://www.nhtsa.gov/recalls በዚህ አድራሻ መጠቀም ይቻላል። የመኪናውን መለያ ቁጥር (VIN) በማስገባት ማወቅ ይቻላል።

Credit - #AlAiN / #Reuters / #Toyota_News_Room

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ፤ የገና ሥጦታ ሎተሪ በትላንትናው ዕለት መውጣቱን ገልጿል።

10 ሚሊዮን ብር የሚያስገኘው የዕጣ ቁጥር 1616519 ሆኖ ወጥቷል።

አጠቃላይ የዕጣ ዝርዝሩ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
#የሥዕል_ውድድር #ጥቆማ

በመቐሌ እና አከባቢው የምትገኙ የሥዕል ችሎታ ያላችሁ ወጣቶች ሪድም ዘጀነሬሽን ከUSAID/OTI ጋር በመተባበር ላዘጋጀው የቡድን የስዕል ውድድር ላይ እንድትሳተፉ ጥሪ አቅርቧል።

ከዚህ ቀደም በሰላም ጉዳዮች ላይ ተከታታይ ውድድሮች ያካሄደው ሪድም ዘጀነሬሽን አሁን ደግሞ በመቐሌ ለሚገኙ ችሎታው ላላቸው እድሜያቸው 13 - 18 ላሉ ታዳጊዎችና 19 - 29 ላሉ ወጣቶች በአጠቃላይ ለ50 ተሳታፊዎች እድሉን አመቻችቷል።

ዘላቂ ሠላም፤ ጽናት፤ እንዲሁም የማኅበራዊ ችግሮችን ማከም በሚችሉ ኃሳቦች ላይ ተወዳዳሪዎች ተመርጠው የሥዕል ውድድሩ ላይ እንዲሳተፉ ይደረጋል። በውድድሩ የተመረጡ ሥራዎች በክልሉ በሚዘጋጁ ፎረሞች ላይ የሚቀርብ ይሆናል።

ፍላጎት ያላቸው አመልካቾች፥ እስከ ጥር 24 ድረስ ማመልከት የሚችሉ ሲሆን በተከታዩ ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።  https://forms.gle/qYmEMneTagoSgKVQA

ዝርዝር መስፈርቱን ለማግኘት https://telegra.ph/Art-as-a-path-to-Healing-01-29

@TikvahethMagazine