ስንክሳር ወግጻዌ ዘተዋሕዶ
870 subscribers
3.46K photos
103 videos
194 files
1.2K links
የየዕለቱ ስንክሳር እና ግጻዌ የሚቀርብበት ቻናል ነው፡፡

ለማንኛውም አስተያየት እና እርማት
@zetaodokos ላይ ይላኩልን።

👇👇የYoutube Channel ይቀላቀሉ👇👇
https://youtube.com/channel/UCupqpIYe_mMpSM7jMT3Njhw
Download Telegram
ከትንሣኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡-

#ሰኞ
#ማዕዶት_ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡

#ማክሰኞ
#ቶማስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29

#ረቡዕ
#አልአዛር_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡

#ሐሙስ
#አዳም_ሐሙስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡

#አርብ
#ቅድስት+ቤተክርስቲያን_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡

#ቅዳሜ
ቅዱሳት_አንስት_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡

#እሁድ
#ዳግም_ትንሣኤ _ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡

👉🏻@zekidanemeheret
👉🏻@zekidanemeheret
👉🏻@zekidanemeheret
#ዳግም_ትንሣኤ

ዳግም ትንሣኤ ሲባል መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ሞቶ፣ ተቀብሮ፣ ተነሳ ሳይሆን በድጋሜ ቅዱስ ቶማስ ባለበት ልክ በመጀመሪያ እንደተገለጠላቸው ሆኖ ስለታያቸው ነው።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአስሩ ሐዋርያት ሲገለጥላቸው ሐዋርያው ቶማስ አልነበረምና መጥቶ በተገናኛቸው ጊዜ እነሱም ጌታችን እንደተነሳና ተገልጦ ሰላምታ እንደሰጣቸው ሲነግሩት የተቸነከረውን እጁን እና እግሩን በጦር የተወጋ ጎኑን ካላየሁ አላምንም በማለቱ (ዮሐ 20፥25) እንደገና ተገልጦላቸዋል።

ቶማስ ይሄንን ሊል የቻለው የተጠራው ትንሣኤ ሙታን የለም ከሚሉት ከማያምኑት ከሰዱቃውያን ወገን ነበርና ነው። አንድም ሌሎች ሐዋርያት ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ አየነው እያሉ ሲያስተምሩ እኔ ግን ሰማሁ ብዬ ላስተምር ነው ብሎ ነው። ጌታም የቶማስን ጥርጣሬ ያስወግድለት ዘንድ በተነሳ በስምንተኛው ቀን ቅዱስ ቶማስ ከሌሎች ሐዋርያት ጋር ሳለ እንደገና በትንሣኤ እንደታያቸው ሆኖ በዝግ ቤት ገብቶ ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ሐዋርያው ቶማስን ለይቶ "ቶማስ ቶማስ ና በችንካር የተቸነከሩ እጆቼን እይ እንዲሁም እጅሀን አምጥተሀ በጦር ወደ ተወጋው ጎኔ አግብተሀ ዳሰኝ ያመንክ እንጅ ተጠራጣሪ አትሁን ባለው ጊዜ ቶማስም በችንካር የተቸነከሩ እጆቹን በጦር የተወጋ ጎኑን በእጆቹ በዳሰሰ ጊዜ ከእሳት እንደገባ ጅማት ኩምትርትር ሲል "ጌታዬ አምላኬ" አለ። መዳሰሱን ሲያይ “ጌታዬ”፤ ማቃጠሉን ሲያይ “አምላኬ” አለ አምላክነቱንም መሰከረ፡፡ ጌታም  አንተ አይተኽ አምነሃል ነገር ግን" ሳያዩ የሚያምኑ ብፁአን ናቸው"ብሎ ፈውሶታል (ዮሐ. 20፥29)። (እስከ ዛሬም ይህቺ ጌታን የዳሰሰች የቅዱስ ቶማስ እጅ በሕንድ አገር ከታቦት ጋር በመንበሩ ላይ ትገኛለች)

በሌላ በኩል ዳግም ትንሣኤ የተባለበት በአከባበር፣ በሥርዓት የመጀመሪያውን ትንሣኤ ስለሚመስል ነው፡፡ የትንሣኤ ዕለት የሚባለው ቃለ እግዚአብሔር ሳይለወጥ፤ በሙሉ በዚህ ቀን ይባላል፡፡

ከዚህም ሌላ ሁለት መጠሪያ ስሞች አሉት፡፡ እነዚህም “#ፈጸምነ እና #አግብዖተ_ግብር” ይባላል፡፡ "ፈጸምነ" የተባለበት የሰሙነ ትንሣኤን በዓል አክብረን ፈጸምን ማለት ነው፡፡ "አግብዖተ ግብር" የተባለበትም ጌታችን ኢየሱስ  ክርስቶስ "አባ ወአቡየ ግብር ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ" "እኔ ልሠራው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር ላይ አከበርሁህ" ያለውን ከቅዳሴ በኋላ ሊቃውንት በዚህ ቀን ስለሚዘምሩት ነው፡፡ (ዮሐ.17፥4)

https://t.me/zekidanemeheret