ስንክሳር ወግጻዌ ዘተዋሕዶ
870 subscribers
3.46K photos
103 videos
194 files
1.2K links
የየዕለቱ ስንክሳር እና ግጻዌ የሚቀርብበት ቻናል ነው፡፡

ለማንኛውም አስተያየት እና እርማት
@zetaodokos ላይ ይላኩልን።

👇👇የYoutube Channel ይቀላቀሉ👇👇
https://youtube.com/channel/UCupqpIYe_mMpSM7jMT3Njhw
Download Telegram
ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡-

#ሰኞ- ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡

#ማግሰኞ- ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29

#ረቡዕ- አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡

#ሐሙስ- አዳም ሐሙስ ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡

#አርብ- ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡

#ቅዳሜ- ቅዱሳት አንስት ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡

#እሁድ- ዳግም ትንሳኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡


#እንኳን ለብርሃነ
#ትንሳኤው በሰላም
#አደረሳችሁ ::
ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡-

#ሰኞ- ማዕዶት ይባላል፡-
ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡

#ማግሰኞ- ቶማስ ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29

#ረቡዕ- አልአዛር ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡

#ሐሙስ- አዳም ሐሙስ ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡

#አርብ- ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡

#ቅዳሜ- ቅዱሳት አንስት ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡

#እሁድ- ዳግም ትንሳኤ ይባላል፡-
በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡

@zekidanemeheret
🌻በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
አሐዱ አምላክ አሜን 🌻

ረቡዕ ነሐሴ ፲፰ ፳፻፲፬ ዓ.ም

❇️ክርስቲያናዊ ሥነምግባር መልመጃ ፩ ❇️

መልመጃውን የምትሠሩት #የተማራችኹትን ብቻ በማስታወስ ይኹን እንጂ ከትምህርቱ እያያችሁ ወይንም ሰው በመጠየቅ አይኹን። "ትምህርቱን ምን ያህል ተረድቼዋለኹ?" ብላችኹ ራሳችኹን የምትገመግሙበት ነውና!

ስማችሁን፦
ከተማችሁን፦

መልሳችሁን @Zekidanemeheretbot
ላይ አስቀምጡ።

ለተጠየቁት ጥያቄዎች በተቻላችሁ አቅም አጭር መልስ አስቀምጡ።

1.የክርስቲያናዊ ሥነምግባር ትምህርት ዓላማዎች ቢያንስ 3ቱን ዘርዝሩ።

2.በክርስቲያናዊ ሥነምግባር ውስጥ የምንማራቸው 10ቱ ትዕዛዛት ለምን 10 ሆኑ?

3.ከ10ቱ ትዕዛዛት ውስጥ በሐልዮ(በማሰብ)፣ በነቢብ(በመናገር) እና በገቢር(በተግባር፣በማድረግ) የሚፈጸሙት ትዕዛዛት ስንት እና ስንት ናቸው?

4.ክርስቲያን ምን ማለት ነው? 5ቱን ትርጉሞች ጻፉ።

5.ክርስቲያናዊ ሥነምግባር በመማር የምናገኘው ጥቅም ምንድንነው? ቢያንስ ሁለቱን ጥቀሱ።

6.ከ10ቱ ትዕዛዛት አንዷ............................. ትባላለች።

7.ክርስቲያናዊ ሥነምግባር ማለት ምን ማለት ነው?

8.10ቱ ትዕዛዛት ለእስራኤላውያን የተሰጠበትን ምክንያት ምንድንነው? ቢያንስ ሁለቱን ጥቀሱ።


መልስ ሠርታችሁ የምትልኩልኝ ከዚህ ሰዓት ጀምሮ በፈለጋችኹት ሰዓት እስከ ነገ #ሐሙስ_ማታ_12_ሰዓት ድረስ #ብቻ ይኾናል። ከተጠቀሰው ሰዓት ውጭ መላክ እንዳለመላክ ይቈጠራል።

(መልመጃውን ሠርቶ ለመላክ 21 ሰዓታት ተሰጥቷችኋል ማለት ነው።)

#አርብ_ማታ 3:00 ሰዓት ላይ ትክክለኛውን
መልስ እልክላችኋለሁ።
የክረምት ኮርስ ክርስቲያናዊ ሥነምግባር ፈተና (50%)

ስማችሁን፦
ከተማችሁን፦

መልሳችሁን @zetaodokos
ላይ አስቀምጡ።

ትእዛዝ ➊ ትክክለኛ መልስ የያዘውን
ሆሄ ብቻ ምረጡ። (15%)

1.በጎ ለማድረግ አውቆ አለመሥራት ኃጢአት ነው?

ሀ. እውነት
ለ.ሐሰት

2.በክርስቲያናዊ ሥነምግባር አንድ ሰው የተጣሉ ሰዎችን ለማስታረቅ ሲል መዋሸት ይችላል?

ሀ. እውነት
ለ. ሐሰት

3. "እርሱ ያገኘው ከእኔ ተሽሎ አይደለምና የእርሱ የሆነው ለኔ ሊሆን ይገባል" ብሎ ማሰብ [አትመኝ]የሚለውን ትእዛዝ አያፈርስም።

ሀ. እውነት
ለ.ሐሰት

4.ፍችን ከሚፈቅዱት ሕጎች ውስጥ አንዱ መካንነት ነው።

ሀ.እውነት
ለ.ሐሰት

5.ክርስቲያን ማክበር ያለበት የጋብቻ ሕግ የቱን ነው?

ሀ.የራስ ሃይማኖት ተከታይ የሆነን ብቻ ማግባት

ለ.በክርስቲያናዊ ሥርዓት ጋብቻን መፈጸም

ሐ.ዝምድናን ማክበር

መ.ሁሉም

6.እግዚአብሔር አምላክ መጀመሪያ የጻፈው ትእዛዝ የትኛውን ነው?

ሀ.የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ

ለ.አባትህን እና እናትህን አክብር

ሐ.አትግደል

መ.ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አታምልክ

7. የጋብቻ መሠረታዊ ዓላማ የሆነው የቱ ነው?

ሀ.ከዝሙት ለመጠበቅ

ለ.በሚስት ላይ ለመሰልጠን

ሐ.አርፎ ለመብላት

መ.በማኅበረሰቡ ዘንድ ለመከበር

8.ቅዱሳን ስዕላት እንዲሳሉ እግዚአብሔር አምላክ አቅጣጫ የሰጠበት ጥቅስ የቱ ነው


ሀ/ ዘጸ 37÷7

ለ/ 1ኛ ነገ 6÷23-29

ሐ/ ዘጸ 25÷19-20

መ/ ሁሉም

ሠ/መልስ አልተሰጠም

9.አንድ ሰው ክርስቲያናዊ ሥነምግባር እየሠራ ነው የምንለው ምን ሲያደርግ ነው?

ሀ.እንዳይታሰር በመፍራት ከሰው ጋር የማይጣላ ሲሆን

ለ.ለእግዚአብሔር የሚያስደስትን ነገር ብቻ ሚሠራ ሲሆን

ሐ.ሲሰጥ ብድርን እያሰበ የሚሰጥ ከሆነ

መ.ሁሉም


10.ክርስቲያን ማለት ምን ማለት ነው?

ሀ.ከክርስቶስ

ለ.ለክርስቶስ

ሐ.እንደክርስቶስ

መ.ሁሉም

ሠ.መልስ አልተሰጠም

11.መጽሐፍ ቅዱስ ............ ያሉትን የሥጋ አባቶች ብሎ ይጠራቸዋል።

ሀ.በአንድ አይነት የኑሮ ወገን ለ.ካሕናት ሐ.አሳዳጊ(ሞግዚት) መ.ሀ እና ሐ

12.የዘማዊነት መንስኤ የሆነው የትኛው ነው?

ሀ.የፍትወት ምስሎችን (ፊልሞችን) ማየት ለ.የጠበቀ የጾታ መቀራረብ
ሐ.ዘፈን መ.ሁሉም

13.የተገዢነት፣ የአክብሮት ፣ የትህትና መግለጫ የሆነው.................... ነው።

ሀ.ስግደት ለ.ጸሎት ሐ.ምጽዋት መ.እግዚአብሔርን መውደድ

14.ቅዱሳንን ማክበር ከእግዚአብሔር ውጪ የሆነ ልዩ አምልኮት ተብሎ አይቆጠርም።

ሀ.እውነት
ለ.ሐሰት

15.የእግዚአብሔር ወልድ ስም ያልሆነው የትኛው ነው?

ሀ.አማኑኤል ለ.ኢየሱስ ሐ.መሲህ መ.መልስ የለም

ትእዛዝ ➋ አዛምዱ (8%)

16.እግዚአብሔር ለሕዝቡ የሰጠው ቀዳማዊ ትዕዛዝ

17.የሰው ሕይወት ሊድንበት የሚችል ነገርን መከልከል

18.አምልኮታችንን በተግባር የምንገልጽበት መንገድ

19.ስለንብረት መጠበቅ የተሰጠ ሕግ

20.የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ ከምንጠራበት መንገድ

21.የጾታ ሕይወት በተቀደሰ ጋብቻ ተጠብቆ እንዲኖር የተሰጠ ሕግ

22.በተለየ ሁኔታ እድሜ የሚያስረዝም ትዕዛዝ

23.ስለሰው ልጆች ስማቸው ክብራቸው እንዲጠበቅ የተሰጠ ሕግ


ሀ.አታመንዝር ለ.ሰንበትን ማክበር ሐ.እናትና አባትን ማክበር መ.አትስረቅ
ሠ.ጸሎት
ረ.በሐሰት መማል ሰ.አትግደል
ሸ.በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር

ትእዛዝ ❸ በአጭሩ መልሱ።

24.ክርስቲያናዊ ሥነምግባር በመማራችሁ ያገኛችሁትን ጥቅም ከእውቀት አንጻር እና ከሕይወት አንጻር በሁለት ከፍላችሁ ጻፉ። (15%)

25.በ10ቱ ትእዛዛት ራሳችሁን መዝኑ። (15%)

መልስ ሠርታችሁ የምትልኩልኝ ከዚህ ሰዓት ጀምሮ በፈለጋችኹት ሰዓት እስከ ነገ #አርብ_ማታ_3_ሰዓት ድረስ #ብቻ ይኾናል። ከተጠቀሰው ሰዓት ውጭ መላክ እንዳለመላክ ይቈጠራል።

(መልመጃውን ሠርቶ ለመላክ 24 ሰዓታት ተሰጥቷችኋል ማለት ነው።)

#አርብ_ማታ 3:30 ሰዓት ላይ ትክክለኛውን
መልስ እልክላችኋለሁ።
ከትንሣኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡-

#ሰኞ
#ማዕዶት_ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡

#ማክሰኞ
#ቶማስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29

#ረቡዕ
#አልአዛር_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡

#ሐሙስ
#አዳም_ሐሙስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡

#አርብ
#ቅድስት+ቤተክርስቲያን_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡

#ቅዳሜ
ቅዱሳት_አንስት_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡

#እሁድ
#ዳግም_ትንሣኤ _ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡

👉🏻@zekidanemeheret
👉🏻@zekidanemeheret
👉🏻@zekidanemeheret