الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
22.9K subscribers
356 photos
16 videos
7 files
907 links
﴿وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً﴾

ለማንኛዉም አስተያየት☞☞ @Tidarbaislam_bot
ለይ ያድርሱን

ለጥያቄ ☞☞ t.me/Hayatbintkedir
Download Telegram
🩸🩸🩸🩸🩸🩸🩸🩸

👉👉ክፍል አንድ👈👈

👉ውድ እህቴ ለአላህ ብለሽ አምብቢው ምን አልባት አንቺ ከዚህ የሀራም ፍቅር ግኑኝነት እርቀሽ ሊሆን ይችላል ግን ብዙ እህቶችሽ ገብተውበታል
እናም ላንችም እውነታውን እውቂው እህቶችሽንም የማስታወስ ግዴታ አለብሽ።
👉መጥፎ ሲሰራ እያየን ዝም ካልን የአላህ ቁጣ ለኛም ይተርፋል።
ነገም በአላህ ፊት እንጠየቅበታለን።
በቀላሉ መልክቱን በቻልነው ሼር ለማድረግ እንሞክር የኛ ግዴታ ማስታወስ ነው የፈለገውን መምራት የፈለገውን ማጥመም የአላህ ስራ ነው።
☞ አንቺ ጠልተሽው እርቀሽው ላንቺ የጠላሽውን ለእህቶችሽም እስካልጠላሽ ድረስ ሙሉ አማኝ ልትባይ አትችይም እናም ፅፍሁፉን በውስጥ መስመርም ሼር በማድረግ ግዴታችንን እንወጣ።
መልክቱ አንገብጋቢና ወቅታዊ ችግር ነው በትግስት አምብበሽ ቆም ብለሽ ማገናዘብ ይኖርብናል።
ፅሁፉ ስለረዘመብኝ በክፍል አምስት ለመጨረስ ሞክሪያለው

👇የሀራም ፍቅር👇

ክፍል አንድ ①

ውድ እህቴ የሀራም ፍቅር ግኑኝነትን በጣም በሩቁ ልትጠነቀቂው ይገባል ምክንያቱም በዚህ ሰዓት ብዙ እህቶችሽ እየተፈተኑበት የሚገኙው ከባድና አስቸጋሪ ፊትና ነው አሁን ባለንበት ዘመን የተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች ተበራክተዋል ለምሳሌ ዋሳፕ ፌስቡክ ኢሞ ቴሌግራም እና መሰል ሚዲያ አፖች በነዚህ ቴክኖሎጂዎች ከሚመጡ ፊትና እራስሽን ማራቅ ይኖርብሻል።
ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ብዙ እህቶች በነዚህ ሶሻል ሚዲያዎች ከተለያዩ ወጣቶች ጋር የሀራም ፍቅር ግኑኝነት ፈጥረዋል
ለምን እህቶች ተብለው ሲጠየቁ ምን ችግር አለው ለቀልድ ለመዝናናት እና ጊዜ ለማሳለፍ ብቻ ነው ብለው ይመልሳሉ
ይሄንንስ የሀራም የቀልድ ግኑኝነት እንድትቀርቢው ማን ነው የፈቀደልሽ
ውድ እህቴ ይሄ ሀራም ነው ሀራም ነው።
እድግመዋለው ሀራም ነው አላህን ፍሪ።
እንዲህ አይነቱ የሀራም ፍቅር ግኑኝነት በጥብቅ የተከለከለ ነው እስከዛሬም ወደፊትም በሸሪዓው አልተፈቀደም።
እንደውም ከከባባድ ወንጀሎች ሊመደብ ይችላል ምክኛቱም እህቴ ያን ሚስኪን ወጣት በለስላሳው ድምፅሽና አንደበትሽ ተስፋን ሰጠሽ ፍተና ላይ ትጥይዋለሽ
በአላህ ይሁንብኝ ስንትና ስንት ወጣቶች ናቸው በሀራም ቆሻሻ ተግባራቶች ላይ የወደቁት ምክንያቱን ሲናገሩ እንደምንሰማው በእከሌ ምክንያት ተፈትኜ እከሌ ፊት ባትሰጠኝ እከሌ ባታማልለኝ ኖሮ እንዲህ አልሆንን ነበር ይላል
እና መሰል የፊትና ሰበቦች ከፊታቸው እያመጣሽባቸው ስለሆነ ነው።
ወድ እህቴ ከየትኛውም አይነት ወጣት ጋር የሶሻል ሚዲያ ሀራም ፍቅር ግኑኝነት ሚባለውን በጣም ልትጠነቀቂው ይገባል በጣም ተጠንቀቂ በቃ ፍቅር አይደለም ብለሽ ልታወሪም አይገባም መንገዱን ዝጊው።

#የመጀመሪያው እውነታ አድምጭኝ ውድ እህቴ አንችን ሊወድሽ ይችላል ግን ካንችም ውጭ አስር ሌሎች ሴቶችንም ይወዳል ይህ ማለት አንችም ላይ ይጫወታል ካንችም ውጭ ብዙ ሴቶች ጋር ግኑኝነትን ይፈጥራል።
ይህ የመጀመሪያው እውነታ ነው።

#ሁለተኛው ደግሞ ምንም ጋብቻ ሚባለውን ነገር አያስበውም አላማውም ግቡም የለውም ይህ ማለት ወደ ጋብቻ አይገፋፋሽም ሀሳቡም የለውም እንደውም ካንች ጀርባ ሁኖ ስላንች ብዙ ያወራል።
ከኔ ውጭ ሌላ ውንድ ጋር እያወራች ከሀዲ ናትኮ እያለ ስምሽን ያጠፈዋል ግን በተዘዋዋሪ እሱም አንችን ይከዳሻል።

#ይቀጥላል
ይቀጥላል

ለአላህ ብለን ሼር እናርገው ቢያንስ በውስጥ መስመር ለምናውቃቸው እንላክላቸው።

ሼር ሼር


💍::::::::::::ቴሌግራማችን:::::::::::::💍

https://t.me/joinchat/AAAAAEOFD8pkvHISwAMj2w
🚫:::::::::::የሃራም ፍቅር:::::::::🚫

#ክፍል_ሁለት/2⃣

ሁሉም ሴት ልጅ ሊያነበው የሚገባ ተጨባጭ የሆነ ትልቅ ምክር

በደምብ አዳምጭኝ
#ሥስተውኛ እውነታ አንችን የሱ ባሪያ ወይም ምርኮኛ የሚያደርግብሽ በሁለት ከባባድ ምክንያቶች ነው።
☞አንድኛው ያንች ፎቶዎች ካሉት ይህ ወንድ ልጅ የሚያስፈራራብሽ የመጀመሪያው ከባድ ሰበብ ነው። ይሄኔ አንች አቋምሽን እያለወጥሽ ትመጫለሽ ምክኛቱም ሌላ ነገር ለማድረግ አትደፍሪም እሱ የያዘብሽ ሚስጥራዊ ፎቶ ስላለ ትፈሪያለሽ።
☞ሌላው እባካችሁ ተጠንቀቁ እህቶች ፎቶ መላላክ ይቅርባችሁ እባካችሁ ለማንም ፎቶ አትላኩ ሌላው ይቅር የምትቀርቢያትና የምታምኛት ጓደኛሽ እንኳ ብትሆን ፎቶሽችን እንዳትልኪላት እስካሁን ከነበረም አስጠፊ ምክንያቱም በገዛ ፎቶሽ አሳልፋ ልትሰጥሽ ትችላለች።
በያዘችብሽ በገዛ ፎቶሽ ልታስፈራራሽ ትችላለች ፎቶ መላላክ ጭራሽ አስፈላጊ አይደለም በፍፁም ለማንም ፎቷችሁን መላክ የለባችሁም አንችን ከናፈቀችሽ ቤትሽ መጣ ትይሽ ከዛ ውጭ ፎቶ መላላክ አስፈላጊ አይደለም።
አሁኑኑ ማስጠፋት ይኖርብሻል አምናታለው ብለሽ አትሸወጂ ታማኝ ልትሆን ትችላለች ግን ጥሩ ነገር መስሏት ወይም እሷ ሳታውቅ ከሷ ስልክ ሌላ ሰው ሊወስደው ይችላል ለዚህ ደግሞ አንች እርግጠኛ መሆን አትችይም እሷንም ለመውቀስ ይከብድሻል ስለዚህ ነገሩን በማስረዳት ማስጠፋት ይኖርብሻል።

☞ሁለተኛው ከባድ ምክንያት ደግሞ ምን ግዜም በሚያወራሽ ነገር ልብሽን ያደክመዋል አንችን የሱ ለማድረግ ቀላል በሆኑ ነገራቶች ያሳምንሻል
በፍቅር ስሜታዊ በሆኑ የውሽት የእዝነት ቃላቶችና ፅሁፎች ባጭሩ ያታልልሻል።
ወዳዘጋጀልሽ ወጥመድ ያስገባሻል ያኔ ወደሱ ወጥመድ በገባሽ ግዜም የፈለገውን ነገር ያዝሻል አንችም በፍቅር ስለከነፍሽ ያዘዘሽን ቆሻሻ ነገር ትፈፅሚያለሽ አላህ ይጠብቀን ይሄኔ የሰውም የጅንም ሸይጧን ይጫወትብሻል።
ውድ እህቴ አንችኮ በሰላምና በተረጋጋ ሁኔታ የተቀመጥሽ ንፁህ ነበርሽኮ ለምን እንዲህ ያለ መከራና ስቃይ ውስጥ ትገቢያለሽ ለምን!?
ስንትና ስንት ሴቶች ናቸው በዚህ ሰዓት በእንደዚህ አይነት መከራ ውስጥ የሚገኙ
ስንስትና ስንት ሴቶች ናቸው በዛቻ ማስፈራሪያ ውስጥ የሚገኙ
ስንትና ስንት ሴቶች ናቸው ሚስጥራቸው አደባባይ ላይ የወጣባቸው
ስንትና ስንት ሰቶች ናቸው ክብረ ንፅህናቸውንና ማንነታቸውን ያረከሱ
ስንትና ስንት ሴቶች ናቸው በፀፀትና በቁጭት የሚገኙ ታዲያ ከነዚህ ሁሉ እህቶቻችሁ ትምህርት መውሰድ አትችይም ከነዚህ ሁሉ እህቶች ታሪክ መማር ማገናዘብና ማስተንተን አለብሽ።

#ይቀጥላል
ይቀጥላል

Share share

💍::::::::::::ቴሌግራማችን::::::::::💍

https://t.me/joinchat/AAAAAEOFD8pkvHISwAMj2w
🚫:::::::::የሀራም ፍቅር:::::::::::🚫

ክፍል 3⃣

ሁሉም ሴቶች ሊያነቡት ሚገባ ትልቅ ምክር

እህቶቸ በዚህ ሀራም ፍቅር ግኑኝነት የሚገኙ ወጣቶች ስለናንተ ምን እንደሚሉ ታውቃላችሁ ሴት ልጅኮ ከኛጋ ልክ እንደ ሲጋራ ናት ትርጉሙ ምን እንደሆነ ታቂያለሽ እንደ ሲጋራ ማለት መጦ መጦ ሲጨርስሽ መሬት ላይ ጥሎ ይረግጥሻል በዚህም አያቆምም
ሌሎች እህቶችሽ ጋ ሂዶ አስቀያሚ ነገሮችን ስላንች ይነግራቸዋል
ይሄ ሁሉ ነገር አንች ላይ እንዲደረግብሽ ካልፈለግሽ ከዚህ የሀራም ፍቅር እራቂ።
የታለ ዲንሽ የታለ ሀያእሽ የታለ ስነ ምግባርሽ የታለ የቤተሰብሽ መልካም አስተዳደግ ሁሉንም ነው የሚያጠፋብን ይሄ ትልቅ ወንጀል ነው
ትንሽም ብትሆን በሀራም ግኑኝነት መጀመር የለባችሁም።

አንዳንድ እህቶች አታካብድ ይሄኮ ቀላል ግኑኝነት ነው ጨዋታና መዝናኛ ብቻ ነው ይላሉ። በፍፁም ቀላል አይደለም በአላህ ይሁንብኝ ይህችን ቀላል ነው የምትለዋን መጨረሻ ብትሰሙ ታዝናላችሁ
አንዷ ግኑኝነት የጀመረችው በቀላል የፌስቡክና የቴሌግራም የፍቅር ቃላቶች ልውውጥ ነበር የጨረሰችው ግን ክብረ ንፅህናዋን ጭራሽ በማጠብቅበት ቦታና ሰዓት ለዚያ ለፌስቡክ ወጣት ነበር ያስረከበችው።
#ሱብሀናላህ
ምክንያቱም ይህ ግኑኝነት የጀመረችው በሀራም ነው።
#አላህ ሱብሀነ ወተዓላ የሸትጧንን ዱካ አትከታተሉ ነው ያለን ለምን ይመስልሻል ምክኛቱም ሸይጧን የሚያዝሽ የቆሻሻና የጥመትን መንገድ ነው ውድ እህቴ ነብያች ሰለላሁዓለይሂ ወሰለም የተናገሩትን ላስታውስሽ ይህችኮ አይን ዝሙትን ትሰራለች ዝሙቷም ሀራምን ማየት ነው።
ይህችም ጀሮ ዝሙትን ትሰራለች ዝሙቷም መጥፎ ነገርን መስማት ነው።
ከዛም በመጨረሻው ሀዲስ ብልትም ወይ እውነት ነው ብሎ ይቀበላል አልያም ይዋሻል።
ውድ እህቶቸ በመጀመሪያ ደረጃ አላህን ልንፍራ ይገባል አላህን እንፍራ የሆነ ቀን ወደድንም ጠላንም ከአላህ ፊት እንቆማለን የሰራነውን እንደምንጠየቅ ማሰብ ይኖርብናል የሰው ልጅ ከሞተ ቂያማው በሱ ላይ እንደሚቆም ማውቅ አለብን ቀብር ደግሞ የመጀመሪያው ቤታችን ነው።
ወይ የጀነት ጮፌ ይነጠፍልናል አልያም የእሳት ስለዚህ ውድ እህቴ ዱንያ የፈለገ እረጅም ብትመስልሽ ባጭር ጊዜ ውስጥ እንደምትጠፋ ማወቅ ይኖርብሻል።
ውድ እህቴ አላህ ሱብሀነወተዓላ መጨረሻሽን አሁን ባለሽበት የሀራም ግኑኝነት እንዲያደርገው ትፈልጊያለሽ በፍፁም አትፈልጊም አይደል ስለዚህ ይሄን የውሽት ፍቅር በእውነተኛው የሀላል ፍቅር ቀይሪው
አንድ ማወቅ ያለብሽ ነገር በሀራም የመጣ ወንድ ልጅ የፈለገ ቢምል ይዋሻል ከመዋሸት ወደኋላ አይልም።
እውነተኛው ሀላልን ፍላጊ ወንድ ወደ ቤተሰቦችሽ ሂዶ ስላንች የሚመለከተው ሰው በሸሪአዊ መንገድ ያናግራል ይጠይቃል የጋብቻንም ጉዳይ በቶሎ ያስጀምራል ።
ነገር ግን በዚህ ሶሻል ሚዲያዎዎች በሜሴጅ በስልክ በፌስቡክ የሚመጣ ወንድ ከመዋሸት እና በራሱም ባንችም ላይ በመጫወት ወደኋላ አይልም
ስለዚህ ውድ እህቴ በደምብ ልታስቢበት ይገባል።
ይሄን ሁሉ የተናገርኩበት ምክንያት ሳታውቁ ትቀራላችሁ ብየ ሳይሆን ለማስታወስ ነው።

#ይቀጥላል
ይቀጥላል

የምትወጃት እህት ካለችሽ ሼር አድርጊላት

💍:::::::::::::::ቴሌግራማችን:::::::::::::💍

https://t.me/joinchat/AAAAAEOFD8pkvHISwAMj2w
👉ክፍል ሁለት👈

↝የትንሹ ዚና አደገኝነት↜


↝ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡-
«እርሱ ያ በሁለት መንጋጋዎቹ መካከል ያለውን (ምላሱን) እና በሁለት ጭኖቹ መካከል ያለውን (ብልቱን) ለሚጠብቅ (ለሚቆጣጠር) ሰው እኔ ለርሱ ለጀነት ዋስ እሆነዋለሁ፡፡» (ሙስሊም)

በተጨማሪም ነብዩ (ﷺ) ለጀነት ዋስትናን ከሰጧቸው ስድስት ዓይነት ሰዎች መካከል አንዱ በሚናገርበት ጊዜ እውነትን የሚናገርና ብልቱን ከሐራም የሚጠብቅ ሰው ነው፡፡ ይህንኑ አስመልክቶ ዑባዳ ቢን ሣቢት (ረድየላሁ ዐንሁማ) እንዳስተላለፉት
↝ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡-
«እናንተ ለስድስት ሥራዎች ዋስትና ስጡኝ፣እኔም በጀነት ዋስትና እሰጣችኋለሁና፡
↦①ኛ አማና በተሰጣቸሁ ጊዜ (እማናውን ለባለቤቱ) መልሱ፤
↦②ኛ ቃል ኪዳን በተጋባችሁ ጊዜ ቃል ኪዳናቸሁን ሙሉት፤
↦③ኛ በምትናገሩበት ጊዜ እውነታውን ተናገሩ፤
↦④ኛ ብልቶቻችሁን (ከሐራም ነገር) ጠብቁ፣
↦⑤ኛ ዓይኖቻቸሁን (ዕይታችሁን) ዝቅ አድርጉ፤
↦⑥ኛ እጆቻቸሁን (ሌሎችን ከመጐዳትና ኃጢአትን ከመፈጸም) ጠብቁ፡፡»

(በይሀቂ) በተጨማሪም ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል፡-
«በአላህ እና በመጨረሻው ቀን የሚያምን ሰው መልካም ነገርን ይናገር አልያም ዝም ይበል፡፡»
(ቡኻሪና ሙስሊም)
☞«ብዙ ሰዎች እሳት የሚገቡት በአፋቸውና በብልታቸው ምክንያት ነው፡፡❗️» (ቲርሚዚ)


👉③/ የጆሮ ዚና አደገኛነት

ወሲባዊ ውይይቶችን ማዳመጥ፣ ወሲብ ቀስቃሽ ዘፈኖችን መስማት፣ በስልክና በሌሎችም የርቀት መገናኛ ዘዴዎች ስለወሲብ መስማትና ማዳመጥ፣ በሃራም መንገድ ከተቃራኒ ፆታ ጋር ማውራት (መጀናጀን) የወሲብ ፊልሞችን ማየት ክላሲካል ማጀቢያዎችን ማዳመጥ፣ ወዘተ ከጆሮ ዚና የሚቆጠሩ ናቸው፡፡❗️
ብዙውን ጊዜ ግን ከዚና ጋር የተያያዙ ድምጽ-ነክ ነገሮች ወደ ጆሮ የሚገቡት ዘፈንን በማዳመጥ በኩል ነው፡፡ እንደሚታወቀው ዘፈን ዛሬ ዛሬ የዚና ነዳጅ ሆኗል፡፡ አዎ❗️ ዘፈን ከዝሙት ዋና መዳረሻ መንገዶች አንዱ ከመሆኑም ባሻገር ልብን ያሸፍታል፤
በአድማጩ ልብ ላይም ኒፋቅን ያሰርጽበታል፡፡ ይህም በግለሰቦች ኢማናዊ ኃይላቸው ላይ ከፍተኛ ድክመትንና መንኮታኮትን ያስከትላል፡፡ ዘፈንን አስመልክተው ታላቁ ሊቅ ኢማም ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁሏህ) አል ፈዋኢድ ውስጥ እንዲህ ብለዋል፡-
«የዘፈን ፍቅርና የቁርኣን ፍቅር በእንድ ግለሰብ ልብ ውስጥ በጋራ አይቀመጡም፤
እንዱ ሌላውን የሚያስወጣው ቢሆን እንጂ፡፡»
አንድ ሌላ ሰለፍ ደግሞ እንዲህ ብለዋል፡- መሳም የወሲብ፣ ዘፈን የዝሙት፣ ማየት የፍቅር፣ በሽታ የሞት መነሻ እንደሆኑ ሁሉ ወንጀልም የክህደት መነሻ ነው፡፡»
(ኢማም ኢብኑል ቀይም አድ-ዳእ ወ አድ-ደዋእ ውስጥ እንደጠቀሱት)

👉④/ የእጅ ዚና ኣደገኛነት

↝ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡-
«ከናን እንዳትሁ ከዚያ ያቺን ለርሱ የተከለከለውን ሴት ከመንካት ይልቅ
»ንቅላቱ በብረት ወስፌ ሲሰፋ ይሻለዋል፡፡» (ጠበራኒ)

  ይህ እንግዲህ የእጅ ዚና ቅጣትን የሚመለከት ነው፡፡ ታዲያ ከዚህ የባሱ ጸያፍና ሕገ-ወጥ ድርጊቶች፡- ለምሳሌ መተቃቀፍ፣ መሳሳም፣ መተሻሸትና እንዲያም ሲል ወሲብን መፈጸም ከዚህ የከፉ ቅጣቶችን እንደሚያስከትሉ ከዚሁ መገመት ይቻላል፡፡ ለምሳሌ ሕገወጥ መሳሳምን በተመለከተ
↝ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡- «እርሱ ያ ያቺን ለርሱ ያልተፈቀደችውን ሴት ከምኞት ቢጋለ የወሲብ ስሜት) የተነሳ የሚነካት ሰው፣ በፍርዱ ቀን እጁ ከአንገቱ ጋር ታስሮ ይቀሰቀሳል፡፡ እርሱ ስሟት ከሆነ ከንፈሮቹ በእሳት ውስጥ ይቃጠላሉ፡፡ በመጨረሻም እርሱ ዝሙት ላይ ወድቆ ከሆነ ጭኖቹ እኔ ያልተፈቀደ ነገር ላይ ተኝቻለሁ ሲሉ በፍርዱ ቀን በርሱ ላይ ይመሰክራሉ፡፡
ከዚያም አላህ ከቁጣ የተነሳ ወደርሱ ይመለከታል፡፡ በዚህን ጊዜ የሰውየው የፊቱ ሥጋ (ተገሽልጦ) ይወድቃል፡፡ እርሱም በትዕቢት እኔ ፈጽም ይህንን አልሠራሁም የሚል ከሆነ ከዚያም ምላሱ እኔ ያልተፈቀደን ንግግር ተናግሬያለሁ ሲል ይመሰክርበታል፡፡
እጆቹም እኔ ያልተፈቀዱ ነገሮቸን ነክቻለሁ ይላል፡፡ ዓይኖቹም እኔ ያልተፈቀደውን ነገር አይቻለሁ ትላለች። እግሮቹም እኔ የሄድኩት ወደተከለከሉ ነገሮቸ ነበር ይላሉ፡፡ በመጨረሻም ብልቱ ያኔ በተግባር እዋልኩት ይላል፡፡
ጠባቂ መላእኮችን በተመለከተ አንዱ እኔ ሰምቻለሁ ሲል ሌላኛው ደግሞ ጽፌዋለሁ ይላሉ፡፡ በመጨረሻም አላህ እኔ ሁሉንም አውቃለሁ ነገር ግን ለርሱ
ደብቄለት ነው እንጂ ይላል፡፡
ከዚያም አላህ (ﷻ) ለመላኢኮቹ እርሱ ይቀጣ ዘንድ ወደ ጀሀነም እሳት ውሰዱት፡፡ የኔ ቁጣ በነዚያ ከኔ ምንም ሐያእ በማያደርጉት ላይ በረታች ይላል፡፡❗️ ይህም በአላህ (ﷻ) መጽሐፍ ውስጥ በእነሱ ላይ ምላሶቻቸው፣ እጆቻቸውና እግሮቻቸውም ይሥሩት በነበሩት (እኩይ) ነገር በሚመሰክሩባቸው ቀን (ከባድ ቅጣት አላቸው) ተብሎ ተጠቅሷል፡፡ (አን-ኑር 24፡24)» (ኢማም ዘሀቢ አል-ከባኢር ውስጥ እንደጠቀሱት)


በዑለሞች አተያይ የእጅ ዚና ሲባል የዘመኑ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ባዳ ሴቶችና ወንዶች የሚጻጻፉትና የሚላላኩት የተለያዩ ሕገወጥ መልዕክቶችም በዚህ ውስጥ ይጠቃለላሉ፡፡❗️ ስልክ ቁጥሮችን የሚፅፉትና ቴክስት ሜሴጆችን የሚጽፉ ጣቶችም ከእጅ ይቆጠራሉ፡፡ የሞባይል ስክሪኖችን የሚነካኩና በቀን ውስጥ በተደጋጋሚ ቻት ሴክስን፣ ፎን ሴክስንና የወሲብ ፊልምን ሳይቀር ጠቅ ጠቅ የሚያደርጉ ጣቶችም በዚሁ ውስጥ ይካተታሉ፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ይህ እውነታ ወደ ዓይን ዚና፣ ወደ ምላስ ዚና፣
ወደ ጆሮ ዚናና ወደሌሎችም ሁሉ በየፊናቸው በሚኖራቸው ተሳትፎ ልክ ይለጠጣታል፡፡❗️


🍂🍂🍂🍂

በክፍል ሦስት⇨
#የእግር_ዚና_አደገኝነት #ይቀጥላል

ሼር ማድረጋችሁ መብት ሳይሆን ግዴታ ነው። ሃላፊነት ሚሰማን ሰው እንሁን።❗️
ነብዩ ﷺ ከኔ አንዲትም አያ ብትሆን አስተላልፏት አላሉምንእ
እና ምን እንጠብቃለን ሼር እናድርገው እንጂ።
Co๓๓ent↝
@Jezakellah


ቀጣዩንና ሌሎችን ለማምበብ
ቤተሰብ ይሁኑን
የግድ ሊኖረዎት የሚገባ ቻናል ነው!
Join us on
telegram channel

👇 👇 👇 👇
https://t.me/joinchat/TFVBJ_TiBpFmNGI0
👍 👆 👍
https://t.me/latekrebu_zina
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
بسم الله الرحمن الرحيم! ☞:::::እህቴ::::::☜ ክፍል አንድ/ ① ያቺን የዱንያ ህይወት ላይ ፈጣ የቀረችን ዐይንን ላናግራት.. አንቺ ዐይን ሆይ! ጀነትን አስታዉሺ! ያቺን ዱንያን ያፈቀረችን፣ ሀሳቧም ግቧም ዱንያ ብቻ የሆነችን ልብ ላናግራት.. አንቺ ልብ ሆይ! ጀነትን አስታዉሺ! ያቺን ዱንያ ላይ መንጠልጠል ያቃጠላትን፣ ደስታዋም ሀዘኗም ከዱንያ ጋር የተያያዘዋን ነፍስን ላናግራት..…
☞:::::::እህቴ::::::::☜

ክፍል ሁለት/ ②

ፊርዖዎን ያቺን ከስሮቿ ወንዞች የሚፈሱባትን፣ ያቺን በቅንጡ ፎቆች የተጌጠችን ዉብን ሀገር ስለሚመራ ይፎክር ነበር። «ታላቁ ጌታችሁ ነኝ!» እያለም ምድር ላይ ጥፋትና ብክለትን ያንሰራፋል።

ነገር ግን ያቺ አማኟ የሙስሊም ሴቶች ምርጥ ሞዴል የነበረችዉ ሚስቱ አሲያ አንዲት የጀነት ቤት እሱ የሚገዛዉን ጨምሮ ዓለም ላይ ካለ ከትኛዉም ሀብት እንደሚበልጥ ዓለምን አስተማረች።

ከሁሉም ግርም የሚለኝ የሳሂሮቹ ጉድ ነዉ። የአላህን ብርሀን ለማጥፋትና በምትኩ ደግሞ ከፊርዖን ዘንድ ምንዳንና ቀረቤታን ፈልገዉ ተደራጅተዉ መጡ። ግን ወዲያዉ አላህ ብርሀኑን ለገሳቸዉና የኢማን ጥፍጥና ወደ ልባቸዉ ዘለቀ። ወዲያዉ እንደአምላክ አጎንብሰዉ ሲያናግሩት የነበረዉን ፊርዖንን አንገታቸዉን ቀና አድርገዉ በሙሳና በሃሩን ጌታ እንደሚያምኑ ነገሩት።

አየሽ! የኢማን በሻሻ ልብን ሲቆጣጠር ዱንያ ላይ ያለዉ የትኛዉም ሀብትና ዝና ተራ እንደሆነ ይገባናል። ዱንያ ላይ ያለ የትኛዉም አካል ዱንያን እንጂ ሌላ ፍርድ እንደሌለዉ እንረዳለን። ከሳሂሮቹ ታሪክን ይሄን ነዉ ምንማረዉ።

ፊርዖን ይመለሱ እንደሆነ ብሎ እጃቸዉን ቆረጠ! ቅጣታቸዉን ሊጨምር እግራቸዉንም ቆረጠ! የተምር ግንድ ላይ ሰቀላቸዉ! «የትኛችን ቅጣቱ አሳማሚና ቀሪ እንደሆነ ትረዳላችሁ!» አላቸዉ። ኢማን ልብ ሲገባ ተዓምር ይሰራልና ፍንክች አላሉም። «ፍረድ! አንተ ምትፈርደዉ ቅርቢቷን ዓለም ብቻ ነዉ!» አሉት።

አጀብ! ጥዋት ኮ ጠንቋዮች ነበሩ! ማታ ግን ሸሂድ ሆነዉ ጌታቸዉን.. የሙሳንና የሃሩንን ጌታ ተገናኙ።

አላሁ አክበር!!

አላህ ነገ ለአማኞች ያዘጋጀዉን ጀነትን በመሻት ዓለም ላይ ያላቸዉን ነገር በሙሉ ሰጡ! ዝናቸዉን፣ ሀብታቸዉን፣ ጊዜያዊ ደስታቸዉን.. ሀታ ነፍሳቸዉን ሳይቀር ሰዉ!! በምትኩም የሰማይና የምድርን ያህል ስፋት ያላትን ጀነትን ወረሱ።

እህቴ! ነፍሴንም አንቺንም በአንድ ነገር ብቻ ነዉ አደራ የምለዉ! ሌላዉ ቢቀር ለዛች ዘላለማዊ ደስታ ስንል ሀራምን እንጠንቀቅ! ዋጂባትን እንፈፅም!

አምስት ወቅትሽን ስገጂ! ወርሽን ፁሚ! የቤተሰብሽን ትዕዛዝ ‛መርሀባ’ በዪ! ነፍስሽን ከሀራም ጠብቂ! ምላስሽን ከወንጀል ቆጥቢ! ወደ መጥፎ ምታዘዋን ነፍስሽን ታገዪ! ሙዚቃን ራቂ! ከወንድ ጋር የሀራም ግንኙነትን አትቅረቢ!

ሁሌም አንድን ነገር ከመስራትሽ በፊት «አላህ ይሄን ነገር ይወደዋል?!» ብለሽ ራስሽን ጠይቂ! ከወደደዉ ተጣደፊበት! ካልወደደዉ ራቂዉ!

ኢንሻ አላህ! እዛኔ የዱንያም የአኼራንም ጀነትን ትወርሺያለሽ!

[[እህቴ! ክስረት ማለት ምን እንደሆነ ታዉቂያለሽ?!

ክስረት ማለት ጀነት የሰማይና የምድርን ያህል ስፋት ኑሯት አንቺ ከዚያ ቦታ ከሌለሽ ነዉ።]]
#ይቀጥላል_ኢንሻአላህ
ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam🌸🍃
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam🌸🍃
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞:::::::እህቴ::::::::☜ ክፍል ሁለት/ ② ፊርዖዎን ያቺን ከስሮቿ ወንዞች የሚፈሱባትን፣ ያቺን በቅንጡ ፎቆች የተጌጠችን ዉብን ሀገር ስለሚመራ ይፎክር ነበር። «ታላቁ ጌታችሁ ነኝ!» እያለም ምድር ላይ ጥፋትና ብክለትን ያንሰራፋል። ነገር ግን ያቺ አማኟ የሙስሊም ሴቶች ምርጥ ሞዴል የነበረችዉ ሚስቱ አሲያ አንዲት የጀነት ቤት እሱ የሚገዛዉን ጨምሮ ዓለም ላይ ካለ ከትኛዉም ሀብት እንደሚበልጥ…
☞::::::እህቴ::::::☜

ክፍል ሶስት/ ③

..ከዕለታት በአንዱ ቀን አንዲት እህትሽ ወደ ተወዳጁ ነብይ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በመምጣት.. «አዉድቅ አለብኝ፣ (አዉድቁ በሚጥለኝ ወቅት ደግሞ) ሰዉነቴ ይገለጣል። ዱዓ አድርጉልኝ!» አለች። ያ የነፍስና የልብ ሀኪም የሆኑት ተወዳጁ ነብይም ሁለት ምርጫ ሰጧት፣ አንድም ዱዓ አድርገዉላት መዳን፣ አልያም ታግሳ ጀነትን ማግኘት። አማኞች ዘንድ ከጀነት በላይ ዉድ ነገር አልነበረምና መታገስን መረጠች።

አየሽ! ሙዕሚን ሰዉ ለጀነት ሲል ሁሉንም ይሰጣል። ሙሲባ የተደራረበባቸዉ ሳይቀር የጀነትን ስም ሲሰሙ ሙሲባቸዉን ይረሱታል። ታግሰዉ አላህ ዘንድ ያለዉን ምንዳን ይከጅላሉ።

የሀሪሳን እናት እንመልከታት እስቲ! ልጇን ሀሪሳን በጣም ትወደዋለች። ሀሪሳ በበድር ወቅት ሸሂድ ሆኖ ይቺን ከንቱ ዓለም ተሰናበት። እሷም ወደ ፍጥረቱ ዐይነታ በመሄድ.. «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ! (መቼስ) ሀሪሳ ልቤ ዉስጥ ያለዉን ቦታ ታዉቃላችሁ። (እስቲ ስለሱ ንገሩኝ!) ጀነት ዉስጥ ከሆነ እታገሳለሁ፣ አላለቅስም። ካልሆነ ግን በሱ ላይ ማልቀስን እጠናከርበታለሁ።» አለችዉ።

ረሱሉም.. «የሀሪሳ እናት ሆይ! ሞኝ ሆንሽ እንዴ?! (በሽታ አገኘሽ?) እሷ ኮ አንዲት ጀነት አይደለችም። እሷ ጀነቶች ናት። እሱ ደግሞ ላይኛዋ ፊርዶስ ዉስጥ ነዉ።» አሏት።

እህቴ! እዚህ ዓለም ላይ ለአንዲት እናት ልጅን ከማጣት በላይ ትልቅ ህመም የለም። ነገር ግን ያ የሷ ልጅ ወደ አላህ ጉርብትና መሄዱን ያወቀች እንደሆነ ህመሟ እንዳልነበረ ይሆናል። ለምን እንደሆነ ታዉቂያለሽ?!

ምክንያቱም እሱ ፀጋ ዉስጥ ነዉ። እሱ ሀሴት ዉስጥ ነዉ። ከንግዲህ ሀዘንም ጭንቀትም አያገኘዉም። ሀዘንና ሀሳብ ምድር ላይ ላሉ ሰዎች ብቻ ነዉ። የጀነት ሰዎች ሁሌም ደስታ፣ ሁሌም ፌሽታ፣ ሁሌም ራሃ ዉስጥ ናቸዉ።

አላህ ያለ ሂሳብና ያለ ቅጣት ጀነትን ከሚወርሱት ያድርገን!!

ሙሲባችን ሚገራዉና ሀዘናችን ሚጠፋዉ አላህ ላይ ያለን የቂን ሙሉ ሲሆን ነዉ። ልባችንን የኢማን በሻሻ ሲወርሰዉ ነዉ።

ኢማን ልብሽ ዉስጥ ሲገባ ጀነት ዘላለማዊ ደስታ እንደሆነችና ለሷ ነፍስሽን፣ ሀብትሽን፣ ሁልሽን መስጠት እንዳለብሽ ይገባሻል።

ኢማን ልብን ሲቆጣጠር የሀራም ስሜት አንቺን አይገዛሽም፣ ነፍስሽ እንደፈለጋት አታዝሽም፣ ነፍስሽ ላይ ንግስት ሁነሽ ሁሉንም እንደልብሽ ታዢያለሽ። የነፍስሽ ፈቃጅም ከልካይም አንቺ ብቻ ትሆኛለሽ! እዛኔ በልብሽ ዐይን ጀነትን ታዪለሽ!

እዛኔ.. አቤት ደስታሽ!!

ነገር ግን.. ለጊዜያዊ ደስታሽ ባሪያ ሁነሽ፣ ሰላትን በጊዜ መስገድን ተሳንፈሽ፣ ሙዚቃን ማዳመጥ አጠናክረሽ.. በአላህ እስቲ በምን ስራሽ ነዉ ጀነትን የተመኘሺዉ?! አላህ አዛኝ ነዉ አዉቃለሁ! ግን ቢያንስ ሰበብ አያስፈልግም?!

አላህ ምስክሬ ነዉ!
የአላህ ፍቅርና የሀራም ፍቅር በአንድ ልብ ዉስጥ አይሰባሰብም.. አንዱ ሌላዉን ገፍትሮ ሚያወጣዉ ቢሆን እንጂ! ወይ ኢማንሽን አድሺና በልብሽ ጀነትሽን ተመልከቺ.. አልያም የሼይጣን መጫወቻ ትሆኚያለሽ!

[[እህቴ! የአላህ ዕቃ ዉድ ነዉ። የአላህ ዕቃ ለዉዶች ነዉ የተዘጋጀዉ። የአላህ እቃ ነፍሳቸዉን ድል አድርገዉ፣ ከሀራም ነፍሳቸዉን ጠብቀዉ፣ ግዴታ የተደረገባቸዉን በአግባቡ ለሚወጡት ነዉ የተዘጋጀዉ።
:
የአላህ ዕቃ ጀነት ነዉ።]]
#ይቀጥላል_ኢንሻአላህ

           ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞::::::እህቴ::::::☜ ክፍል ሶስት/ ③ ..ከዕለታት በአንዱ ቀን አንዲት እህትሽ ወደ ተወዳጁ ነብይ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በመምጣት.. «አዉድቅ አለብኝ፣ (አዉድቁ በሚጥለኝ ወቅት ደግሞ) ሰዉነቴ ይገለጣል። ዱዓ አድርጉልኝ!» አለች። ያ የነፍስና የልብ ሀኪም የሆኑት ተወዳጁ ነብይም ሁለት ምርጫ ሰጧት፣ አንድም ዱዓ አድርገዉላት መዳን፣ አልያም ታግሳ ጀነትን ማግኘት። አማኞች ዘንድ ከጀነት በላይ…
☞::::::እህቴ!::::::::☜

ክፍል አራት/④

ይህ ታሪክ ትዝ ባለኝ ቁጥር ሰዉነቴን ከእግሬ እስከ ፀጉሬ ይነዝረኛል። ገና ሳልፅፈዉ ዐይኔን በእንባ ይሞላዋል። ወላሂ ደስታ ይሁን ሀዘን እንጃ አላዉቀዉም.. ግን ልቤን ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ይወርሰዋል።

ዛሬ የማወራዉ ስለዚያች.. በረሱል ምስክርነት የሷ ተዉባ ለሰባ ሰዎች ቢከፋፈል ይበቃ ነበር ስለተባለላት ሴት ነዉ።

ያ አላህ!! ያ ረሱላችን ምስክር በሰጡት በኢማኗ ታላቅነት ልገረም?! ወይስ ያለ አንዳች ግፊት የሰራችዉን በግልፅ ተናግራ ሀድ እንዲቆምባት ረሱሉን በጠየቀቺዉ እዉነተኝነቷ ልገረም?!

ይህ ወሬ በማሰማመር ምናልፈዉና ዝምብለን እንባ ተራጭተን ምናወራዉ ተራ ወሬ አይደለም። ይህ የአላህን ዒቃብ ለሚፈሩት ይገሰፁ ዘንድ የተፃፈ ታሪክ ነዉና ጥሞና ይፈልጋል። እዚች ሴት ላይ ከየትኛዉ ጊዜ በላይ ሙሉ የሆነን ትኩረትን እፈልጋለሁ።

እቺ ታላቅ ሴት አንድ ቀን ወደ ረሱሉ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በመምጣት.. «አንቱ የአላህ መልዕክተኛ! ዝሙት ሰርቻለሁ አጥሩኝ!» አለች። ረሱሉም መለሷት። በነገታዉም መጣችና «ለምንድን ነዉ ምትመልሱኝ?! ምናልባትም ማዒዝን እንደመለሳችሁት ልትመልሱኝ ፈልጋችሁ ይሆናል። ወላሂ እኔ እርጉዝ ነኝ!» አለች። «(እንደዚያ ከሆነ) ስትወልጂ ተመልሰሽ ነይ!» አሏት። በወለደችም ጊዜ ልጁን ይዛዉ መጣችና «ይሄ እሱ ነዉ! ወልጃለሁ!» አለቻቸዉ። ረሱሉም «ይዘሺዉ ሂጂና (ጡት እስኪጥል) አጥቢዉ!» አሏት። አጥባታዉ በጨረሰች ጊዜ በእጁ ዳቦ አስይዛዉ መጣችና «ይሀዉ የአላህ ነብይ! (ጡት ጥሏል!) እንደምታዩትም ምግብ ጀምሯል።» አለቻቸዉ።

ረሱሉም (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ለአንዱ ሰሀባ ልጁን ሰጡና ጉድጓድ ቆፍረዉ አዘጋጇት። ‛ረጅም’ እንድትደረግ አዘዙ። ኻሊድም መጣና (በትልቅ) ድንጋይ ራሷን ፈነከታት። ደም በደም አደረጋት። ደሟ ኻሊድን ሳይቀር አለበሰዉ። ኻሊድ ሰደባት። ረሱላችንም ኻሊድ መሳደቡን በሰሙ ጊዜ እንዲህ አሉት.. «ኻሊድ ሆይ ተረጋጋ! ያ ነፍሴ በእጁ ባለችዉ ጌታ ይሁንብኝ! እሷ ኮ (ያ ቀረጥ ሚቀበለዉ) ሰዉ ቢቶብት እንኳን አላህ ይቅር የሚለዉን ተዉባ ነዉ የቶበተችዉ።»

በሌላ ዘገባ ሊሰግዱባት ሲዘጋጁ ዑመር ዝሙት ሰርታ ሳለ እንዴት ትሰግድባታለህ?! ሲሏቸዉ እንዲህ አሉት.. «በእርግጥም እቺ ሴት ለ70 የመዲና ሰዎች ተዉባዋ ቢከፋፈል የሚበቃን ተዉባ ነዉ የቶበተችዉ። አንዲትን ነፍሷን ለአላህ ከሰጠች ሴት በላይ ትልቅ ደረጃ ያለዉን ሰዉ አግኝተሃልን?!»

ሱብሀነላህ!
እቺ ሴት ኮ ከአላህ ዉጪ ማንም ባላያት ሁኔታ ላይ ሁና ነዉ ሸይጣን ወስዉሷት ለዝሙት የተዳረገችዉ። ወደ አላህ አልቅሳ፣ ተመልሳ ብትለምነዉና ትክክለኛ ተዉባን ወደሱ ብትመለስ ይበቃት ነበር። ግን የኢማን ለዛ ልብን ሲቆጣጠር እንዲህ ነዉ። በሌሎች ሰዎች ዘንድ ተራ ሚመስለዉ ወንጀል ኢማን ልባቸዉን ለተቆጣጠረ ሰዎች ቀንና ማታ ሀዘንና ቁጭትን ሚያወርስ ነዉ።

አይገርምም! ሲመልሷት እንኳን ተመልሳ ትመጣለች ኮ! እስክትወልድ ብዙ ወራት ነበራት። ከወለደች ብኃላ ጡት እስኪጥል ሁለት አመት ገደማ ያቆያል። ግን በዚህ ሁላ መሃል አንድም ቀን የአላህ ሀድ እንዳይቆምባት ወደኃላ ማለትን አልመረጠችም። በወደቀ ማንነት ጌታዋን መገናኘትን አልፈለገችም።

እቺ ሴት ወደ አላህ ቁርጥን የሆነን መመለስን ለሚሹት ምርጥ ምሳሌ ናት። እርግዝናዋ፣ ዉልደቷ፣ ማጥባቷ አንድኛቸዉም ከተዉባ አላገዷትም። የልጇ ዉብ ዐይኖች እሷ እንደዚያ ስትቀጠቀጥ በእንባ መሞላቱ ከተዉባ አላገዳትም። ልጇን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተሰናብታ በጠራ ልብ አምላኳን ተገናኘች።

በአላህ ዉዴታ ተፅናንታ የዚያን የድንጋዩን ህመም ተቋቋመች። ወንጀሏን እንዲያፀዳላት በመሻት ልብሷኗ መላዉ ሰዉነቷ ደም እስኪለብስ ፀናች።

ይህ ሁላ ለአላህ ዉዴታ የተከፈለ ዋጋ ነዉ።
:
ይህ ሁላ
#ለጀነት የተከፈለ ዋጋ ነዉ።

እህቴ! ልክ እንደዚች እህትሽ ቁርጠኛ ሁኚ! በተራ ነፍስ አላህን መገናኘትን አትሺ! ከሱ ብኋላ መንሸራተት የሌለዉን ትክክለኛ መመለስን መደ አላህ ተመለሺ!!

[[አንዲት ነፍሷን ለጌታዋ ከሰጠች (ነፍስ) በላይ አላህ ዝንድ ትልቅ ደረጃ ያለዉን ሰዉ ታገኛላችሁ?!]]
#ይቀጥላል_ኢንሻአላህ

     ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞::::::እህቴ!::::::::☜ ክፍል አራት/④ ይህ ታሪክ ትዝ ባለኝ ቁጥር ሰዉነቴን ከእግሬ እስከ ፀጉሬ ይነዝረኛል። ገና ሳልፅፈዉ ዐይኔን በእንባ ይሞላዋል። ወላሂ ደስታ ይሁን ሀዘን እንጃ አላዉቀዉም.. ግን ልቤን ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ይወርሰዋል። ዛሬ የማወራዉ ስለዚያች.. በረሱል ምስክርነት የሷ ተዉባ ለሰባ ሰዎች ቢከፋፈል ይበቃ ነበር ስለተባለላት ሴት ነዉ። ያ አላህ!! ያ ረሱላችን ምስክር…
☞::::::እህቴ::::::::☜

ክፍል አምስት/ ⑤

..አንዱን ዓሊም
«እስቲ ስለጀነት ፀጋዎች ንገረንና ጀነትን አስናፍቀን!» አሉት።

እሱም በአንዲት ዐ.ነገር ብቻ ልብን ጀነት ላይ እንድትንጠለል ምታደርግን ንግግር ተናገር። መልካም ስራ መስራት ላደከማቸዉ አሪፍ ብርታት ሚሆንን ንግግር ተናገረ።

«በዉስጧ ረሱሉ አሉ።» አላቸዉ።

አለቀ።
አንድ በልቡ ዉስጥ የረሱሉ ሙሃባ ላለበት ሰዉ በቂ ማነቃቂያ ነዉ።

ምናልባትም «ደክሞኛል፣ ብርታቴ ዝሏል፣ ነፍሲያዬን ቀጥ ማድረግ ከብዶኛል።» ትዪ ይሆናል። የዚህ ታላቅ ዓሊም ንግግር ብርታት ይሆንሻልና ልብሽ ዉስጥ ጥሩ ቦታ አስቀምጪዉ።

እህቴ! ከወንጀል መታቀብ ሲከብድሽም በዚህ ንግግር ዊስዋስን ከላይሽ ላይ ግፈፊ! ዒባዳ መስራት ሲከብድሽም በዚህ ንግግር ተበራቺ!

ጀነት ዉስጥ ረሱሉ አሉ። መርየም፣ አሲያ፣ ኸዲጃ፣ አዒሻ፣ ፋጡማ፣ ማሺጣ.. ሁላቸዉም አሉ። በነሱ ሙሀባ ተጠናከሪ!

ጀነት ዉስጥ ዱንያ ላይ እንደነሱ ለመሆን ምትደክሚላቸዉ መልካም ስብዕናዎች በሙሉ አሉ።

ጀነት ዉስጥ የፀጋዎች ቁንጮ የሆነዉ ታላቁ ኒዕማም አለ። ጀነት ዉስጥ ጀነት ከመግባት በላይ ትልቁ ኒዕማ የዚያን የአላህን ዉብ ፊት ማየት ነዉ። አላህ የሱን ዉብ ፊት ማየትን ይወፍቀን!!

አንቺ የአላህ ባሪያ የሆንሺዉ እህቴ! በአላህና በረሱሉ ፍቅር አአሳስሮ ያስቀመጠሽን የድካም ሰንሰለትን በጣጥሺዉ! አላህ ፅናቱን ይወፍቅሽ!

[[ሲደክምሽ፣ ብርታት ሊሆንሽ ይችላልና ይሄን ፅሁፌን በፈለግሺዉ ሰዓት ልታገኚዉ ምትችዪበት ቦታ አስቀምጪዉ!]]
#ይቀጥላል_ኢንሻአላህ

ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞::::::እህቴ::::::::☜ ክፍል አምስት/ ⑤ ..አንዱን ዓሊም «እስቲ ስለጀነት ፀጋዎች ንገረንና ጀነትን አስናፍቀን!» አሉት። እሱም በአንዲት ዐ.ነገር ብቻ ልብን ጀነት ላይ እንድትንጠለል ምታደርግን ንግግር ተናገር። መልካም ስራ መስራት ላደከማቸዉ አሪፍ ብርታት ሚሆንን ንግግር ተናገረ። «በዉስጧ ረሱሉ አሉ።» አላቸዉ። አለቀ። አንድ በልቡ ዉስጥ የረሱሉ ሙሃባ ላለበት ሰዉ በቂ ማነቃቂያ ነዉ።…
☞:::::::::እህቴ::::::::::☜

ክፍል ስድስት/⑥

ዛሬ ከሌሎች ጊዜ ለየት ያለ ትንሽ ጠጠር ያለ ሀሳብ ነዉ የማነሳዉ። ርዕሳችን ስለጀነት ነዉና ምናልባትም ይህ ዛሬ የማነሳዉ ጉዳይ በኛና በጀነት መሃል መጋረጃ ሊሆን ስለሚችልም ወቅታዊም ጉዳይ ስለሆነ ማንሳቱን መረጥኩኝ።

ሀገራችን ካፈራቻችዉ ታላላቅ ስብዕናዎች መሃል አንዱ የሆኑት.. ታላቁ ሼይክ ሙሀመድ አሊ ኣደም እንዲህ ይላሉ..

«ወሳኙ ነገር ‛አሉ! አሉ!’ መብዛቱ አይደለም። ወሳኙ ነገር ማስረጃዉ ጠንካራ መሆኑ ነዉ።»

አብዘሀኛዉ ሰዉ የሆነን ነገር ያደርጋል ማለት ያ ነገር ልክ ነዉ ማለትን አያስይዝም። በሆነ መንገድ ላይ ሚሄዱ ሰዎች መበራከታቸዉ ያ መንገድ ልክ ነዉ ማለትን አያስንዝም።

እቺን ወሳኝ ነጥብ ከያዝን ወደ ጉዳያችን እንግባ።

እንበልና ያ ከልበወለድ የማያወራዉ ተወዳጁ ነብይ ሙሀመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከዛሬ 1400 አመታት በፊት አንድን ነገር ከለከሉ። ነገር ግን ከዉዱ ነብይሽ ህልፈት ከ7 እና ከ6 መቶ አመታት ብኋላ አንድ ሰዉ መጣና «ያ ነብያችሁ ሲከለክሉት የነበረዉ ነገር ኮ ስህተት ነዉ። እኔ መልካምን ነገር አዉቅላችኋለሁ። እኔን ብትከተሉ መልካም ነዉ።» ቢል ትከተዪዋለሽ?!

አላህ አይቀድረዉና አንቺ ምናልባት መዉሊድን እያከበርሽ ከሆነ ያን ከ1400 አመታት በፊት «ዲናችሁን ሞላሁላችሁ!» ብሎ ቁርዓንን ያወረደዉን አላህን፣ እንዲሁም ያን «ትዕዛዛችን ያልሆነን አንድን ነገር የፈፀመ በሱ ላይ ተመላሽ ነዉ።» ብሎ የተናገረዉን የረሱሉን ቃል ጥሰሽ.. ከረሱሉ ህልፈት ብኋላ ከ700 አመታት ብኋላ መጥቶ መዉሊድን ያወጀዉን ሙዘፈርን አስበልጠሻል ማለት ነዉ።

አላህ ምስክሬ ነዉ!
እኔ ላንቺ አሳቢና ተቆርቋሪ ብቻ ነኝ።

ያ.. እንዴት መብላት፣ እንዴት መጠጣት፣ እንዴት መልበስ፣ እንዴት መተኛት፣ እንዴት መሄድ፣ እንዴት ማዉራት.. በተጨማሪም ብዙ ቀላል ሚመስሉ ነገሮችን ያስተማሩን ነብይ መዉሊድም ኸይር ቢሆን ኖሮ ባስተማሩንና ባመላከቱን ነበር። ግን በአስተምህሮታቸዉ ዉስጥ አንድንም መዉሊድን ሚደግፍ ነገር አናገኝም።

ሰሀቦችም፣ ታቢዕዮችም፣ አትባዓ ታቢዒንም አንድኛቸዉም አልፈፀሙትም። ታዲያ ዲን በነብያትና ከነሱ ቀጥሎ በመጡት መልካም ዓሊሞች ይመራል እንጂ.. በንጉስና በመጥፎ ዓሊሞች ይመራል እንዴ?!

እህቴ! የዚህ ዘመን ሰዎች ምንስተካከለዉ የበፊቶቹ በተስተካከሉት ነዉ። እነሱ የተስተካከሉት ደግሞ በቁርዓንና በሀዲስ ነዉ። በቁርዓንና በሀዲስ ማስረጃዎች አደራ እልሻለሁ!!

[[አደራ!
ብዙ ሰዉ መዉሊድን ማክበሩ አያታልልሽ!
አብዘሀኛዉ ሰዉ ነፍሱ ምታጌጥለትን እንጂ ቁርዓንና ሀዲስን አይከተልምና።]]
#ይቀጥላል_ኢንሻአላህ

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞:::::::::እህቴ::::::::::☜ ክፍል ስድስት/⑥ ዛሬ ከሌሎች ጊዜ ለየት ያለ ትንሽ ጠጠር ያለ ሀሳብ ነዉ የማነሳዉ። ርዕሳችን ስለጀነት ነዉና ምናልባትም ይህ ዛሬ የማነሳዉ ጉዳይ በኛና በጀነት መሃል መጋረጃ ሊሆን ስለሚችልም ወቅታዊም ጉዳይ ስለሆነ ማንሳቱን መረጥኩኝ። ሀገራችን ካፈራቻችዉ ታላላቅ ስብዕናዎች መሃል አንዱ የሆኑት.. ታላቁ ሼይክ ሙሀመድ አሊ ኣደም እንዲህ ይላሉ.. «ወሳኙ ነገር…
☞::::::::::እህቴ! ::::::::::☜

ክፍል ሰባት/⑦

ወሳኝ ጥያቄ!
ዲንን የምትወስጂበት ዋና ቦታ የት ነዉ?!

እስከዛሬ የገባኝ ነገር ቢኖር አብዘሀኛዉ ሰዉ ቀላል የሆነን መንገድ ነዉ ሚከተሉት። ከነፍሳቸዉ ጋር የሚገጥምን ነገር ፈተዋ የሚሰጥን ሰዉ ይወዳሉ። አንዳንዱ እንደዉም ነፍሱ ደስ ያለዉን ነገር ፈተዋ ሚሰጥ ሰዉ ከሰማ በደስታ በሮ.. «ሼይክ ማለትማ ይህ ነዉ፣ ያለንበትን ተጨባጭ የተረዳ ታላቅ ዓሊም ማለት ይህ ነዉ፣ የሙስሊሞችን ቁስል ጠንቅቆ ሚያዉቀዉ እሱ ነዉ።» ይላሉ።

ፈተዋዉ የፈለገዉን ያህል ልክ ባይሆንና በደዒፍ ሀዲሶች ቢሞላ እንኳን የነፍሱን ሙራድ ከገጠመ ፈተዋ ማለት ለሱ ያ ነዉ። ሙፍቲ ማለት ያ ሼይክ ነዉ።

አላህ የቂያማ ቀን እያንዳንዳችንን አንድን ጥያቄ ይጠይቃል..
«..መልዕክተኞችን ምን ብላችሁ መለሳችሁ?!»

አላህ ስለ ሸይክ አገሌ አልያም ስለ ሙፍቲ እገሌ አንጠይቅሽም። ቁርዓንና ሀዲስን ስለመከተልሽ ነዉ የሚጠይቅሽ።

ይበልጥ ግልፅ እንዲሆን ጥያቄዬን ልድገመዉ..

ዲንን የምትወስጂበት ዋና ቦታ የት ነዉ?!

እህቴ! ኮፊያ የለበሰ፣ ጥምጣም የጠመጠመ፣ በአላህ ምስጋና ጀምሮ በ‛ወላሁ አዕለም!’ የዘጋ ሁላ ሙፍቲ ይሆናል እንዴ?!

ዓሊም መስሎ ራሱን ያሳየ ሁሉም ሰዉ ዲን ከሱ ሚያዝ ሰዉ ይሆናል እንዴ?!

እህቴ! ዲንሽን ማንም እንደፈለገዉ የሚቀንሰዉና የሚያበላሸዉ ተራ እቃ አታድርጊዉ! እንደመጣለት የሚፈርድን ተራ ሰዉን እንደሼይክ አድርገሽ አትከተዪዉ! አንቺ ብቻሽን ነዉ ምትመረመሪዉ..

«..መልዕክተኞችን ምን ብላችሁ መለሳችሁ?!» ተብለሽ ብቻሽን ነዉ ምትጠየቂዉ። የጠመሙ ዓሊሞችን እንዳትከተዪ አደራ እልሻለሁ።

እስቲ አንዲት ፈገግ ምታረግን ታሪክ ልንገርሽ!! ላነሳነዉ ርዕስም ምርጥ ምሳሌ ይሆናል።

አንድ ገያስ ኢብኑ ኢብራሂም የሚባል ራሱን ዓሊም ሚያስመስል ዉሸታምና ወራዳ ሰዉ ነበር። ሰዉዬዉ ወሬ ይችላል፣ ሀዲሶችን እንደሀፈዘና ብዙ ዒልም እንዳለዉ ይናገራል። በዚህም ብዙ ሰዎች በዙሪያዉ ይሰባሰባሉ።

አንድ ቀን አንድ ሰዉዬ ገያስን በሚያሳፍር ሁኔታ ላይ ተቀምጦ አየዉና «ከሰዎች አታፍርም?! (ተስተካከል እንጂ!)» አለዉ።

ገያስም «ሰዎች የት አሉ?!» አለዉ። ሰዉዬዉም «እነዚህ በዙሪያህ የተሰበሰቡት ሳ?!» አለዉ። ገያስም «እነዚህማ ሰዎች አይደሉም። እነዚህ ከብቶች ናቸዉ። ከፈለክ ላረጋግጥልህ!» አለዉ።

ከዚያም ገያስ ያለዉን ሊያረጋግጥለት ወደ ሰዎቹ ሄደና ስለጀነትና ፀጋዎቿ ይነግራቸዉ ጀመር። ሁሉም አፉን ከፍቶ ያዳምጣል። ልባቸዉ ወደሱ መንጠልጠላቸዉ ባየ ጊዜ አንድን የዉሸትን ሀዲስ ፈጠረና እንዲህ አላቸዉ.. ረሱል (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል.. በምላሱ የአፍንጫዉን ጫፍ የነካ ሰዉ ጀነት ገባ!

ሰዎቹም ይህን በሰሙ ጊዜ ወዲያዉ ምላሳቸዉን እያወጡ አፍንጫቸዉን ለመንካት መሞከር ጀመሩ።

ገያስም ወደሰዉዬዉ ዞረና «ከብት ናቸዉ አላልኩህም ነበር።» አለዉ።

እህቴ! አላህ የጠበቀዉ ሰዉ ሲቀር አብዘሀኛዉ የኛ ዘመን ሰዉ ቁርዓንና ሀዲስን ሳይሆን እንዲህ አይነት ዓሊሞችን በጭፍን ሚከተሉ «ከብቶች» ሆነዋል።

እህቴ መላልሼ አደራ የምልሽ ነገር..
ዲንሽን ማንም ‛ዓሊም ነኝ!’ ባይ ከመሬት ተነስቶ የሚመራዉ ተራ ነገር አድርገሽ አትያዢዉ።

[[አንድ ሰዉ ዓሊም ሚባለዉ ሁለትን ነገር አንድ ላይ ሲይዝ ነዉ። ዒልምና ተቅዋን።

ዒልም ከቁርዓንና ከትክክለኛ ሀዲሶች ማስረጃ የሚያረግበት መሳሪያዉ ሲሆን.. ተቅዋው ደግሞ በፈተዋዉ ዉስጥ አላህን እንዲፈራ፣ በሀብትና በክብር እንዳይታለልና ሀቅን ለመናገር የወቃሽን ወቀሳ እንዳይፈራ ያደርገዋል።

ትክክለኛ ምርጥ የአላህ ዑለሞች በኛ ዘመን አቤት ማነሳቸዉ።
#ይቀጥላል_ኢንሻአላህ

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞::::::::::እህቴ! ::::::::::☜ ክፍል ሰባት/⑦ ወሳኝ ጥያቄ! ዲንን የምትወስጂበት ዋና ቦታ የት ነዉ?! እስከዛሬ የገባኝ ነገር ቢኖር አብዘሀኛዉ ሰዉ ቀላል የሆነን መንገድ ነዉ ሚከተሉት። ከነፍሳቸዉ ጋር የሚገጥምን ነገር ፈተዋ የሚሰጥን ሰዉ ይወዳሉ። አንዳንዱ እንደዉም ነፍሱ ደስ ያለዉን ነገር ፈተዋ ሚሰጥ ሰዉ ከሰማ በደስታ በሮ.. «ሼይክ ማለትማ ይህ ነዉ፣ ያለንበትን ተጨባጭ የተረዳ…
☞::::::::እህቴ::::::::::☜

ክፍል ስምንት/⑧

የጀነት ሰዎች ነፍሳቸዉ ከፍጥረቱ ዉዴታ ተሳንፋ ወደ ፍጥረቱ ፈጣሪ የተጠናከረች ናት። ጌታቸዉ ከንብረታቸዉ፣ ከቤተሰባቸዉ፣ ከነፍሳቸዉ በላይ እነሱ ዘንድ ተወዳጅ ነዉ።

ምናልባትም በሌሊት ተነስተዉ ለሱ አንሾካሽከዋል፣ ቀንም በሱ ፍራቻ አንብተዋል፣ ዐይናቸዉ እሱ ማየትን ናፍቀዋል፣ ልባቸዉ በሱ ዉዴታ ረፍት አግኝተዋል።

በዱንያ ላይ ልባቸዉ እሱን ማየትን ናፈቀችና አላህም በዚያኛዉ ዓለም የሱን ዉብ ፊትን ማየትን ወፈቃቸዉ።

እህቴ ከነሱ ሁኚ! ልባቸዉ በሀራም ፍቅር ከታወሩ ሰዎች አትሁኚ!

በቂያማ ቀን በአላህ ዉዴታ ላይ ከተገናኙ ሰዎች በቀር ሌሎች አብዘሀኛዉ ሰዎች ፍቅራቸዉ ወደ ከባድ ጥላቻ ይቀየራል። አንዱ አንዱን ይረግማል። «ምናለ እገሌን ጓደኛ ባላረኩ!» እያለች ነፍስ በቁጭት ትዋጣለች። ጓደኛ ስል በሴትና ሴት መሃል ብቻ ሳይሆን በሴትና በወንደ መሃል ሚፈፀመዉን የሀራም ግኑኝነትንም ይይዛል።

እናም ከሀራም ፍቅር እንድትጠነቀቂ አደራ እልሻለሁ!!

ወደ ሀራም ግንኙነት ከሚመሩ ነገሮች መሃል አንዱ ፊልም ነዉ። በየፊልሞች የሴትና የወንድን አንድ ላይ መሆን እየደጋገመ የሚያይ ሰዉ በህይወት ዉስጥም የወንድና ሴት አንድ ላይ መሆን ኖርማል ነገር ይመስለዋል። ከዚያም ህይወቱን ምታደምቅለትን ፍቅረኛ፣ እሷም ህይወቷን ሚያደምቅላትን ፍቅረኛ መፈለግ ይጀምራሉ።

በተለይ ፊልሙ ኢክቲላጥ ከበዛበት.. በዉስጡ ፍቅር መገላለፅ፣ መነካካት፣ መደባበስ፣ መሳሳምና መሰል ነገሮች ካሉበት በነፍስ ዉስጥ ሰክኖ የነበረን ስሜት ይቀሰቅስና መጨረሻዉ ወደ ማያምር ነገር ይወስዳል።

እንደዚሁ የሀራም ፎቶዎችን የሚያይ ሰዉ.. ነፍሱ ያን ነገር መስራት ላይ ማነሳሳቱ አትቀርም። ያ ነገር ወደ ከባድ ሀራም ሊመራዉ ይችላል።

በጣም ሚገርመዉ አላህ ራሱ ሀራምን አትፈፅሙ ሳይሆን አትቅረቡት ነዉ ያለዉ። ሱብሀነላህ!!

ረሱልም «አይን ዝሙት ትፈፅማለች፣ የዐይን ዝሙት እይታ ነዉ።» ብለዋል።

ወደ ሀራም ፍቅር ከሚወስዱ ነገሮች መሃል ሌላኛዉ ዘፈን ነዉ። ኢብን መስዑድ እንዲህ ይላል.. «ዘፈን የዝሙት መንገድ ነዉ።»

ኢብኑ መስዑድ እንደዛ ያሉት እዛኔ ዘፈን በሴት ባሪያዎችና በሚገራርሙ የአረበኛ ግጥሞች ብቻ በሚባልበት ወቅት ላይ ነዉ። የዚህን ዘመን ዘፈንን ቢመለከት ምን ይል ይሆን??!

የዚህ ዘመን ዘፈን ሸህዋን የሚቀሰቅስና ለሀራም መንገድ ዋና በር ነዉ። አላህ ይጠብቀን!!

ከሀራም ፍቅር የሚያርቁ ነገሮች ደግሞ..
ዒልም፣ አላህን መፍራት፣ ሞትን ማስታወስ፣ ነፍስ አኼራን እንድታስታዉስ ማድረግና መሰል ነገሮች ይገኙበታል። በተጨማሪም መልካምና ምርጥ የአላህ ባሮችን መጎዳኘት አንዱ ነዉ።

መልካም ጓደኞች የዱንያም የአኼራም ብርሀኖች ናቸዉ። ጀነት ዉስጥ ቢያጡሽ እንኳን ይፈልጉሻል። «ጌታዬ ጥፍጥናዉ ከሷ ዉጪ አይሞላም።» ይሉታል።

[[አላህና አኼራን በሚያስታዉሱሽ መልካም እህቶች አደራ እልሻለሁ!!]]
#ይቀጥላል_ኢንሻአላህ

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
☞ትዳር_በኢስላም☜

 
#ክፍል_አንድ/①

  
#ኹልዕን_በተመለከተ_በባል_እና_ሚስትመካከል_የሚፈፀሙ_ስህተቶች!!!!!

❗️
#በወንዶች_ላይ_የሚስተዋሉ_ጥፋቶች

    ኹልዕ በሸሪዓችን የተፈቀደ እና ሁሉም ሰው ያለጥላቻና ያለማመንታት ሊቀበለው ግድ ይለዋል።አንዳንድ ወንዶች በዚህ ላይ የተለያዩ ስህተቶችን ሲፈፅሙ ይስተዋላሉ።ከፊሉ ስለዚህ ነገር ምንም እውቀቱ እና ግንዛቤው ስለሌለው ለሚስቱ ሳይመቻት ቀርቶ ሸሪዓው በሚፈቅደው መሰረት ማስለቀቂያ ከፍላ ኹልዕ ስትጠይቅ የታባሽ ብሎ ጨቁኖ ለማኖር የሚፈልግ አለ። ይቺ ሴት ችግር ኑሮባት ፍታኝ ብላ ብትጠይቀው ሸሪዓ እንደሚደግፋት ማወቅ ግድ ይለው ነበር። እያስፈራራ ሳትፈልግ በግዴታ ከኔ ጋር ኑሪ ማለት ከየት የተገኘ ሸሪዓ ነው? ይህን ቢያደርግ አላህ ፊት ተጠያቂ ነው።

     ☞ ሴቷ ወዳው እና አፍቅራው እንጂ ተገዳ እንድትኖር ኢስላም አያዝም።የሚሰራ ጉልበት አለኝ የሚናገር አንደበት አለኝ ብሎ ይቺን የአላህን ሴት ባሪያ ቢበድላት ነገ ሃያሉ ጌታችን ዚህ ትፋረደዋለች። ዛሬ ሰሚ አጥታ ብትጨቆን ነገ የፍትህ ባለቤት ናት።

    ከነብዩ( صلى الله عليه وسلم) ዘመን ጀምሮ ኢስላም ለሴቶች የሰጠው ክብር እና ዋስትና ከዚህ በፊት በነበሩት ሀይማኖቶች ያልተጠቀሰ ሆኖ እናገኘዋለን። ከነዚህ አንዱ ሴት ልጅ የማይመቻትን እና የማትወደውን ባል እርሷ  ከፈለገች ሸሪዓውን ሳትፃረር መፍታት መቻሏ ነው። ለዚህም ማስረጃው የሚከተለው አንቀፅ ነው፣

فَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا يُقِيمَا حُدُودَ اللَّهِ فَلَا جُنَاحَ عَلَيْهِمَا فِيمَا افْتَدَتْ بِهِ ۗ

የአላህንም ሕግጋት አለመጠበቃቸውን ብታውቁ በእርሱ (ነፍሷን) በተበዠችበት ነገር በሁለቱም ላይ ኃጢኣት የለም፡፡ (አል በቀራህ 229)

    ቡኻሪ ላይ በተዘገበው ሀዲስ የሳቢት ኢብኑ ቀይም ሚስት በማለዳ ወደ ነብዩ ሰአወ ዘንድ መጣችና እንዲህ አለች፣ "የአላህ መልክተኛ ሆይ ሳቢት በዲንም ሆነ ፀባዩ ሳካ አላወጣለትም ነገር ግን በራሴ ላይ ክህደትን እፈራለሁ(ስለምጠላው ሀቁን ባለመጠበቄ ዝቅተኛው ኩፍር ላይ ልወድቅ ስለምችል ይፍታኝ) አለች፣ የአላህ መልእክተኛ( صلى الله عليه وسلم)"
የአትክልት ቦታውን ተመልሽለታለች?" አሏት እሷም "አዎ" አለች ፣የአትክልቱንም ቦታ መለሰች።እንዲፈታትም አዘዙት።

     የቁርአን አንቀፁ እና ሀዲሱ እንደሚያስረዳው አንዲት ሴት ከባሏ ጋር እንዳትኖር የሚያግዳት በቂ ምክንያት ካላት በጉልበት አፍኖና ጨቁኖ ማኖር እንደማይቻል አበክሮ ያስተምራል።

    ☞ ❗️
#ወንዶች_አላህንፍሩ!! ኢስላም ለሰው ልጆች ሁሉ በቂ መፍትሄ የሚሰጠውን በእናንተ የግንዛቤ ችግር ሴት ልጅን የበታች አድርጎ እንደሚጨቁን አታስመስሉት።ከኢስላም ውጭ ያለው አካል ኢስላምን አያውቅም ኢስላምን የሚመዝነው በተከታዮቹ ነው። ወንዶች ሆይ፣ ዱኒያም አኼራም የተስተካከለ ይሆን ዘንድ #የነብዩ_(ሰለላሁ_ዓሌይሂ_ወሰለም) ፈለግ እግር በእግር በመከታተል ጥሩ ሞዴል ለመሆን ሞክሩ ።

ለ/
#በሴቶች_ላይ_የሚስተዋሉ ጥፋቶች❗️
   ❗️
#የሴት_ልጅ_ፍቺ_መጠየቅ የተፈቀደ ነው ሲባል ገደብ የሌለው አስመስለው እንደፈለጉ እየተነሱ #ፍታኝ_እሄደዳብላ እያሉ ባሎቻቸውን እና ቤታቸውን የሚያምሱ ሴት እህቶቻችን ቁጥራቸው እየተበራከተ መጥቷል።ከዚህም በባሰ ሁኔታ ኢስላም መፍትሄን አስቀምጦ እያለ በቁርአን መዳኘት ሲገባት አሻፈረኝ ብላ ባሏን በሌላ ህግ ለመዳኘት የማታደርገው ጥረት የለም።ለዚህ ተግባር  አላህ ፊት መልስ የለውም። ባልሽን መፍታት ስትፈልጊ በምን መልኩ መሆን እንዳለበት የአላህ መልክተኛ አሳምረው አስተካክለውልሽ አልፈዋል።ይህን አልፈሽ በሰው ሰራሽ ህግ እዳኛለሁ ብለሽ የምትፈልጊ ከሆነ የአላህ ቅጣት ከባድ መሆኑን ማወቅ ግድ ይልሻል። አላህ በቁርአኑ እንዲህ ብሏል፣👇

ۚ فَلَا تَخْشَوُا النَّاسَ وَاخْشَوْنِ وَلَا تَشْتَرُوا بِآيَاتِي ثَمَنًا قَلِيلًا ۚ وَمَن لَّمْ يَحْكُم بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ فَأُولَـٰئِكَ هُمُ الْكَافِرُونَ
ሰዎችንም አትፍሩ፡፡ ፍሩኝም፡፡ በአንቀጾቼም አነስተኛን ዋጋ አትለውጡ፡፡ አላህም ባወረደው ነገር ያልፈረደ ሰው እነዚያ ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡(ሱረቱ አል-ማኢዳህ - 44)

    የቁርአኑ አንቀፅ እንደሚያስረዳው የአላህ ህግጋት እያለ ወደ ሌላ ሰው ሰራሽ ህግ ለመሄድ አስገዳ ጅ ነገር ሳይኖር በሸሪዓ ከመዳኘት ሰው ሰራሽ ህግ የበለጠ ይጠቅመኛል ብሎ አስበልጦ የሄደ በአላህ የካደ ነው ሲል አስግጧል።

#እህቴ_ሆይ_ኢስላም ያስቀመጠልሽን ፍትህ ትተሽ በሰው ሰራሽ ህግ ለጊዜው የተጠቀምሽ ሊመስልሽ ይችል ይሆናል በኃላ ግን ፀፀት ውስጥ ትወድቂያለሽ ለዱኒያም ሆነ ለአኼራ ትክክለኛ ፍትህ እና ጥቅም ያለው በኢስላም ውስጥ ብቻ ነው።
    አንዳንድ እህቶች በሰላም እየኖሩ በቤተሰብ ወይም በጓደኛ ግፊት ከሜዳ ተነስተው አምባጓሮ ፈጥረው ባላቸውን ፍቺ የሚጠይቁ አሉ።በጣም ይገርማል!! መጀመሪያ እነዚህ ቤተሰቦች በቅናተወ ወይም እሷ የምታመጣውን ሀብት ለመቀራመት በመፈለግ ወይም ባሏን በመጥላት እንዲፈታት ያግባቧታል።ይቺ የዋህ ሴት በሰላም ከምትኖርበት ቤት በክብር ከያዛት ባሏ ለመፈታት ዉሳኔ ላይ ትደርሳለች።ይህን ስትፈፅም ለህይወቷ ባታስብ እንኳን የነብዩ (ሰአወን) ሀዲስ ማክበር ግዴታ ይሆንባት ነበር። ይህን የነብዩን (ሰአወ) ማስጠንቀቂያ ወደ ጎን በመተው የምትጓዝ ከሆነ የሚጠብቃት ቅጣት ከባድ ለመሆኑ  የሚከተለው ሀዲስ ይጠቁማል ።

  ሶውባን ከነብዩ ሰአወ ሰምተው ባስተላለፉት ሀዲስ እንዲህ አሉ፣
#ማንኛዋም ሴት አስቸጋሪ ነገር ሳይገጥማት ባሏን ፍቺ የጠየቀች ከሆነ የጀነት ሽታ በእርሷ ላይ እርም ይሆናል። (አቡ ዳውድ፣ቲርሙዚይና ሌሎችም ዘግበውታል) #ይቀጥላል_ኢንሻአላህ_ቴሌግራማችን_ሼር_ያድርጉ👇👇

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞ትዳር_በኢስላ☜   #ክፍል_ስድስት/⑥ ☞ከአንድ በላይ ሚስት በቀደምት ህዝቦች ዘንድ   #በቀደምት_ቻይናውያን_ዘንድ የቻይና ወንዶች በቀድሞ ዘመን የመጀመሪያ ሚስታቸውን ካገቡ በኃላ በርካታ ልጅ አገረዶችን በመግዛት እንደፈለጉ ይጠቀሙባቸው ነበር። #በኃላየ ተገቡት ወይም የተገዙት ሴቶች ለመጀመሪያዋሚስት ታዛዥ የመሆን ግዴታ አለባቸው ከሌሎች ሚስቶቹ የሚወለዱት ልጆች ለመጀመሪያዋ ሚስት እንደልጅ ታስበው…
☞:::::ትዳር በኢስላም:::::☜

 
#ክፍል_ሰባት_⑦ት

     
#ከአንድ_በላይ_ሚስት_በኢስላም

   ባለፈው እንዳሳለፍነው በጃሂሊያ ዘመን (ኢስላም ከመታደሱ በፊት) በአለም ላይ ያሉ ሀገራት ለሴት ልጅ ያላቸው ክብር እና ግምት በእጅጉ የወረደ በመሆኑ ያለምንም የቁጥር ገደብ ብዙ ሴቶች በአንድ ባል ስር እንዲተዳደሩ ይገደዳሉ።በዚህ ድርጊት ምክንያት በሴቶች ላይ የሚደርስባቸው ግፍና በደል ወንዶችን ምንም የሚያስጨንቃቸው አልነበረም።

    የሰው ልጅ አይነታ የሆኑት
#የአላህ_መልእክተኛ_ሰአወ ኢስላምን ለማደስ ከመጡ በኃላ በጃሂልያ ይተገበር የነበረው ፈር የለቀቀው በሴቶች ላይ ይደረግ የነበረው #ግፍና_መከራ ገፈው ጣሉት።ከአንድ በላይ ሚስትን በተመለከተ እስልምና ቁጥርን ብቻ መገደብ ሳይሆን በሚስቶችም መካከል ፍትሀዊነትም ጭምር ትኩረት ሰጥቶ አስተካክሏል

#በፍትህ_ማስተዳደር_ያልቻለ_አንድ_ትብቃው_እሷንም_ማስተዳደር_ያልቻለ_ማስተዳደር_እስኪችል_ድረስ እንዲፆም_እና_እንዲታገስ በማድረግ ከእንግዲህ ሴት ልጅን እንደፈለጉ ማድረግና መጨቆን እንዳከተመለት ለሴት ልጅ ኢስላም ሙሉ የሆነ ዋስትና እንደሰጣት ታወጀ።አዋጁም ከአፅናፍ እስከ አፅናፍ ተስተጋባ።

    ከዚህም በተጨማሪ ሴት ልጅ ውጭ ወጥታ ከወንድ ጋር እንዳትጋፋ የወንዶች ዘለፋ እንዳያገኛት ሂጃቧን ጠብቃ ቤቷ እንፍትሆን በማድረግ እሷን የመንከባከብ ግዴታውን በወንዶች ላይ አደረገ።እየቻለ ቢያስቸግራት ፀቡ ከማንም ጋር ሳይሆን ከአላህ ጋር እንደሆነ ነብዩ ሰአወ አስጠነቀቁ። በኢስላም ውስጥ
#ሴት_ መሆን_መታደል ነው።እንዲሉ በአጠቃላይ እስላም ለሴቶች ምሽግ ነው።ነገር ግን የኢስላም ጠላቶች ኢስላም ከአንድ በላይ በመፍቀዱ የሴቶችን መብት ይጋፋል። የሚል የእብድ ወሬ ሲያናፍሱ ይደመጣሉ።ኢስላም ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ማስገደድ ሳይሆን በአለፉ እምነቶችና ባህሎች ፈር ለቆ የነበረውን ከአንድ በላይ ሴቶችን ማግበስበስ በገደብ እና በፍትህ እንዲሆን ህግ ማሰረቀመጥ እንደሆነ በዝርዝር አሳልፈናል..

እስከ አራት የተፈቀደ ለመሆኑ ማስረጃ

               
#ቁርአናዊ_ማስረጃ
   አላህ ሱብሀነ ወተአላ እንዲህ ብሏል፣

وَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا تُقْسِطُوا فِي الْيَتَامَىٰ فَانكِحُوا مَا طَابَ لَكُم مِّنَ النِّسَاءِ مَثْنَىٰ وَثُلَاثَ وَرُبَاعَ ۖ فَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا تَعْدِلُوا فَوَاحِدَةً أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُكُمْ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَلَّا تَعُولُوا

በየቲሞችም (ማግባት) አለማስተካከላችሁን ብትፈሩ (ዝሙትንና ከተወሰነላችሁ በላይ ማግባትንም ፍሩ)፡፡ ከሴቶች ለእናንተ የተዋበላችሁን ሁለት ሁለት ሦስት ሦስትም አራት አራትም አግቡ፡፡ አለማስተካከልንም ብትፈሩ አንዲትን ብቻ ወይም እጆቻችሁ ንብረት ያደረጉትን ያዙ፡፡ ይህ ወደ አለመበደል በጣም የቀረበ ነው፡፡ (ሱረቱ አል-ኒሳእ - 3)

    ☞ይህ የቁርአን አንቀፅ፣ በኢስላም ውስጥ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት የሚፈቀድ መሆኑን ግልፅ ማስረጃ ነው።ነገር ግን በሴቶች መካከል በፍትህ ማስተዳደርን ቅድመ መስፈርት አድርጎ ደንግጓል።
#ፍትህ ዋና ቅድመ መስፈርት ለመሆኑ የቁርአን አንቀፁ የወረደበት ሰበብ ማወቅ መልክቱ ግልፅ ያደርገዋል..

    እናታችን አኢሻ ረአ እንዲህ ይላሉ፣ "አንድ ሰው በውስጡ የሚያሳድጋት ብዙ ንብረት ያላት የቲም ሴት ልጅ ነበረችው፣ ንብረቷን ፈልጎ ጥሎሹን በትክክል ሳይሰጣት አገባት።ከዚያ ይቺ የቁርአን አንቀፅ ወረደች.።

   ☞  በሌላ ዘገባ ዑርወት ኢብኑ ዙበይር ወደ እናታችን አኢሻ ዘንድ መጣና ስለ
"وَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا تُقْسِطُوا فِي الْيَتَامَىٰ"
ጠየቃቸው እሳቸውም እንዲህ ብለውታል፣ "የወንድሜ ልጅ ሆይ;አንድ ወንድ ሃላፊ ሆኖ የሚያሳድጋት የቲም ሴት ልጅ ገንዘቧ እንዲሁም መልኳ አስቀንቶት መህሯን በትክክል ሳይሰጣት እንዳያገባት ማለት ነው፣ ይህ ነው የተከለከለው። እሷን ማግባት የሚፈልግ ከሆነ መህሯን ለሌሎቹ እንደሚሰጠው አድርጎ በፍትህ መህሯን ለሌሎች ሚስቶች የሚገባውን ሰጥቶ ያግባት።ነገር ግን ፍትህ ማጓደልን ከፈራ እሷን ትቶ ሌሎችን የሚያስደስቱትን እስከ አራት ማግባት ይችላል ማለት ነው።" ቡኻሪ ዘግበውታል።.

#ይቀጥላል_ኢንሻአላህ_ሼር_ያድርጉ👇👇👇

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☞:::::ትዳር በኢስላም:::::☜   #ክፍል_ሰባት_⑦ት       #ከአንድ_በላይ_ሚስት_በኢስላም    ባለፈው እንዳሳለፍነው በጃሂሊያ ዘመን (ኢስላም ከመታደሱ በፊት) በአለም ላይ ያሉ ሀገራት ለሴት ልጅ ያላቸው ክብር እና ግምት በእጅጉ የወረደ በመሆኑ ያለምንም የቁጥር ገደብ ብዙ ሴቶች በአንድ ባል ስር እንዲተዳደሩ ይገደዳሉ።በዚህ ድርጊት ምክንያት በሴቶች ላይ የሚደርስባቸው ግፍና በደል ወንዶችን…
☞::::::ትዳር በኢስላም:::::☜

  .
#ክፍል_ስምንት/⑧ት
     
#ከአንድ በላይ ሚስት በኢስላም

#እስከ_አራት_የተፈቀደ_ለመሆኑ_ማስረጃ

               
#ቁርአናዊ_ማስረጃ
   አላህ ሱብሀነ ወተአላ እንዲህ ብሏል፣

وَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا تُقْسِطُوا فِي الْيَتَامَىٰ فَانكِحُوا مَا طَابَ لَكُم مِّنَ النِّسَاءِ مَثْنَىٰ وَثُلَاثَ وَرُبَاعَ ۖ فَإِنْ خِفْتُمْ أَلَّا تَعْدِلُوا فَوَاحِدَةً أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُكُمْ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَلَّا تَعُولُوا

በየቲሞችም (ማግባት) አለማስተካከላችሁን ብትፈሩ (ዝሙትንና ከተወሰነላችሁ በላይ ማግባትንም ፍሩ)፡፡ ከሴቶች ለእናንተ የተዋበላችሁን ሁለት ሁለት ሦስት ሦስትም አራት አራትም አግቡ፡፡ አለማስተካከልንም ብትፈሩ አንዲትን ብቻ ወይም እጆቻችሁ ንብረት ያደረጉትን ያዙ፡፡ ይህ ወደ አለመበደል በጣም የቀረበ ነው፡፡ (ሱረቱ አል-ኒሳእ - 3)

#ከአንቀፁ_የምንማራቸው_ቁም_ነገሮች

_አንቀፁ አንድ ወንድ ማግባት የሚችለው ከፍተኛው ቁጥር አራት መሆን እንዳለበት ይደነግጋል።ከአራት ሚስት በላይ ከነብዩ ሰአወ  ውጭ ማንኛውም ሰው መጨመር እንደማይፈቀድለት ኢማም አሻፊኢይ ኢጅማእ (የሙስሊም ሊቃውንት የጋራ አቋም)) አለው ይላሉ።ነብዩ ሰአወ ለምን ከአራት በላይ እንደተፈቀደላቸው እና ከአንድ በላይ የማግባታቸው ጥበብ ሌላው ተራው ሰው ከአንድ በላይ ከሚያገባበት ምክንያት የተለየ ነው።ይህን በተመለከተ እራሱን የቻለ ምዕራፍ ስላለው ከማውጫው ላይ በመፈለግ በዝርዝር ማንበብ ጠቃሚ ነው።

_አንቀፁ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት የፈለገ ሰው
#ፍትሃዊነት ቅድመ መስፈርት መሆን እንዳለበት ያስተምራል።በፍትህ ማስተዳደር የማይችል ወይም ፍትሃዊነት ሊጎለኝ ይችላል
ብሎ የሚያስብ ወንድ ከሆነ ከአንድ በላይ ማግባት እንደማይፈቀድለት አንቀፁ ከሚሰጠን ግንዛቤ የተወሰኑት ናቸው።

    ☞ ፍትሃዊነት ሲባል አንድ ሰው ማድረግ በሚችለው
#እንደቀለብ_ልብስ_መኖሪያቤት_እና_አብሮማደርን የሚያካትት ነው።ነገር ግን ከእርሱ ቁጥጥር ውጭ ሆኖ በማይችለው እና ከአቅሙ በላይ በሆነው እንደ #ፍቅር_መስጠት ያሉ ነገሮች ሁሉንም ሚስቶቹን እኩል ላድርግ ቢል ማድረግ አይችልም።ምክንያቱም አላህ በልቡ ላይ #ትወደድ_ያላት_ሴት_እሱ_ዘንድ_የበለጠ_ትወደዳለች።ለዚህ ሲባል አላህ እንዲህ ይላል፣

وَلَن تَسْتَطِيعُوا أَن تَعْدِلُوا بَيْنَ النِّسَاءِ وَلَوْ حَرَصْتُمْ ۖ فَلَا تَمِيلُوا كُلَّ الْمَيْلِ فَتَذَرُوهَا كَالْمُعَلَّقَةِ ۚ وَإِن تُصْلِحُوا وَتَتَّقُوا فَإِنَّ اللَّهَ كَانَ غَفُورًا رَّحِيمًا
በሴቶችም መካከል ምንም እንኳ ብትጓጉ (በፍቅር) ለማስተካከል አትችሉም፡፡ እንደ ተንጠለጠለችም አድርጋችሁ ትተዋት ዘንድ (ወደምትወዷት) መዘንበልን ሁሉ አትዘንበሉ፡፡ ብታበጁም ብትጠነቀቁም አላህ መሓሪ አዛኝ ነው፡፡[ ሱረቱ አል-ኒሳእ - 129 ]

☞ ከቁርአን አንቀፁ የምንማረው ቁምነገር፣ አንድ ሰው በሚስቶቹ መካከል በልብ ላይ ባለው ነገር(ፍቅር) ማስተካከል የማይችል መሆኑን ነው። ነገር ግን የሰው ልጅ የሚችለውን ማስተካከል ጠብቆ መያዝ እንዳለበት ካለፈው የቁርአን አንቀፅ ለማየት ሞክረናል። እንደውም በሚስቶች መካከል ፍትሃዊ መሆን የመጀመሪያ መስፈርት ከሚባሉት ውስጥ ነው።

#ማሳሰቢያ፣ አንዳንድ አዕምሯቸው እንዳያገናዝብ የተዘጋባቸው ሰዎች ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት አይቻልም ብለው የሚከራከሩ በኢስላምም ውስጥ ብቅ ብለዋል።ማስረጃ ብለው ያቀረቡት ከላይ ያሳለፍነውን የቁርአን አንቀፅ ነበር።እንደነሱ አባባል የቁርአኑ አንቀፅ "በሴቶች መካከል ምንም እንኳን ብትጓጉ ለማስተካከል አትችሉም" ብለው በመተርጎም * በሴቶች መካከል ማስተካከል ደግሞ ቅድመ መስፈርት ስለሆነ ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት አይቻልም* የሚል ድምዳሜ ላይ ደረሱ። #ትርጉሙን_ለስሜታቸው_እንዲመቻቸው_አድርገው_በመተርጎም_እነሱ_ይህን_ይበሉ_እንጂ_ትክክለኛ_የአንቀፆቹ_መልእክት_እንዳሳለፍነው_ነው

    📚 የመጀመሪያው የቁርአን አንቀፅ የሚለው በየቲሞች መካከል ፍትህን እናጓድላለን ብላችሁ ከፈራችሁ ሌሎች ሴቶችን እስከ አራት ማግባት ትችላላችሁ የሚል ሲሆን የሁለተኛው የቁርአን አንቀፅ የሚያስረዳው ደግሞ በሴቶች መካከል ፍቅርን እኩል ማካፈል አትችሉም።ነገር ግን በምትችሉት ነገር ሴቶቻችሁን ችላ ብላችሁ እንዳትተዋቸው የሚል መልክ አዝሏል።
#ትክክለኛውም_የቁርአኑ_መልእክት_ይህ_ነው
  ☞ በሚችለው ነገር በሚስቶቹ መካከል ፍትሃዊ ያልሆነ ወንድ አላህ ዘንድ ትልቅ ቅጣት እንደሚጠብቀው ነብዩ ሰአወ ተናግረዋል።

    ☞አቡ ሁረይራ ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ ሰአወ እንዲህ አሉ፣ "ሁለት ሚስቶች እሱ ዘንድ ያሉት እና በመካከላቸው ፍትሃዊ ያልሆነ ወንድ የቂያማ ቀን አንድ ጎኑ የተዘነበለ ሆኖ ይመጣል"  (ቲርሚዝይ ዘግበውታል

      ❗️ሙስሊም ሲባል ከዚህም ባለፈ በሁሉም ነገር ላይ በሚችለው አቅሙ በፈቀደው ፍትሃዊ መሆን መለያ ባህሪይው ሲሆን በተለይ ደግሞ በውስጡ ባሉት የኑሮ አጋር ከሆኑት ሚስቶቹ ጋር ሲሆን በእጅጉ ትኩረት የሚሰጠው ነው.።

  
#ይቀጥላል

            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
☀️እህቴ ሆይ እስቲ አንዴ ከሂወትሽ ትንሽን ደቂቃ ቀንሰሽ እህህ ብለሽ ስሚኝ ምናልባት ይጠቅምሽ ይሆናል... قال الرسول ﷺ: "الحياء شعبة من الإيمان" 💫 ነቢዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ :- "ሀያዕ ( ማፈር ) ከኢማን ቅርንጫፎች ውስጥ ነው " 💫 ውዷ እህቴ ሀያዕ ማድረግ ለሴት ልጅ  ክብር ነው እንደውም ውበቷም ጭምር ነው ። 💫 አንዳንድ እህቶች አሉ አለባበሳቸው፣…
#የቀጠለ
☀️በርካታ እህቶች ሒጃብ ከማድረጋቸው ጋር አንዳንድ ሒጃብ ካደረገች ሴት የማይጠበቁ ነገሮችን ሲያደርጉም ይስተዋላል ለምሳሌ፥መንገድ ላይ ሲሄዱና ታክሲ ውስጥ ሆነው ጮክ ብሎ ማውራት፣ መሳቅና መቀለድ፣ ያለ በቂ ምክንያት መንገድ ዳር ላይ በሚያጠራጥር መልኩ ከወንድ ጋር መቆም (ዘመድ/መሕረም እንኳ ቢሆን ይህ ተገቢ አይደለም)፣ ጅልባብ ላይ፤ ሻሽ (ሒጃብ) መጠቅለል፣ጃኬት መደረብ፣ ሲራመዱ ጅልባብን ወደ ላይ ሰብስቦ በመያዝ እግር/ባት እንዲታይ ማድረግ፣ ዘመዴ ነው የአጎት የአክስት ልጅ ነው ወዘተ እያሉ ለሱ ፊትን መግለጥና ተጠጋግቶ መቀመጥ፣ ካፌና ምግብ ቤት መመላለስ ማብዛትና እዛ ውስጥም አደብ የጣሰ አካሄድን መሄድ ወዘተ አንዳንድ እህቶች ጋ የሚታዩ ስህተቶች ናቸውና

እህቴ ሆይ፥ የሒጃብን አላማ እወቂ ዲንና ክብርሽንም ጠብቂ! ሒጃብ አድርገሽ የኢስላምን አደብ ባለመጠበቅሽ ምክንያት ኢስላምን አታሰድቢ
#ይቀጥላል...
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም
#የቀጠለ ☀️በርካታ እህቶች ሒጃብ ከማድረጋቸው ጋር አንዳንድ ሒጃብ ካደረገች ሴት የማይጠበቁ ነገሮችን ሲያደርጉም ይስተዋላል ለምሳሌ፥መንገድ ላይ ሲሄዱና ታክሲ ውስጥ ሆነው ጮክ ብሎ ማውራት፣ መሳቅና መቀለድ፣ ያለ በቂ ምክንያት መንገድ ዳር ላይ በሚያጠራጥር መልኩ ከወንድ ጋር መቆም (ዘመድ/መሕረም እንኳ ቢሆን ይህ ተገቢ አይደለም)፣ ጅልባብ ላይ፤ ሻሽ (ሒጃብ) መጠቅለል፣ጃኬት መደረብ፣ ሲራመዱ ጅልባብን…
☀️ታክሲ/ትራንስፖርት ላይ በተወሰነ መልኩ ከወንድ ጋር መገናኘት (መቀራረብ) ሁኔታዎች የሚያስገድዱት ነገር ሊሆን ይችላል ይሁንና በተቻለሽ ያክል ከወንድ አጠገብ ላለመቀመጥ እንዲሁም ስትገቢ ከወንድ ጋር ላለመላፋት ሞክሪ።ነገር ግን! በምንም ሁኔታ ላይ ታክሲ እየጠበቅሽም ይሁን እየተጓዛሽ በሁለት ባዕድ ወንዶች መሃል አትሁኚ! (አትቁሚ/አትቀመጪ)! እጅግ በጣም የሚያሳዝነው አልፎ አልፎ ሙስሊም ሴት ከባጃጅ ሾፌር ጋር ጋቢና ቁጭ ብላ ሰውነቷን ከሰውነቱ ጋር አጣብቃ ስትሄድ ይታያል!!
فالله المستعان!
"እህት ሆይ፥ አላህን ፍሪ! ከእንዲህ ዓይነቱ ድርጊት ዲንና ኢማን ባያግድሽ ዓቅል/ህሊናሽ ሊከለክልሽ ይገባል!
💥((ሐያዕ የሌለው ኢማን የለውም))
#ይቀጥላል
            ቴሌግራማችን

╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝
@Tidar_Be_Islam