TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update መቀለ⬇️

ህወሓት “የፖለቲካ #መስመሩን የመቀየር ዕቅድም ሆነ ምክንያትም የለኝም” ሲል አስታውቋል።

አራተኛ ቀኑን ያስቆጠረው 13ኛው የህወሓት ጠቅላላ ጉባዔ #በመቀለ እየተካሄደ ሲሆን፤ ድርጅቱ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አቶ #ጌታቸው_ረዳ እንደተናገሩት፤ የፖለቲካ መስመር የሚወሰነው በዋናነት የቆመለት የህብረተሰብ ክፍል የደረሰበት የዕድገትና የለውጥ ደረጃ ነው፡፡

ህወሓት ደግሞ ሰፊውን ገበሬና ደሃውን ለሚወግነው ልማታዊ ዴሞክራሲ መስመር የሚያራምድ ነው። ህወሓት የእነዚህን የህብረተሰብ ክፍሎች የኑሮ ሁኔታ የመለወጥ ዓላማ ይዞ የሚንቀሳቀስ አስተሳሰብ አለው ያሉት አቶ ጌታቸው፤ ይህንንም በሚፈለገው ደረጃ እንደለወጠ ዕምነት ያለው ድርጅት ሲሆን ብቻ ነው የአስተሳሰብ መስመሩን #ሊቀይር የሚችለው ሲሉ አብራርተዋል፡፡

ህወሓት ተራማጅ አስተሳሰብ የሚያራምድ ድርጅት በመሆኑ መሻሻል ያለባቸው ፖሊሲና ስትራተጂዎች ካሉ ግን የህዝቦችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሚችል መልኩ ማስተካከያ እያደረገ ይራመዳል ሲሉ ጠቁመዋል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬሥ ድርጅት
@tikvahethiopia @tsegabwolde