STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.8K subscribers
11K photos
271 videos
452 files
1.93K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
Photo
" እባክችሁ መፍትሄ ስጡን ፤ ጊዜው ያለ ትምህርት እየሄደብን ነው " - ተማሪዎች

በአማራ ክልል ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የሚማሩ ተማሪዎች እስካሁን ወደ ትምህርት እንዳልተመለሱ በመግለፅ ትምህርት ሚኒስቴር መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጥሪ አቀረቡ።

መልዕክታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩ ተማሪዎች እስካሁን የሚማሩባቸው ግቢዎች እንዳልጠሯቸው በማመልከት ያለ ትምህርት መቀመጣቸውን ገልጸዋል።

በእነሱ እድሜና ተመሳሳይ የትምህርት ደረጃ የሚገኙ በሌሎች ክልሎች በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ጓደኞቻቸው ትምህርታቸውን ለመጀመር ወደ ሚማሩበት ተቋም ከበርካታ ቀናት በፊት መግባታቸውን እነሱ ግን እስካሁን መቼ እንኳን እንደሚጠሩ እንደማያውቁ በመግለፅ ትምህርት ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ መፍትሄ ቢሰጥ ብለዋል።

ተማሪዎቹ ከእኩዮቻቸው ወደ ኃላ እየቀሩ መሆኑን አመልክተው ይህም የሚያሳድረው ጫና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የፊልድ ምርጫ ካደረጉ በኃላ ወደቤት ተመልሰው ከወራት በላይ ያለትምህርት መቀመጣቸውን አመልክተዋል።

" ትምህርት ሚኒስቴር ስለኛ ጉዳይ ችላ ማለት የለበትም " ሲሉ ያሳስቡት ተማሪዎቹ የትግራይ ተማሪዎች አይነት ዕጣ ፋንታ እንዳይደርሰን ከወዲሁ አፋጣኝ መፍትሄ ይፈለግልን ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

በሌላ በኩል ፤ በአማራ ክልል ባለው ተለዋዋጭ የሆነ የፀጥታ ሁኔታ ከአማራ ክልል ወደ ተለያዩ ክልሎች ወደሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ሄደው መማር ያልቻሉ ተማሪዎች ስለመኖራቸው ለማወቅ ተችሏል።

ተማሪዎቹ በፀጥታ ሁኔታ ምክንያት ለመሄድ መንገዶች ፈታኝ እንደሆነባቸው አመልክተዋል።

አቅም ያላቸው በአየር ትራንስፖርት ፤ አንፃራዊ ሰላም ያለባቸው ቦታዎች የሚኖሩ በብዙ ብር በየብስ ትራንስፖርት ወደ ሚማሩበት ተቋም መግባታቸውን ነገር ግን የፀጥታና ደህንነት ሁኔታው ባልተሟላባቸው በተለይ ጎጃም አካባቢዎች ያሉ ተማሪዎች ወደ ትምህርት መመለስ እንዳልቻሉ የደረሱን መልዕክቶች ያስረዳሉ።

ያለው የትራንስፖርት ዋጋም ውድ በመሆኑና መንገዶችም ስለሚያሰጉ እንደ " ቀይ መስቀል " አይነት ተቋማት እስካሁን ወደ ተቋማቸው ያልገቡ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ተቋማቸው የሚወስዱበት መፍትሄ እንዲፈለግ ጠይቀዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ተወካይ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑን ለቪኦኤ ሬድዮ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

ዶ/ር ሰለሞን ፤ የደህንነት ችግር ካለባቸው አካባቢዎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ወደ ተቋማቸው የመመለሱ ስራ የሚሰራው ከወታደራዊ ኮማንድ ፖስት ጋር በመተባበር ነው ብለዋል።

" አሁን ባለው ሁኔታና ካለው የፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ዩኒቨርሲቲዎች በሴኔት ተማሪዎችን የሚቀበሉበትን ቀን እየወሰኑ ተማሪዎችን እየጠሩ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው። ይሄ ደግሞ እየተሰራ ያለው በዋናነት የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች በአካባቢው ከሚገኙ የኮማንድ ፖስት አካላት ጋር በቅርብ እየተወያዩ ለተማሪዎች ካለው Safety እና Security አኳያ እየተገመገመ እየተሰራ እንደሆነ እናውቃለን " ብለዋል።

" እንደ ትምህርት ሚኒስቴርም ያለው concern ትክክለኛ ስለሆነ በቅርብ እየተከታተልን ነው። የሚፈለገው የድጋፍ እና ክትትል ስራ እየሰራን ነው። እስካሁን የጎላ ችግር አልቀረበም በኛ በኩል ቀጣይ የሚነሱ ችግሮች ካሉ በዛው ካለው የፀጥታ አካላት ጋር በጋራ ሆነን እንሰራለን " ሲሉ ተናግረዋል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
Photo
#ጥቆማ

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፤ በ2014 ዓ.ም እና 2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን የዩኒቨርስቲ መግቢያ መቁረጫ ውጤት ያመጡ እና በፖሊስ የሙያ ዘርፍ ሀገራቸውን ለማገልገል #የሚፈልጉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደሚፈልግ አሳውቋል።

ተቋሙ ለ4  አመታት በ " ፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ " አስተምሮ በመኮንንነት (ረዳት ኢንስፔክተር ማዕረግ) በማስመረቅ በተለያዩ የፌደራል ፖሊስ የስራ ክፍሎች አስመድቦ ለማሰራት እንደሚፈልግ ነው የገለፀው።

በተጨማሪ በ "ፎረንሲክ ሳይንስ ዲግሪ" አስተምሮ በመኮንንነት (ረዳት ኢንስፔክተር ማዕረግ) በማስመረቅ በፎረሲክ ምርመራ የላብራቶሪ ሙያተኝነት (ኤክስፐርት) በማስመደብ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡

በተቋሙ በ  " ፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ " ለመማር የሚያስፈልጉ የመመልመያ መስፈርቶች ከላይ በምስሉ የተዘረዘሩ ሲሆን ከነሱም ውስጥ ፦

- አመልካቾች ከማንኛውም ወንጀል ነፃ ስለ መሆኑ ከሚኖርበት ወረዳ ፖሊስ ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው።

- ለፖሊስ አካል ብቃት ስልጠና ብቁ የሆነ አካላዊ አቋምና አዕምሮ ጤንነት ያላቸው ሊሆኑ ይገባል።

- በ2014 ዓ/ም እና 2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባ የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስተር መቁረጫ ውጤት ያላቸው  የትምህርት ማስረጃቸውንም ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።

- የ #ሪሚዳል_ትምህርት ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡ ከሆነም ማስረጃ ማቅረብ አባቸው።

- አመልካቾች እድሜያቸው ከ18 እስከ 28 ዓመት መሆን አለበት።

- ቁመት ለወንድ 1.65 እና ከዚያ በላይ፣ ለሴት 1.55 እና ከዚያ በላይ፣
ሲሆን የተስተካከለ የሰውነት ክብደት 18.5-24.9 kg/m) ያለቸው ሊሆኑ ይገባል።

- ከተመረቁ በኋላ 7/ሰባት/ አመት በተማረበት የፖሊስ ሙያ በየትኛውም የአገሪቱ ክልልና የፖሊስ የስራ መደቦች ላይ ተመድቦ ለመስራት ፍቃደኛ መሆን አለበት።

- ሴት አመለካቾች ከእርግዝና ነፃ መሆን አለባቸው።

- ሁሉም አመልካቾች ከዚህ በፊት የፖሊስ ወይም የመከላከያ ሰራዊት ስልጠና ያልወሰዱ መሆን ያለባቸው ሊሆኑ ይገባል።

ለ " ፎረንሲክ ሳይንስ ዲግሪ " ከላይ ያሉት አብዛኛው መስፈርቶች እንደተጠበቁ ሆነው ፦
- ዜግነት #ኢትዮጵያዊ
- የ12ኛ ክፍል #በተፈጥሮ_ሳይንስ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በ2014 ዓ/ም እና በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን መቁረጫ ውጤት ያላቸው
- በተፈጥሮ ሳይንስ የሪሚዳል ትምህርት ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል።

በሁለቱም የዲግሪ ትምህርት ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን የሚቀላቀሉት በራሱ በተቋሙ የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና ማለፍ ሲችሉ ብቻ ነው።

የት እና እስከመቼ መመዝገብ ይቻላል ?

ማመልከት የሚቻለው እስከ ጥቅምት 22/2016 ዓ/ም ድረስ ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት ነው።

ተማሪዎች በአካባቢያቸው በሚገኝ በሁሉም የክልል እና የከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽኖች በአካል በመገኘት መመዝገብ ይችላሉ።

ለመዝገባው የትምህርት ማስረጃቸውን የ8ኛ ፣ የ10ኛና 12ኛ ክፍል ካርድ እና ትራንስክርፕት ኦርጅናል ከማይመለስ አንድ ፎቶ ኮፒ ጋር ይዘው መቅረብ አለባቸው።

#ደመወዝ / #ክፍያን በተመለከተ ፦

ዕጩ መኮንኖች በትምህርት ላይ በሚቆዩበት ጊዜያት ከ3 ወር የሙከራ (recruit) ጊዜ ቆይታ በኋላ እስከሚመረቁ ድረስ የኪስ ገንዘብ/ደመወዝ ታስቦ ይከፈላቸዋል ተብሏል።

ስልክ ካስፈለጋችሁ ፡ 0116735564

(ተጨማሪ ዝርዝር ጉዳዮችን ከላይ በምስሉ ያንብቡ)

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
የቻይና ሳይንቲስቶች ስምንት አዳዲስ የማይታወቁ ቫይረሶችን አግኝተዋል ፥ ሙከራም ሊያደርጉባቸው አቅደዋል።

ከቫይረሱ ዝርያዎች አንዱ የCOVID-19 የሆነ የአንድ ቤተሰብ አባል ሲሆን ሌሎች ደግሞ ካንሰርን ሊያስከትሉ ይችላሉ  የሚል ግምት አለ።
 
የሳይንስ ሊቃውንት እነዚህ ቫይረሶች ዝርያቸው ከቀጠለ   ለሰው ልጆች አደገኛ ሊሆኑ እንደሚችሉ ይናገራሉ።

@NATIONALEXAMSRESULT
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በአካዳሚክ ጉዳዮች ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሚጄና አማካኝነት ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በላከው ደብዳቤ በ2016 ዓ.ም አጋማሽ ላይ ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ዝግጅት ለማድረግ እንዲቻል ለፈተናው የሚቀመጡ ተማሪዎች መረጃ በአስቸኳይ እንዲላክለት ጠይቋል።

ሚኒስቴሩ ፤ ተቋማት መረጃው እጅግ ቢዘገይ እስከ ጥቅምት 16 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲልኩ ያሳሰበ ሲሆን የማያሳውቅ ዩኒቨርሲቲ " ተፈታኝ ተማሪ የለውም " በሚል ተይዞ የሚታቀድ መሆኑን በጥብቅ አስገንዝቧል።

በ2015 ዓ/ም ለመጀመሪያ ጊዜ በተሰጠው የመውጫ ፈተና በመንግስት ተቋማት ለፈተናው ከተቀመጡት 77,981 ተማሪዎች ውስጥ 50 እና ከዚያ በላይ በማምጣት ያለፉት 48,632 ተማሪዎች ወይም 62.37 በመቶ መሆናቸው አይዘነጋም።

በግል ተቋማት ደግሞ ለፈተና ከተቀመጡት 72,203 ተማሪዎች ውስጥ 50 እና ከዚያ በላይ ውጤት አምጥተው ያለፉት 12,422 ተማሪዎች ወይም 17.2 በመቶ ብቻ ነበሩ።

በድምሩ ከአጠቃላይ 150,184 የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ፈተናውን ያለፉት 61,054 ብቻ ወይም 40.65 በመቶ ናቸው።

የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና አስተዳደር መመሪያ እንደሚያሳየው ከሆነ ፈተናው በዓመት ሁለት ጊዜ ይሰጣል። የመጀመሪያው በአመቱ መጨረሻ ሲሆን ሁለተኛ በአመቱ አጋማሽ ነው።

የመጀመሪያውን የመውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች በዚህ አመት አጋማሽ ላይ በሚዘጋጀው ሌላ ፈተና መፈተን የሚችሉ ሲሆን ከዚህ ቀደም ትምህርት ሚኒስቴር  ተፈታኞች ዳግም ፈተና ለመውሰድ መጀመሪያ ሲማሩበት ወደነበረበት ተቋም መሄድ ሳይጠበቅባቸው ባሉበት አካባቢ ባሉ ተቋማት ፈተናውን እንደሚወስዱ የሚደረግበት ስርዓት እንደሚዘረጋ መግለፁ አይዘነጋም

@NATIONALEXAMSRESULT
#MoE

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ ከሚማሩት ትምህርት ውጪ ወደ ተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ሔደው ለሚያደርጓቸው የተግባር ላይ ልምምዶች የሚደረግ ወጪ÷ ከምርቃት በኋላ በሚከፍሉት የወጪ መጋራት ውስጥ እንዲካተት ጥናት መጀመሩ ተገለጸ፡፡

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የወጪ መጋራት (Cost Sharing) መመርያ መሠረት ወደ መንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተቀላቀሉ አዳዲስ ተማሪዎች÷ ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ ተመርቀው እስኪወጡ ድረስ፣ መንግሥት ለምግብና ለመኝታ ያወጣውን ወጪ በሚገቡት ውል መሠረት ከምርቃት በኋላ ግዴታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተደንግጓል፡፡

ተማሪዎች ወደ ተግባር ልምምድ ሲወጡ ለሚቆዩባቸው ጊዜያት ለሚኖራቸው የተግባር ላይ ትምህርት፣ ከምረቃ በኋላ ከወጪ መጋራት ጋር ተደምሮ እንዲከፍሉ ለማድረግ የትምህርት ሚኒስቴር ዕቅድ መያዙንና ጥናት መጀመሩን፣ በትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር ተሾመ ዳንኤል ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል፡፡

ሐሳቡ በጥናት ላይ መሆኑንና ዓላማውም ወደፊት ተማሪዎች የተግባር ላይ ልምምድን ትኩረት ሰጥተው እንዲማሩ ለማድረግ በማሰብ የታቀደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ይሁን እንጂ ለክፍያው የልማት አጋር ድርጅቶች ለትምህርት ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች ትስስር የሚመድቡት ገንዘብ ስለሚኖር፣ ከዚህ ገንዘብ ለወጪ መጋራት ሊከፈል የሚችልበት አሠራርም ሊዘረጋ እንደሚችልም አስረድተዋል፡፡

መረጃው የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#የምስራች @#Exitexam Tutorial
🥇 ለአካውንቲንግ
🥇 ለማኔጅመንት
🥇 ለቢዝነስ ማኔጅመንት
🥇ለማርኬቲንግ ማኔጅመንት
🥇ለሲቪል ምህንድስና
🥇ለኮምፒውተር ሳይንስ
#የመውጫ ፈተና መዘጋጃ #ልዩ ትምህርት
➾  በአንጋፋ ፕሮፌሰሮችና የዪኒቨርስቲ
      መምህራን
➾ በት/ት ሚ/ር ለፈተና በተመረጡ ኮርሶች
      ላይ ብቻ: የፈተና ጥያቄዎች ላይ በማተኮር
➾ በቂ የጥናት ሞጁሎች
➾ ሞዴል የመለማመጃ ፈተናዎች ከሙሉ
      መልስና ማብራሪያ  ጋር
➾ የኦንላየን መለማመጃ   ሲስተም
➾ ውጤታማ የፈተና አሰራር ሥልጠና
***
💥 እጅግ በተመጣጣኝ ክፍያ 

🛎 በየማዕከላቱ ያሉ ውስን ቦታዎች ቀድመው
      ይያዙ
🔔 ሙሉ  ስምዎን  : የስልክ ቁጥርዎንና
     ዲፓርትመንትዎን 0908-198-786 
      ላይ ቴክስት በማድረግ ይመዝገቡ ።
➾➾➾➾➾➾
ለበለጠ መረጃ
➧ 0908198786 ማነጋገር ይቻላል።

➧➧     #Joinus @ t.me/aec_ethiopia

አድቫንስድ የት/ት ማማከር ማዕከል
           ከፍላጎትዎ ባሻገር !!!
#AASTU

በ2016 ዓ.ም በአዲሰ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ እና የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርት ለመማር ያመለከታችሁና ብሔራዊ የመግቢያ ፈተና (GAT) ወስዳችሁ የተቀመጠውን ማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ አመልካቾች ምዝገባ ጥቅምት 19 እና 20/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ የትምህርት ማስረጃዎች፦

• ዲግሪ እና ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣

• ሁለት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣

• የወጪ መጋራት የሚመለከታችሁ አመልካቾች ከወጪ መጋራት ነጻ መሆናችሁን የሚገልፅ ማስረጃ

• ኦፊሺያል ትራንስክሪፕት ከተማራችሁበት ዩኒቨርሲቲ ማስላክ

• የመመዝገቢያ ክፍያ መክፈላችሁን የሚያረጋግጥ ደረስኝ - Online ላመለከታችሁ ብቻ፣

• ከግል ከፍተኛ ተቋማት የተመረቃችሁ ተማሪዎች በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ትክክለኛነቱን የተረጋገጠ የትምህርት ማስረጃ ማቅረብ፣

• መንግሥታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ስፖንሰር የተደረጋችሁ አመልካቾች ኦሪጂናል የስፖንሰርሺፕ ደብዳቤ ማቅረብ።

ለሦስተኛ ዲግሪ አመልካቾች የምርምር ሥራ ሃሳብ (Concept Note/Synopsis/Draft Research Proposal) ማቅረቢያ ቀናት ጥቅምት 19 እና 20/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ArbaMinchUniversity

በ2016 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል ተመዝግባችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠውን የመግቢያ ፈተና ማለፋችሁን የሚገልጽ መረጃ በመያዝ ከጥቅምት 19 እስከ 23/2016 ዓ.ም ምዝገባ እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

የ2ኛ ዲግሪ አመልካቾች የመጀመሪያ ዲግሪ ፤ የ3ኛ ዲግሪ አመልካቾች የመጀመሪያ እና የ2ኛ ዲግሪ ኦፊሺያል ትራንስክሪፕት በፖስታ ሳጥን ቁ. 21 ወይም በኢሜይል አድራሻዎች official@amu.edu.et / our@amu.edu.et በኩል በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ማስላክ ይጠበቅባችኋል።
የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#HawassaUniversity

ዶ/ር አያኖ በራሶ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ሆነው እንዲቀጥሉ ተወሰነ።

ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ ዲራ ደግሞ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚደንት ሆነው እንዲያገለግሉ ተወስኗል።

ይህ ውሳኔ የተላለፈው ጥቅምት 18 ቀን 2016 ዓ/ም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ነው።

ከላይ ከተገለፀው ውሳኔ በተጨማሪ ለአራት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ ዕድገት በየደረጃው ተገምግሞ በዩኒቨርሲቲው ሴኔት የፀደቀውን ውጤት ቦርዱ በዝርዝር ከመረመረ በኃላ ጥያቄውን አፅድቋል።

ሙሉ ፕሮፌሰር የሆኑት ፦

- ከወንዶ ገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ፕሮፌሰር መሰለ ነጋሽ በ"Forest Ecology and Agroforestry"

- ከማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ ፕሮፌሰር ዘለቀ አርፊጮ በ "TEFL"

- ፕሮፌሰር መብራቱ ሙላቱ በ"TEFL" እንዲሁም

- ከተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ፕሮፌሰር ጀመረ በቀለ በ"Veterinary Parasitology" ናቸው።

መረጃው ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተገኘ ነው።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
የዩኒቨርሲቲ ምደባ

ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥቷል።

ማብራሪያ ፦

- የምደባ ስርዓቱ በተፈጥሮም ሆነ በማህበራዊ ሳይንስ መስኮች 1000 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በመጀመሪያ የዩኒቨርስቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸው ምደባ የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።

- የምደባ ስርዓቱ እያንዳንዱ ተማሪ ያስመዘገበውን አጠቃላይ ውጤት በምደባ ስርዓት ሂደት ውስጥ መለያ አድርጎ ይጠቀማል፡፡ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ሌሎች ተፈጻሚ የሚሆኑ ህግና ደንቦችን ባልጣሰ መልኩ ምርጫቸውን በመጠበቅ ረገድ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል።

- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የቅበላ አቅም ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ተማሪዎች 46 ዩኒቨርሲቲዎች ለምርጫ ቀርበውላቸዋል፤ በነዚህ ውስጥ ይመደባሉ።

- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች እና የተመረጡት ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የትምህርት ፕሮግራም መሰረት ያደረገ ነው ተብሏል።

- በተቋማት የጾታ ተዋጽኦን ለመጠበቅ በሚኖረው የምደባ ስርዓት የጾታ ተዋጽኦና ሚዛን እንዲጠበቅ መደረጉ ተገልጿል።

- የምደባ ስርዓቱ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሚመደቡ ተማሪዎችን ተዋጽኦ በጠበቀ መልኩ እንዲሆን እንደሚያግፅ ተነላክቷል። ይህም ከአንድ ት/ቤት የወጡ ተማሪዎች በአንድ ዩኒቨርሲቲ ወይም ፕሮግራም ውስጥ እንዳይታጨቁ ይደርጋል።

- የምደባ ስርዓቱ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት  ታሳቢ ያረገ ሲሆን ይህም ተመሳሳይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች አንድ ላይ እንዳይመደቡ በማድረግ የተለያየ ችሎታና ተሰጥኦ ያላቸው ተማሪዎችን ቀላቅሎ ለማስተማር እንደሚያግዝ ተገልጿል።

- የምደባ ስርዓቱ እንደ ወሊድ ያሉ ልዩ ሁኔታዎችን ያማከለ ነው ተብሏል። በመሰል ሁኔታ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ለመቀጠል የሚቸገሩ ከሆነ ትክክለኛ ለውጥና ድጋፍ የሚደረግ ይሆናል፡፡

-  በምደባ ወቅት የጤና ችግር ኖሮባቸው ትክክለኛ የሕክምና ማስረጃ ላላቸው ተማሪዎች ምደባው በተለየ መልኩ ሊታይ ይችላል።

- በተማሪዎቹ መካከል ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትዮች ካሉ የምደባ ስርዓቱ ከፍተኛ ነጥብ ያገኘው/ችው ተማሪ ከተመደበበት/ችበት የትምህርት ተቋም ቀሪው መንትያ ደግሞ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በቀጥታ ይመድባል።

- የምደባ ሲስተሙ የአካል ችግር ላለባቸው ተማሪዎች እኩል እድሎችን የሚሰጥ ሲሆን ልዩ ፍላጎቶቻቸውን እና ለምደባ መስፈርቶቻቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት የሚሰራ ይሆናል።

ትምህርት ሚኒስቴር ሀሰተኛ የህክምና ማስረጃ  የሚያቀርብ ተማሪ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከምደባ ውጭ የሚሆን መሆኑን አሳስቧል።

ትምህርት ሚኒስቴር

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
#ጥቆማ

የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ የርቀት ትምህርት አገልግሎት መስጠት ለሚፈልጉ ተቋማት ጥሪ አድርጓል።

በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በትግራይ ያለው የትምህርት ሽፋን አደጋ እንደገጠመው የገለጸው ቢሮው፤ በክልሉ ያለውን የትምህርት ሽፋን ለማሳደግ የርቀት ትምህርትን እንደ አማራጭ ማቅረቡን ገልጿል።

ቢሮው ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የርቀት መርሐግብር በአማራጭነት በማቅረብ የትምህርት ዕድል ያላገኙ ተማሪዎች የሚማሩበትን ዕድል አመቻችቷል።

በመሆኑም በትግራይ ክልል የርቀት ትምህርት ለመስጠት የምትፈልጉ ተቋማት ከጥቅምት 26/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 ቀናት ፕሮፖዛላችሁን ለክልሉ ትምህርት ቢሮ እንድታቀርቡ ጥሪ ቀርቧል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የሕክምና ትምህርት ለመማር አመልክታችሁ ተቀባይነት ላገኛችሁ የመግቢያ ፈተና የፊታችን እሁድ እንደሚሰጥ ኮሌጁ አሳውቋል።

የፈተና ቀን፦ ጥቅምት 25/2016 ዓ.ም ጠዋት 2:00

የፈተና ቦታ፦ መድኃኔአለም 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት

ተፈታኞች መታወቂያ፣ እስኪብርቶ፣ እርሳስ፣ መቅረጫ እና ላጲስ መያዝ ይጠበቅባችኋል። መታወቂያ ያልያዘ ተፈታኝ ወደመፈተኛ ክፍል መግባት እንደማይችል ኮሌጁ አሳስቧል።

ለፈተናው የተመረጡ አመልካቾች ዝርዝር በኮሌጁ ድረገጽ ላይ ማግኘት የሚችሉ ሲሆን ቅሬታ ያላቸው አመልካቾች እስከ አርብ ጥቅምት 23/2016 ዓ.ም ጠዋት 4:00 በኮሌጁ ሬጅስትራር በመገኘት ቅሬታቸውን ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
ቴክኒክና ሙያ ተቋማት 600 ሺህ ተማሪዎችን ለመቀበል ተዘጋጅተዋል
****
(ኢ ፕ ድ)
12ኛ ክፍል ካጠናቀቁት ተማሪዎች ውስጥ በዘንድሮው ዓመት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚገቡ 600 ሺህ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት መደረጉን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ።

በሚኒስቴሩ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ እንደ ሀገር ከ700 በላይ የመንግሥትና ከ900 በላይ የግል የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ተቋማት አሉ።

እነዚህ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት 600 ሺህ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት አድርገዋል።

የትምህርት ተቋማቱ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ የ2016 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ሠልጣኞችን እንደሚቀበሉ የገለጹት ዶክተር ተሻለ፤ በዘንድሮው ዓመት 600 ሺህ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማሠልጠን የሚያስችል በቂ የትምህርት ግብዓት ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።

በቴክኒክና ሙያ ሥርዓተ ትምህርት በየዓመቱ ከሚሠለጥኑት የመደበኛ ፕሮግራም ሠልጣኞች በተጨማሪ በአጫጭር ሥልጠናዎች ሁለት ሚሊዮን ዜጎች......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=112560

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
“በጸጥታ ችግር ምክንያት 310 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ኾነዋል” የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ አሳሰበ።

በሰላም መደፍረስ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የኾኑ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ለመመለስ በትኩረት መሥራታ እንደሚገባ የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ አሳሰበ።

ከመስከረም ጀምሮ የትምህርት ዘመኑ የመማር ማስተማር ሂደቱ መጀመሩ ይታወቃል። የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ታደሰ ሸዋፈራው በሰጡን መረጃ “በጸጥታ ችግር ምክንያት በዞኑ 310 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ኾነዋል” ብለዋል።

በአንደኛ ደረጃ ትምህር ቤት መማር የነበረባቸው 219 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ናቸው። በተመሳሳይ በሁለተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች መማር የነበረባቸው 57 ሺህ ተማሪዎች የመማር እድል አላገኙም።

33 ሺህ የቅድመ መደበኛ ተማሪዎችም ወደ ትምህት ቤት አልሄዱም። በአጠቃላይ በዘንድሮው የመማር ማስተማር ጅማሮ 500 ትምህርት ቤቶች ከመማር ማስተማር ተግባር ውጪ ናቸው። አንድ ትምህርት ቤት ደግሞ የተማሪዎች ምዝገባ እንኳን አላደረገም።

የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ሂደት ውስጥ በርካታ ውስንነቶች መኖራቸው ይታወቃል። ከነዚህ ውስንነቶች መካከል የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ አናሳ መኾን፣ በሽፋንም ይሁን በጥራት የትምህርት መሠረተ ልማት በሚፈለገው ደረጃ አለመሟላት፣ የግብዓት እጥረት እንዲሁም በልዩ ልዩ መልኩ ሊገለጽ የሚችል የፍላጎት ማነስ ተጠቃሽ ናቸው።

በተጠቀሱት እና ተያያዥ ችግሮች ምክንያት በየትምህርት ክፍሎቹ የሚመዘገበው ውጤት አመርቂ አይደለም። ወደ ቀጣዩ የትምህርት ደረጃ የማለፍ ምጣኔው አናሳ እየኾነ ስለመምጣቱም ከሰሞኑ ይፋ በተደረገው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መረዳት ይቻላል።

አሁን ላይ በጸጥታ ችግሩ ምክንያት ታዳጊዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ደግሞ ችግሩን ‘በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ’ አድርጎታል። ባለሙያዎች በነጻነት ተንቀሳቅሰው የትምህርት ዘርፉን መደገፍ አለመቻላቸውንም አቶ ታደሰ ነግረውናል።

“የሁሉም ነገር መሰረቱ ሰላም ነው” ያሉት ኀላፊው ሰላም የጠፋበት አካባቢ ከልማት እና ከእድገት የተነጠለ መኾኑ አይቀሬ ስለመኾኑ አስገንዝበዋል። ስለዚህ ከምንም ነገር ቅድሚያ ለሰላም መስራት ይገባል ነው ያሉት።

የሰላምን ዋጋ በውል በመገንዘብ ስለሰላም እንሥራ፤ ተሻጋሪ አስተሳሰብ ያላቸውን ሀገር ተረካቢ ልጆች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱም ሁላችንም ጥረት እናድርግ ሲሉ ኀላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

#አሚኮ
የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot