ስንክሳር ወግጻዌ ዘተዋሕዶ
813 subscribers
3.46K photos
104 videos
194 files
1.2K links
የየዕለቱ ስንክሳር እና ግጻዌ የሚቀርብበት ቻናል ነው፡፡

ለማንኛውም አስተያየት እና እርማት
@zetaodokos ላይ ይላኩልን።

👇👇የYoutube Channel ይቀላቀሉ👇👇
https://youtube.com/channel/UCupqpIYe_mMpSM7jMT3Njhw
Download Telegram
#ኦርቶዶክስ_መልስ_አላት
#ክፍል_2
#ፕሮቴስታንት /ጴንጤ /
ፕሮቴስታንት ተቃዋሚ ከሚለው የእንግሊዘኛ ቃል የተወሰደ ነው ። ይህም ሊሆን የቻለው የካቶሊክ ፓፓ የነበረው አቡነ ሊዎ አስረኛ የቅ/ጴጥሮስን ትልቅ ቤተክርስቲያን ለማሰራት በማሰቡ መንግስተ ሰማያት መግቢያ ብሎ ካርድ መሸጥ ጀመረ ። ማርቲን ሉተር ግን መንግስተ ሰማያት በክርስቶስ እንጂ በካርድ አይገባም ብሎ ተነሳ ።ይባስ ብሎም 90 ነጥቦችን ነቅሶ አውጥቶ ለጠፈላቸው ። ተቃዋሚ ሲሉትም ፕሮቴስት አሉት እሱን የተከተሉትን ደግሞ ፕሮቴስታንት አሏቸው ። አሁን ደሞ እስቲ ልዩነታችንን እንያቸው #1ኛ.ፕሮቴስታንት የንስሀ አባት አያስፈልግም ይላሉ ። ኦርቶዶክስ ግን ከ7ቱ ሚስጥራተ ቤተክርስቲያን አንዱ በመሆኑ ከታላቅ አክብሮት ጋር ትገለገልበታለች ። ጌታችን በወንጌል "ኃጢያቱን የተዋቹለት ቀረችለት ፡ "የያዛችሁበትም ተያዘችበት " በማለት አስተምሯልና ። (ዮሀ 20:23 ማቴ 16:19)። ደሞ በፕሮቴስታንት ሴቶች ስልጣነ ክህነት ሊኖራቸው ይችላል ። በኦርቶዶክስ ግን አይቻልም ። ጌታ የመረጣቸውና ስልጣነ ክህነትን የሰጣቸው ለወንዶች እንጂ ለሴቶች አይደለም ። #2ኛ. ፕሮቴስታንቶች የእምነት መሰረቱ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው ይላሉ ። ይህም ማለት በቤተክርስቲያን ሊቃውንት መፃህፍትና ሲወርድ በመጣው ቤተክርስቲያናዊ ትውፊትና አዋልድ መፃህፍት ላይ እምነት የላቸውም #3ኛ.ፕሮቴስታንቶች የቅዱሳን አማላጅነት አያስፈልግም ይላሉ ። ኦርቶዶክስ ግን ቅዱሳንን በተሰጣቸው ቃልኪዳን መሰረት ያማልዳሉ ብላ ታምናለች ። #4ኛ.ፕሮቴስታንቶች ጥምቀት እግዚአብሔርን ለማምለክ ምልክት እንጂ ድኀነት አያስገኝም ይላሉ ። በኦርቶዶክስ ግን በክርስቲያናዊ ህይወት የመጀመሪያ መግቢያ በር በመሆኑ ወደ ቤተክርስቲያን ለመግባትና ሚስጥራትን ለመካፈል አስፈላጊ መሆኑን ታምናለች #5ኛ.ፕሮቴስታንቶች ቁርባን መታሰቢያ እንጂ የክርስቶስ ሥጋና ደም አይደለም ይላሉ ።ኦርቶዶክስ ግን መለኮት የተዋሀደው ነብስ የተለየው ቁርባን አማናዊ የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው ትላለች #6ኛ.ፕሮቴስታንቶች ለመዳን ማመን ብቻ በቂ ነው ስራ አያስፈልግም ይላሉ ።ኦርቶዶክስ ግን እምነትና ምግባርን ነጣጥላ አትመለከትም ። ስራ የሌለው እምነት ነብስ የተለየው ስጋ ነው የሞተ ነው ትላለች ። #7ኛ.ፕሮቴስታንቶች መፅሀፍ ቅዱስን ሁሉም በሚገባው መልኩ መተርጎም ይችላል ይላሉ ። ኦርቶዶክስ ግን ማንም እንደፈለገውና እንደመሰለው እንዲተረጉም አትፈቅድም ።ወስብሀት ለእግዚአብሔር ። የአባቶቻችን የተባረከች በረከታቸው ፡ ርትዕት ሀይማኖታቸው ፡ ጥርጥር የሌላት ድል የማትነሳ እምነታቸው ከኛ ትሁን ለዘለአለሙ አሜን ።

ምንጭ= ኰኲሕ ሐይማኖት
ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ኦርቶዶክሳዊ_የጾታ_ትምህርት
#ክፍል_2
#እውነተኛ_ፍቅር
"ወደ እውነተኛ ፍቅር ስንደርስ ወደ እግዚአብሔር መድረሳችንና የጉዞአችንም መጨረሻ ነው ። በእውነተኛ ፍቅር ተንሳፈን ከዓለም ባሻገር አብ ወልድና መንፈስቅዱስ ወዳሉበት ደሴት እንደርሳለን " (ቅዱስ ይስሐቅ/ሶርያዊ/ የእውነተኛ ፍቅር ምንጭ #እግዚአብሔር ነው ። እግዚአብሔር ደግሞ ለሁለት የፍቅር ተጓዳኞች ቃላት ሊገልፀው የማይችለው የመዋደድን ጸጋ ይሰጣቸዋል ። #ከልብ የሆነ ፍቅር በወርቅ ፣ በብር ፣ በዕንቁ ፣ በአልማዝና በፔትሮሊየም የማይለውጡት ፣ዝገት የማይበላው ፣ ቀናትና ዘመናት ሊሽሩት አቅም የማያገኙለት የእውነተኛ ስሜት ነጸብራቅ ነው ። #ፍቅር ጥልቅ ነገር ነው ። ለባልና ለሚስትም ትልቁ ሐብት ውበትና እርካታቸው #ፍቅራቸው ነው ።ባል ለሚስቱ ሚስትም ለባሏ የምትመግበው ፍቅር ትዳሩን በመልካም ውበት እንዲያሸበርቅ የሚያደርገው የሕይወት ፈርጥ ነው ።ራሳቸውን ለይተው /በገዳም ህይወት/ ለመኖር ከተሰጣቸው በስተቀር ሰው ያለ ፍቅር ብቻውን መኖር አይችልም። ለዚህ ነው እግዚአብሔርም አለ "ረዳት እንፍጠርለት"ያለው ። #ፍቅር በሀገር ርቀት ተገድቦ የሚወሰን አይደለም ። ፍቅርን ሀገር አይወስነውም ። ድንበርም አይከለክለውም ። ክልል ጥሶ የመጓዝ አቅሙም አስተማማኝ ነው ። ፍቅርን ሐብትና ድህነት ፣ በዜግነት መለያየትም አያግደውም ። ቅዱስ ጳውሎስ "አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም ባሪያ ወይም ጨዋ የለም " እንዳለው ሁሉም ሰው ለፍቅር እኩል ነው ። /ገላ 3÷28/ ። #ፍቅር ከባድ ኃይል ያለው ሕይወት ነው ። "ሰው እናትና አባቱን ይተዋል " እንደተባለው እናትና አባት ያህል ነገር እስከማስተው ድረስ ብርቱ አቅም አለው ። #ፍቅር ለማንም አይሸነፍም ። በማንም ልብ ውስጥ ገብቶ የሰውን ማንነት የሚያንበረክክ ጀግና ነው ። #እውነተኛ ፍቅር ማስመሰልን አያውቅም ። ከሽንገላም የጸዳ ነው ። ፍቅር በአንደበት ብቻ የሚገለፅ ሳይሆን በሥራና በእውነት የተደገፈም ነው ።"በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና በአንደበት ብቻ አንዋደድ /1ኛ ዮሐ3÷18/ ። #እውነተኛ_ፍቅር በጥቅም የማይለካ ፣ በመከራ ቀን የማይበገር ፣ የማይሞት ፣ ሁሌም የሚያብብና የማይደርቅ ፣ ጎርፍ የማይንደው ጠንካራና ጽኑ ነው ። "ፍቅር እንደ ሞት የበረታች ናትና... ብዙ ውሃ ፍቅርን ያጠፋት ዘንድ አይችልም ፡ ፈሳሾችም አያሰጥሟትም "ተብሎ /መኃ 8÷6/ የተመዘገበው ለዚህ ነው ። በአጠቃላይ ከእውነተኛ ፍቅር የሚታጨደው #ደስታ ነው ። ለዚህም ይመስላል ምሁራን "ሕይወት አበባ ሲሆን ፍቅር ደግሞ ከዚህ የሚቀሰም ማር ነው " ያሉት ። ፍቅር የሚጓጓለት ድንቅ የሕይወት አንዱ ክፍል ነው ። እውነተኛ ፍቅር የሕይወት ግሩም ቅመም ናትና ።በቀጣይ ክፍላችን ደሞ #12ቱን የፍቅር አይነቶች እናያለን ። ይቆየን

ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ትምህርተ_ንስሐ (በአቡነ ሺኖዳ)
#ክፍል_2
#የንስሐ_አፈፃፀም_3_ደረጃዎች
#ሀ የንስሀ የመጀመሪያ ደረጃ ኃጢአትን መተው ብቻ ሳይሆን ንስሐ ለመግባት ማሰብ ወይም መፈለግ ነው። ይህ ኃጢአትን ከመተው የሚቀድም ነው ። ሰዎች ንስሐ ለመግባት ባልፈለጉና ባላሰቡ መጠን በኃጢአት እየተደሰቱ ኃጢአትን እየሰሩ ይኖራሉ። በእነርሱ አመለካከትም የያዙት የኃጢአት ኑሮአቸው መልካም ስለሚመስላቸው አይለወጡም ። ስለዚህ ንስሐ ለመግባት ማሰብና መፈለግ የንስሐ የመጀመሪያ ደረጃ ነው ።
#ለ ሁለተኛው ደረጃ ፦ በንስሐ ሂደት ሁለተኛው ደረጃ ኃጢአትን መተው ነው ። ኃጢአትን መተው ሲባልም ኃጢአትን ከኅሊናና ከልቡና ጨርሶ በፍፁም ማጥፋት ነው ። ይህም ኃጢአትን ከማሰብ መለየት ማለት ነው ። ፀፀቱ ወይም ንስሐው ልቡናው ከኃጢአት እስኪነፃ ድረስ መሆን አለበት ። ከዚህ አንፃር ኃጢአትን መተው የንስሐ ሁለተኛው ደረጃ ነው።
#ሐ ሶስተኛው ደረጃ ፦ የንስሐ የመጨረሻ ደረጃ ኃጢአትን መጥላት ነው ። ይህም ኃጢአትን በፍፁም ልብ መጥላት ፣ አለማሰብና ባሕርይን ለኃጢአት አለማስገዛት ማለት ነው ። ይህ ደግሞ የፍፁምነት ደረጃ ነው ። ሰው ኃጢአትን ከልቡ ከአስወገደና ፍፁም ካላሰባት ከፍጹምነት ደረጃ ደርሷልና ንፁህ ነው ይባላል። ሰው በመንፈሳዊ ሕይወቱ ውስጥ ከፍተኛውንና ዋነኛውን ኃጢአት ለመተው የሚችለው በክርስትና ሕይወቱ የዕለት ተዕለት ብስለት የሚገለጡለትን ረቂቃን ኃጢአቶች በመተው ነው።
ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ክርስቲያናዊ_ሥነ_ምግባር
ተከታታይ ትምህርት
#ክፍል_2
@zekidanemeheret
#10ቱ_ትዕዛዛት (ኦሪ ዘፀ 20)
#1.እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ነኝ ከግብፅ ምድር ያወጣሁህ ነኝ ከኔ በቀር ሌሎቹ አማልክት አይሁኑልህ ።
#2.የእግዚአብሔር የአምላክህን ስም በከንቱ አታንሳ ። #3.የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ ።
#4.እናትና አባትህን አክብር ። #5.አትግደል
#6.አታመንዝር
#7.አትስረቅ
#8.በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር
#9.የባልንጀራህን ቤት አትመኝ #10.ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ።
🖊የክርስትና ህግ የፍቅር ህግ ነው ። ቅዱስ ጳውሎስ ሌላውን የሚወድ ሕግን ፈፅሞታል ካለ ቡሃላ ከ10ቱ ትዕዛዛት የተወሰኑትን በመጥቀስ #ፍቅር የሕግ ሁሉ ፍፃሜ መሆኑን በግልፅ ይናገራል። /ሮሜ 13÷8/ 🖊ጌታችን እንዳስተማረን ፍቅር በሁለት ይከፈላል ። #1ኛ_ፍቅረ_እግዚአብሔር #2ኛ_ፍቅረ_ቢፅ
🖊በሌላ በኩል ደግሞ ከአዎንታዊና አሉታዊ ከመነገራቸው አንፃር በሁለት ይከፈላሉ ።
#1ኛ_ሕግ_በአሉታ_የተነገሩ /አታድርግ/
#2ኛ_ትዕዛዝ_በአዎንታ_የተነገሩ /አድርግ/ ይባላሉ
🖊ከዚህም ሌላ ከአፈፃፀማቸው አንፃር ሲታዩ በሦስት ይከፈላሉ ። #1ኛ_በሐልዩ /በማሰብ/ የሚፈፀሙ ህግ1,3,4 እና 9 #2ኛ_በነቢብ /በመናገር/ የሚፈፀሙ ህግ 2,8
#3ኛ_በገቢር /በማድረግ/ ህግ 5,6,7,10 ናቸው ።
🖊#10ቱ ትዕዛዛት ለሙሴ በተሰጡ ጊዜ በሁለት የድንጋይ ፅላቶች ላይ ተፅፈው ነበር ። እንዲሁም ሁሉ በተለይም እስራኤል ዘነፍስ የምንባለው ለእኛ ለክርስቲያኖች ከልባችን ፅላት ላይ በመንፈስ ልንፅፈው ይገባል። በቤተክርስቲያናችን በፅላቶቻችን ላይ የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይገኛል ። ጌታችን ደግሞ ማንኛውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለው ካለ ቡሃላ ብትወዱኝስ ትዕዛዜን ጠብቁ ብሎ አስተምሯል ። እንዲህ ከሆነ የሚያስፈልገንን ነገር ለመለመን የጌታችን ስሙ ስለተፃፈበት በዙሪያው ተሰብስበን መለመን ያስፈልጋል ። ህጉ ከልባችን ስለማይጠፋ ሕጉን መጠበቅና መፈፀም ይገባናል ።
🖊ለዚህም በቀጣይ እያንዳንዳቸውን በዝርዝር እንማማራለን ።

ይቀጥላል....

@zekidanemeheret
ለሌሎችም ማጋራትን አይርሱ
👉ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@zekidanemeheret @zekidanemeheret @zekidanemeheret
#ፍኖተ_ቅዱሳን
#ክፍል_2
(በቀሲስ ደጀኔ ሽፍራው)
#10ሩ_ማዕረጋተ_ቅድስና
መንፈሳዊ ህይወት የቅድስና ኑሮ እንደ መሆኑ መጠን በጥምቀት ጀምሮ ደረጃውን የጠበቀ እድገት ያለበት ሕይወት ነው ።ከዚህም በሃላ እግዚአብሔርን በፍፁም ልቡናቸው ሰውነታቸውና ሕዋሳቶቻቸው እያመሰገኑ አሰረ ፍኖቱን የሚከተሉ ሰዎች ከቅድስና ወደ ከበረ ቅድስና ከሚኖሩበት መንፈሳዊ ኃይል ወደ ሌላ ታላቅ መንፈሳዊ ኃይል ይሸጋገራሉ ። እነዚህ የቅዱሳን የመንፈሳዊ ጉዞአቸው የእድገት ደረጃዎች 3 ናቸው ። እነዚህም #ወጣኒነት (ንፅሀ ስጋ) ፣ #ማዕከላዊነት (ንፅሀ ነፍስ) እና #ፍፁምነት (ንፅሀ ልቡና ) በመባል ይታወቃሉ ። በእነዚህ በእያንዳንዳቸው ስር ደግሞ የተለያዩ ማዕረጋት አሉ ።በንፅሀ ስጋ 3 በንፅሀ ነፍስ 4 በንፅሀ ልቦና 3 ሲሆኑ በጠቅላላው #10ሩ ማዕረጋተ ቅዱሳን በመባል ይታወቃሉ ።
#ንፅሀ_ሥጋ /ወጣኒነት/
ይህ ደረጃ ወጣንያን በባሕርዩ ፍፁም ከኾነው እግዚአብሔር ፍፁም ፀጋን ተቀብለው ለመክበር ቁርጥ ተጋድሎ የሚጀምሩበት ሕይወት ነው ። በዚህም ጊዜ ጠላት የተባለ ሰይጣን የተጋድሎ ሕይወታቸውን የሚያቀጭጭ ፈተና ያመጣባቸዋል ። እነርሱ ግን በፍፁም ተጋድሎ በእግዚአብሔር ፀጋ ከአንዱ ማዕረግ ወደ ሌላው ይሸጋገራሉ ።
#1ኛ #ጽማዌ ፦ ዝምታ ማለት ነው ። ይኸውም አውቆና ፈቅዶ በመናገርና በመቀባጠር ከሚመጣው ኃጢአት መቆጠብ ነው ።ይህን የመጀመሪያውን ደረጃ በዝምታ ማለፍም ታላቁን የሰይጣን ፆር /እሳትን / በተጋድሎ ማጥፋት ነው ።አንደበት እሳት ነውና።
#2ኛ #ልባዌ ፦ ልባዊ ማለት ልብ ማድረግ ፣ ማስተዋል ማለት ነው ። ጌታ በወንጌል "መስማትንስ ትሰማላቹ ነገር ግን አታስተዉሉም " ይላቸው የነበረው ማስተዋል ታላቅ ማዕረግ ስለሆነ ነው ።
#3ኛ #ጣዕመ_ዝማሬ ፦ይህ ደግሞ ሳይሰለቹና ሳይቸኩሉ ምስጢርና ትርጓሜውን እያወጡ እያወረዱ በንቁ ሕሊና ማመስገንና መጸለይ ማለት ነው ። አንድ ሰው የሚፀልየውን ፀሎትና የሚያቀርበውን ምስጋና በትርጓሜና በምስጢር በውሳጣዊ ልቡናው እያዳመጠ የሚያደርሰው ከሆነ ተመስጦን ገንዘብ ማድረግ ይቻለዋል ። ጸጋ መንፈስ ቅዱስንም እየተጎናፀፈ ከዚህ ከስጋዊ አለም ማምለጥ ይቻለዋል።
... ይቀጥላል ...

👉ለመቀላቀል 👇👇👇
@zekidanemeheret @zekidanemeheret @zekidanemeheret
"የሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ"
ዝማሬ ዳዊት On Telegram
👉 የሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ
🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
"የማክሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ"
ዝማሬ ዳዊት On Telegram
👉 የማግሰኞ ውዳሴ ማርያም አንድምታ
🎙 ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
2_5276342373670979386.mp4
62.6 MB
📺 መንፈሳዊ ፊልም
👉 ግብፃዊቷ ቅድስት ማርያም
              #ክፍል_2

📍WiFi ብትጠቀሙ ይመረጣል