ስንክሳር ወግጻዌ ዘተዋሕዶ
836 subscribers
3.46K photos
103 videos
194 files
1.2K links
የየዕለቱ ስንክሳር እና ግጻዌ የሚቀርብበት ቻናል ነው፡፡

ለማንኛውም አስተያየት እና እርማት
@zetaodokos ላይ ይላኩልን።

👇👇የYoutube Channel ይቀላቀሉ👇👇
https://youtube.com/channel/UCupqpIYe_mMpSM7jMT3Njhw
Download Telegram
#ኦርቶዶክስ_መልስ_አላት
#ክፍል_5
#በጥምቀት_ላይ_ያለ_ልዩነት
#የጥምቀት_ጥቅሙ_ምንድነው ?
በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት በጥምቀት ድህነትን ፣ መንጻትን ፣ ፍትህን ፣ አዲስ ሕይወትንና በክርስቶስ ክርስቲያን መሆንን ያስገኛልን ? ወይስ እንደ ፕሮቴስታንት እምነት እነዚህ ሁሉ በማመን ብቻ ይገኛሉ ? በማመን ብቻስ ከሆነ ለምን መጠመቅ ያስፈልጋል ? #ማጥመቅ_የሚችለው_ማነው ?
በኦርቶዶክስ ማጥመቅ የካህናት ተግባር ነው ። ነገር ግን በፕሮቴስታንቶች ዘንድ በ ክህነት ጨርሶ አይታመንም ። ስለዚህ በቤተክርስቲያናቸውም ጥምቀት በተራ ሰው እንጂ በካህናት ፈፅሞ አይደረግም ። አጥማቂው ሴትም ወንድም ሊሆን ይችላል ። እኛ ግን #ጥምቀትን ከሚስጥራተ ቤተክርስቲያን አንዱ ነው ብለን እናምናለን። ፕሮቴስታንቶች ግን ይህንን አያምኑም ። እኛ ውሃ ውስጥ እናጠምቃለን እነርሱ ግን በመርጨት ያጠምቃሉ ።እኛ ህፃናትን ስለቤተሰቦቻቸው እምነት እናጠምቃለን ፡ ፕሮቴስታንቶች ግን ሕፃናትን በማጥመቅ አያምኑም ። ምክንያት ሲሰጡም "ከጥምቀት ማመን መቅደም አለበት "ይላሉ። #የጥምቀት_ጥቅሞች
መዳን በጥምቀት የተሟላ ይሆናል ። ጌታችን "ያመነ የተጠመቀም ይድናል " ብሎ አስተምሮናል ። /ማር 16:16/ ጌታችን ያመነ ይድናል አላለም ነገር ግን ከማመን ጎን ለጎን የመጠመቅንም ነገር አስቀመጠ እንጂ ። #በጥምቀት ከውሃና ከመንፈስ የሆነውን ሁለተኛውን ልደት እናገኛለን ። #ጥምቀት ኃጢያትን ያስወግዳል ። "አሁንስ ለምን ትዘገያለህ ተነሳና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኀጢአትም ታጠብ ። " አለው ። (ሐዋ 22-16) ከዚህ እንደምናየው የመጠመቅ አንዱ ውጤት ከኀጢአት መታጠብ ነው ። #ጥምቀት ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብሮ መሞትና አብሮ መነሳት ነው ።መፅሐፍ "ወይስ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደተጠመቅን አታውቁምን ? (ሮሜ 6:3) አለ። በቆላስያስ መልእክቱ "በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀብራቹ በጥምቀት ደግሞ ከሙታን ባስነሳው በእግዚአብሔር አሰራር በማመናችሁ ከእርሱ ጋር ተነሳችሁ ። /ቆላ.2:12/
ሌላው የጥምቀት ጥቅም #በጥምቀት ክርስቶስን ለብሰነዋል/መስለነዋል ። ጳውሎስ "ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኀልና " /ገላ3:27/ የጥምቀትን ታላቅ ጥቅም ሊገልፅ የሚችል ከዚህ የተሻለ ቃል አለን ? በጥምቀት በደሙ የሆነውን ክርስቶስን ለበስነው ፤ ጽድቁንም በጥምቀቱ የተሰጠንን ድኀነትንም እንዲሁ ለበስነው ። "ሰውን በመልካችን እንደምሳሌያችን እንፍጠር " /ዘፍ 1:26/ ብሎ በቀደመ በደላችን ያጣነውን እግዚአብሔርን መምሰልን ተላበስን ። በቀጣይ ደሞ ለምን#በ40እናበ80ቀን እንጠመቃለን የሚለውን እናያለን ።
ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ኦርቶዶክሳዊ_የጾታ_ትምህርት
#ክፍል_5
#የፍቅር_አይነቶች (types of love)
እንደሚታወቀው ባለፉት ክፍሎቻችን 12 አይነት የፍቅር አይነቶች አሉ ብለን ከ12ቱ አይነት 6ቱን ማየታችን ይታወቃል ። እነሆ ቀጣይ ከፍልን ዛሬ እናያለን ።
#7ኛ_አንሰልፊሽ_ላቭ (unselfish love) ፦ ይህ ፍቅር የሚጀምረው ራስ ወዳድ ካለመሆን የሚመነጭ የፍቅር ዓይነት ነው ። ለምሳሌ በዚህ ፍቅር ውስጥ የሚገባ ሰው ለቀረበለት የፍቅር ጥያቄ የእሺታ መልስ ሊሰጥ ይችላል። የሚሰጠው ግን "እሷ ከምትጎዳ እኔ ልጎዳ " በሚል ዓይነት ስሜት ነው ። ነገር ግን ያንን ፍቅር ውስጡ ላያምንበት ይችላል ። የሰውን ጉዳት ስለማይፈልግ ብቻ ግን ፈቃደኛ ይሆናል ። እንደዚህ አይነት ሰዎች ብዙ ጊዜ በባህርያቸው ገራም ፣ ለስለስ ያሉ ፣ ቅንና ቁምነገረኝነት ያለባቸው ፣ ለጀመሩት የፍቅር ሕይወት ይህ ይገጥመኛል ብለው ሳይፈሩ ራሳቸውን መስዋዕት የማድረግ ባህርይ እንዳለባቸው ይታመናል ።
#8ኛ_ጌም_ፕሌይንግ_ላቭ (Game Playing Love) ፦ ይሄኛው የፍቅር ዓይነት ደግሞ ነውሩ በጣም ደምቆ የሚታይ የፍቅር ዓይነት ነው ። ይህ አፍቃሪ ራሱን ማርካት ብቻ የሚፈልግ አፍቃሪ ነው ።ለሰው ሕይወት ግድ አይሰጠውም ። ለጊዜው ጠንካራ አፍቃሪ መስለው ሊታዩ ይችላሉ ። #አፈቀርኩ ካሉት ሰው ጋር ሁልጊዜ መጫወት ነው የሚፈልጉት ። ለትዳር መሰረት የሚሆነው ነገር አይታያቸውም ። ዓላማቸው አንድ ነገር ብቻ ነው ። እሱም የሩካቤ ሥጋ ጥማቸውን ማርካት ብቻ ! ከዚያ በሗላ ደግሞ ሌላ ሰው ይቀይራሉ ። አሁንም ደግሞ ይቀይራሉ ። እንዲህ እንዲህ እያሉ ልቅ በሆነ ዝሙት መስከር በጣም ነው የሚያስደስታቸው ። እንዲህ አይነት ሰው ባህሪው እስካልተቀየረ ድረስ ለትዳር ፍፁም ምቹ አይደለም ። ይህ ባህሪ ብዙውን ጊዜ በወንዶች ላይ እንደሚንጸባረቅ ይታመናል። እነዚህ ሰዎች በሕይወታቸው ሰፊውን ቦታ የሚይዘው #ስሜት ነው ።
#9ኛ_ኢምፒቲ_ላቭ (Empty Love ) ፦ "ባዶ ፍቅር" ከምንም ነገር ተነስተው ባዶ ፍቅር የሚይዛቸው ሰዎች አሉ ። ለጊዜው "ፍቅር ያዘኝ " ይበሉ እንጂ ፍቅራቸው ግን ምንም ጣዕምና ትርጉም የሌለው ነው ። ለምን እንዳፈቀሩ ቢጠየቁ እንኳን በቂ መልስ የላቸውም ። ፍቅር ፍቅር የሚሆነው ደግሞ ሰጥቶ መቀበል ሲኖርበት ነው ። በእነዚህ ሰዎች መካከል ግን ፍቅርን መስጠትና መቀበል የሚባለው ነገር እንኳን በቅጡ አይታወቅም ። ፍቅርን ሰጠን ቢሉ እንኳን በቂ መልስ ግን የለውም ። ብቻ ባጋጣሚ ስለተገናኙ ተቀራርበው ሊሆን ይችላል። ግን ቅርበታቸው ትርጉምና ደስታ የማይሰጥ ዓይነት ባዶ ቅርበት ሲሆን ቁርጠኝነትም ስሜትም በውስጡ የሌለው የፍቅር ዓይነት ነው። በቀጣይ ደሞ የቀሩትን እናያለን ። ሃሳብ አስተያየት ኢዮአታም ላይ ልትነግሩኝ ትችላላቹ ።

🌼share it

ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ክርስቲያናዊ_ስነ_ምግባር
#ክፍል_5

#3የሰንበትን_ቀን_ትቀድሰው_ዘንድ_አስብ
🖊 የቃሉ ትርጉም አቆመ አረፈ ማለት ነው ። ይህ ማለት የሰው ልጅ ከጌታ ጋር የሚቀራረብበት መገናኛ መንገድ ነው ። ከማንኛውም ስጋዊ ተግባር የምናርፍበት ፣ ትርጓሜው የእግዚአብሔርን ሥራ እንድናስታውስ የሚያደርግበት ቀን ነው ።
🖊 #ሰንበት የመንግስተ ሰማይ ምሳሌ ነች። የሰው ልጅ በዓለም ሠርቶ ወርዶ በመልካም ሥራው የሚያርፍበት ቦታ ናት ።
🖊ሰው ዕረፍት ያስፈልገዋል የሰንበት ቀን የተፈጠረውም ለዚህ ነው ። የሰንበት ቀን የዕረፍት ቀን ስለሆነ የሚከተሉትን ሁለት ነገሮች ያሳስበናል ።
#፩ኛ ሰው በኀጢአት ከመውደቁ በፊት ከአምላኩ ጋር ያለውን ግንኙነት የነበረውን ዕረፍት
#፪ኛ ከጌታችን ከመድኀኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት የተገኘውን ዘላለማዊ የነፍስ እረፍት ።
🖊በሐዲስ ኪዳን ሰንበት ሁለት ናቸው #ቅዳሜና_እሁድ#ቅዳሜ ማለት የበፊቷ የቀደመችው ማለት ነው ። #እሑድ ማለት ደግሞ መጀመሪያ 🖊ስለሆነ ከዚህ ጀምረን ስንቆጥር ቅዳሜ ሰባተኛ ቀን ይሆናል ። በ፫ኛው ትዕዛዝ እንዲከበር የታዘዘው ይህ ቀን ነው ። ፈሪሳውያን በሰንበት ቀን እግር ከዘረጉ አያጥፉም ፣ ከአጠፉም አይዘረጉም መልካምም ሥራ ቢሆን አይሰሩም ።
#እሑድ ሥነፍጥረት የጀመረበት ፣ ኀላም ጌታ የተነሳበት፣ መንፈስቅዱስ የወረደበት እንዲሁም ጌታ የሚመጣበት ዕለት ነው ። ስለዚህ እናከብረዋለን ። በቤተክርስቲያን ታሪክ ደግሞ ቆስጠንጢኖስ ዕለተ እሑድ የክርስቲያኖች ቀን ስለሆነች ሥራ እንዳይሰራ በ፫፻፳፩ ዓ-ም በሕገመንግስቱ አፅድቆ እንዳወጀና እንደወሰነ ይነገራል ። ስለዚህ ሰንበት የእረፍት ቀን ነው ስለተባለ ሥራ ፈተን መዋል የለብንም ። በእግዚአብሔር ቤት በመገኘት ማስቀደስ ፣ ቃሉን መማር ፣ መዘመርና ማመስገን አለብን ። ከዚህም ሌላ ጌታ በሰንበት መልካም ሥራ ማድረግ ተፈቅዷል ስላለ የታመመና የታሰረ መጠየቅ ፣ የተጣላ ማስታረቅ ፣ ያዘነ ማፅናናት ፣ ለተቸገረ ደግሞ ምፅዋት መመፅወት አለብን ። እንግዲህ በክርስትና ሰንበት የሚከበረው እንዲህ ነው ።
🇪🇹ሠንበትን ለምን እናከብራለን
፩ ፦ከቀናት ሁሉ ተለይታ ለበረከት ለቅድስና ለማመስገን ትሆን የተፈጠረች ነች
፪ ፦ሰውን ስለ ወደደ ለዕረፍት የሠራት ቀን ናት
፫ ፦በእግዚአብሔር ና በህዝብ መካከል ምልክት ናት
፬ ፦የሚያምን ከማያምን መለየት ኩፋ ፫÷፭-፱
፭ ፦እግዚአብሔር አምላክ ለህዝቡ የሠጠው የመጀመሪያው ህግ ናት ዘፍ፲፮÷፳፫


ይቀጥላል...

Share👇share👇share
👉ለመቀላቀል 👇👇👇
@zekidanemeheret @zekidanemeheret @zekidanemeheret
"የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ"
ዝማሬ ዳዊት On Telegram
👉 የአርብ ውዳሴ ማርያም አንድምታ
🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!