TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጥቆማ #YALI2023

የማንዴላ ዋሽንግተን ፌሎ ሺፕ ፕሮግራም የ2023 (Mandela Washington Fellowship) ማመልከቻ ዛሬ ክፍት ተደርጓል።

በአህጉሪቱ ያሉ ወጣቶች ተወዳድረው #በአሜሪካ ሀገር በሚደረግ ሥልጠና ላይ እንዲሳተፉ እድሉ ተመቻችቶላቸዋል።

ከዚህ ቀደም በርካታ #ኢትዮጵያውያን ወጣቶች እድሉን ተጠቅመው ይህንን ሥልጠና ወስደዋል።

በሥልጠናው ላይ ለመሳተፍ የሚያስፈልጉትን መስፈርቶችን ለማየትና ለማመልከት ይህን ይጫኑ👇
https://www.mandelawashingtonfellowship.org/apply/

👉 Application Timeline :

• August 16, 2022 | Application opens

• September 13, 2022 | Application deadline

• November 2022 – January 2023 | Semi-finalists interviewed by local U.S. embassies and consulates

• March 2023 | Applicants are notified of their status

• May 2023 | Visa processing and Pre-Departure Orientations for Finalists

June 2023 | Fellowship begins in the United States

Via @tikvahethmagazine
ቪዲዮ ፦ ከላይ የምትመለከቱት #በአሜሪካ ሀገር ፣ ፊላደልፊያ በአንድ የ " አይፎን ስቶር " ላይ ከቀናት በፊት የተፈፀመ ዘረፋ ነው።

ነገሩ እንዲህ ነው በርካታ #ጭምብል የለበሱ እና ያለበሱ ሰዎች የአፕል ስትሮን በኃይል ሰብረው ይገባሉ።

በኃላ ውስጥ የነበሩ ለእይታ የቀረቡ #ሁሉንም አዳዲሶቹን የ " አይፎን 15 " ምርቶች እና ሌሎች የአፕል ቴክኖሎጂ ውጤቶችን " free iPhone " እያሉ እየጮሁ ይወስዳሉ።

ከአፕል ስቶር ስልኮቹን ይዘው ከወጡ በኃላ አንድ ድምፅ ይሰማሉ ፤ ስልኩ አገልግሎት እንደማይሰጥ እንዲሁም ስልኩን የያዘው ሰው ላይ ክትትል እንደሚደረግ ስልኩ ላይ በተመለኩት ፅሁፍ ይረዳሉ።

በየአፕል ስቶር ውስጥ ለማሳያ የሚቀመጡት አይፎን ስልኮች ለሽያጭ ከሚቀርቡት አይፎኖች ላይ ከሚጫነው ሶፍትዌር በተለየ ልዩ ሶፍትዌር የሚጫንባቸው ናቸው።

ይህን ሲገነዘቡ " አይፎን 15 " ስልኮቹን ጥቅም እንዳይሰጡ አድርገው ወደ መሬት እየጣሉ #ይሰባብራሉ። የውሃ መውረጃ ትቦ ውስጥም ይጨምራሉ።

ፖሊስ ደርሶ በዘረፋው ላይ የተሳተፉትን በቁጥጥር እንዳዋለ ተነግሯል። በርካታ ሰዎች መታሰራቸውን ፖሊስ አሳውቋል።

ድርጊቱ ብዙ የአሜሪካ ዜጎችን በማህበራዊ ሚዲያ እያናጋገረ እና እያወያየ ሲሆን አንዳንዶች በዘረፋ ድርጊት ፈፃሚዎች ላይ ላልቷል ያሉትን ህግ ሲተቹ ታይተዋል።

@tikvahethiopia
#TOYOTA

ቶዮታ / Toyota ዓለም አቀፍ የመኪና አምራች ኩባንያ በዓለም ገበያ በዋነኝነት #በአሜሪካ የተሸጡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎቹን  ከገበያ ላይ እንዲሰበሰቡ አዟል።

ቶዮታ እንዲሰብሰቡ ያዘዘው ከ2020 እስከ 2022 ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የተመረቱ ተሽከርካሪዎችን ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ የ " ኤርባግ " ደህንነት ችግር አለባቸው ተብሏል።

ከ2020 እስከ 2022 ወደ ገበያ የቀረቡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎች (በዋነኝነት #አሜሪካ) ከ " ኤርባግ " ጋር በተያያዘ ችግር እንዳለባቸው ተደርሶበታል።

ችግሩ በፊት ለፊት ተሳፋሪ መቀመጫ በኩል በስህተት ከተሰራ የ " ኤርባግ ሴንሰር " ጋር የሚያያዝ ሲሆን ምናልባትም በአደጋ ጊዜ " ኤርባጉ " አገልግሎት ላይሰጥ ይችላል። ይህ አደጋ በሚፈጠር ጊዜ ኩዳቱ እንዲጨምር ያደርጋል።

ቶዮታ የትኞቹ ሞዴሎች ይሰብሰቡ አለ ?

#ቶዮታ

ኮሮላ (2020 - 2021)
ራቭ4 ፣ ራቭ4 ሃይብሪድ (2020 - 2021)
ሃይላንደር፣ ሃይላንደር ሃብሪድ (2020 - 2021)
አቫሎን ፣  አቫሎን ሃይብሪድ (2020 - 2021)
ካምሪ፣ ካምሪ ሃብሪድ (2020 - 2021)
ሴና ሀይብሪድ (2021)

#ሌክሰስ

ES250 (2021)
ES300H (2020-2022)
ES350 (2020-2021)
RX350 (2020-2021)
RX450H (2020-2021) የተሰኙ ከ2020 እስከ 2022 ላይ የተመረቱት የ " ኤርባግ " ችግር ስላለባቸው ይሰብሰቡ ብሏል።

ከላይ የተጠቀሱት ተሽከርካሪዎች ያላቸው ሰዎች ኤርባጋቸውን #እንዲያረጋግጡ እና ችግር ካጋጠማቸው እስከ ቀጣዩ የካቲት ወር ድረስ እንዲመልሱለት ቶዮታ ጥሪ አቅርቧል።

የቶዮታ ተሽከርካሪዎች ችግር እንዳለባቸው የታወቀው የጃፓን ትራንስፖርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ ተሽከርካሪ እምራች ኩባንያዎች ላይ ባደረገው #ምርመራ ላይ እንደሆነ ተገልጿል።

ይህን ተከትሎ የቶዮታ ኩባንያ አክስዮን ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል።

ምርመራው ከቶዮታ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ ዳይሀትሱ በተሰኘው ኩባንያ ላይም ተመሳሳይ ችግር መታየቱን ገልጿል።

ከ87 ዓመት በፊት ኪቺሮ ቶዮታ በተባለ ግለሰብ የተመሰረተው ቶዮታ የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ አሁን ላይ በዓመት 10 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎችን በማምረት ላይ ይገኛል።

ከ360 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያሉት ቶዮታ ኩባንያ 300 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ሀብት እንዳለው የኩባንያው ዓመታዊ ሪፖርት ያስረዳል።

#ጥቆማ ፦ ከደህንነት ጋር በተያይዘ በተለይም በአሜሪካ እንዲሰበሰቡ የታዘዙ ተሽከርካሪዎችን ቼክ ለማድረግ https://www.nhtsa.gov/recalls በዚህ አድራሻ መጠቀም ይቻላል። የመኪናውን መለያ ቁጥር (VIN) በማስገባት ማወቅ ይቻላል።

Credit - #AlAiN / #Reuters / #Toyota_News_Room

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሩዋንዳ ዛሬ የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ (ጄኖሳይድ) 30ኛ ዓመት መታሰቢያ ነው። በ1994 እ.አ.አ ሩዋንዳ ውስጥ በቱትሲ ጎሣ ላይ የደረሰው የዘር ማጥፋት ዘመቻ በሰው ልጆች ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከደረሱት አሰቃቂ የዘር ጭፍጨፋዎች አንዱ ነው። በ100 ቀናት ገደማ ውስጥ ብቻ ከ800,000 እስከ 1,000,000 የሚሆኑ ሰዎች እንዳለቁ ይገመታል። ከተገደሉት ሰዎች መካከል አብዛኞቹ ቱትሲዎች ናቸው፤ ሆኖም…
በሩዋንዳው #ጄኖሳይድ ወቅት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አደረገ ?

ከ800 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች ባለቁበት የሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ ወቅት የዓለም መሪዎች ምንም እንኳን ስለ ዘር ጭፍጨፋው (ጄኖሳይድ) ቢያውቁም ጣልቃ አልገቡም ነበር።

ለረጅም ጊዜ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ' ጄኖሳይድ ' የሚለውን ቃል ከመጠቀም ተቆጥቦ ነበር ፤ ይህም #በአሜሪካ ጫና እንደሆነ ይነገራል።

አሜሪካም ወታደሮቿን ወደ ሩዋንዳ ለመላክ ያልፈለገች ሀገር ናት።

የቀድሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ሃላፊ ባን ኪሙን በ20ኛው ዓመት የዘር ጭፍጨፋው መታሰቢያ ወቅት " ድርጅቱ የዘር ማጥፋት ወንጀሉ  መከላከል ባለመቻሉ አሁንም ድረስ ያፍራል " ሲሉ ተናግረው ነበር።

ጭፍጨፋው ከመጀመሩ በፊት (እኤአ በ1994 መጀመሪያ ላይ) ተመድ ወደ ሩዋንዳ የላከው ኃይል UNAMIR አዛዥ ጄኔራል ሮሜዮ ዳላይር ስለ ግድያው / ጭፍጨፋው በቂ የደህንነት መረጃ ደርሶት ነበር። በሁቱዎቹ የተከማቸ ሚስጥራዊ የጦር መሳሪያ (እንደ ገጀራዎች) እንዳለ አውቆ ነበር። 

ከጥር እስከ መጋቢት ወር ድረስ 5 መልዕክቶችን ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ልከዋል።

በዚህም በሩዋንዳ ያላቸው ተልእኳቸው እንዲሰፋ ሁቱዎች ያከማቿቸው መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ እና የተመድ የሰራዊት ቁጥር እንዲጨምር ቢጠይቁም እዛ ያሉት ሰዎች ግን ማስጠንቀቂያዎቹን ችለ ብለው ትተዋቸዋል።

ግድያው ሲጀመር ተመድ እና የቤልጂየም መንግሥት የUNAMIR ሰላም አስከባሪዎችን አስወጡ።

የፈረንሳይ እና የቤልጂየም ሰላም አስከባሪዎች ቱትሲዎችን ለመርዳት ፍቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረት በተሽከርካሪ የነበሩ የሌላ ሀገር ዜጎችን አስወጥተዋል።

ሳይወጡ የቀሩና ትንሽ የተረፉ የተመድ ኃይሎች በኪጋሊ ውስጥ እንደ " ሆቴል ዴ ሚሌ ኮሊንስ " እና " አማሆሮ ስታዲየም " ባሉ ቦታዎች የተሸሸጉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ጥበቃ አድርገዋል።

በአንድ አጋጣሚ ግን በኪጋሊ ኢኮሌ ቴክኒክ ኦፊሴሌ (የቴክኒክ ት/ቤት) የተጠለሉ 2,000 ሰዎችን የሚጠብቁ ወታደሮች ቦታቸውን የውጭ ዜጎችን ለማስወጣት ሲሉ ቦታቸውን ለወቀው ሲወጡ በትምህርት ቤቱ እልቂት / ጭፍጨፋ ተፈፅሟል።

ቱትሲዎችን ለማጥፋት እቅድ እንዳለው እያወቀች የፕሬዝዳንት ሃብያሪማናን መንግሥት ስታስታጥቅ የከረመችው ፈረንሳይ በግድያዎቹ የመጀመሪያ ቀናት ጭምር ከሁቱ መንግስት ጋር መተባበሯን ቀጥላ ነበር። RPFንም ለፍራንስ አፍሪካ ግንኙነት ጠንቅ ነው ብላ ታስብ ነበር።

በመጨረሻ ተመድ ግንቦት 17/1994 በሩዋንዳ ላይ የጦር መሳሪያ እገዳ ጣለ፣ UNAMIRን ለማጠናከር ውሳኔ አሳለፈ። እስከ ሰኔ ድረስ ግን አዲስ ወታደሮች ሩዋንዳ መግባት አልጀመሩም ነበር።

ይህ ሁሉ እስኪሆን አብዛኛው ግድያ ተፈጽሞ ነበር።

የምዕራቡ ዓለም የሚዲያዎችም ጭፍጨፋውን “ የእርስ በርስ ” ወይም “ የጎሳ ” ጦርነት በማለት ነው ሲገልጹ የቆዩት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Rwandan genocide
Apr 7, 1994 – Jul 15, 1994
Al Jazeera

@tikvahethiopia