መዝገበ ቅዱሳን
24.2K subscribers
1.97K photos
9 videos
6 files
26 links
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው! መ/ሳ 1÷7
Bewust mesimer lemanegager
@Yesadkusitota
የሰማነውን እንናገራለን
ያየነውን እንመሰክራለን
Download Telegram
#ጥር 4 ተዝካረ ፍልሰቱ #ለቅዱስ_ዮሐንስ_ሐዋርያዮሐንስ ወንጌላዊ ፤ ፍቁረ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ

#በተለያዩ_ቅጽል_ስሞች_የሚጠራ፤ (100 አካባቢ ከሚጠጉ ስሞቹ ጥቂቶቹን /21ዱን ስሞች ከጽሑፍ በስተመጨረሻ ይመልከቱ)
#ሰዓሊ_የኾነ፤ የጌታችንን ስነ ስቅለት የሳለ፡፡
#ከ81ዱ_የመጽሐፍ_ቅዱስ_ክፍሎች_5ቱንና_ሌሎች_መጻሕፍትንም_(ነገረ ማርያምን ..) የደረሰ፤
#ብዙ_ደቀ_መዛሙርትን_ያስተማረ

#share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ
ጌታ እናቱንም እነሆ ልጅሽ ያላት እርሱን ደቀ መዝሙሩንም እነኋት እናትህ ያለው ነው፡፡
ዮሐንስ ንጹሕ በአምሳለ ትጉሃን፤ (#ዮሐንስ_እንደ_መላእክት_ንጹሕ_ነው፤)
ዮሐንስ ድንግል ምክሐ ቅዱሳን፤ (#ዮሐንስ_ድንግል_የቅዱሳን_መመኪያ_ነው፤)
ዮሐንስ ስርግው በቀጸላ ሥን በሜላተ ብርሃን፤ (#ዮሐንስ_በብርሃን_መጐናጸፊያና_ሻሽ_የተጌጠ_ነው፤)
ዮሐንስ አርጋኖነ ዘቤተ ክርስቲያን፤ (#ዮሐንስ_የቤተ_ክርስቲያን_በገና_ነው፤)
✤ወበቃለ ቀርን ዘይኬልህ በኤፌሶን፥ ይስአል ለነ ስርየተ ለኀጥኣን፡፡ (#በኤፌሶን_ዐዋጅ_የሚናገር_ዮሐንስ_ኀጥኣን_ለምንሆን_ለኛ_ይቅርታን_ይለምንልን፡፡ /እመጽሐፈ ሰዐታት/

፨ ‹‹ሰላም ለአፉከ ለዮሐንስ ዘሰዓሞ፤
ንጽሐ ኅሊናሁ ወልቡ ለዐይነ ፍትወትከ ሶበ አደሞ›› /መልክአ ኢየሱስ/
፨ ሰላም ለሥዕልኪ ወለሥዕለ ወልድኪ ዘሰዓሞ፤
ዮሐንስ ርኄ ዮሐንስ ቀናንሞ፤
ለዝ ወልድኪ መሐሪ ኅሩመ በቀል ወተቀይሞ፤
ማርያም ሀብኒ በእዴኪ እንዘ ትጼውዒ ስሞ፤
ሥጋሁ ቅዱሰ ወክቡረ ደሞ፡፡ /መልክአ ሥዕል/

#100_አካባቢ_ከሚጠጉ_ስሞቹ_ጥቂቶቹን_21ዱን_ስሞች_እነኾ
#ሐዋርያው_ቅዱስ_ዮሐንስ
ዮሐንስ #ፍቁረ እግዚእ፥ (የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ለጌታ በጣም ቀራቢ ከነበሩት ሦስት የምሥጢር ሐዋርያት (ጴጥሮስ ፣ ናያዕቆብ ) ዮሐንስ ቀዳሚዉ ነዉ፡፡
ጌታችን ምሥጢረ ተአምራትን በኢያኢሮስ ቤት ፣ ምሥጢረ መንግስትን (መለኮትን) በደብረ ታቦር፣ ምሥጢረ ምጽአትን በደብረ ዘይት ፣ ምሥጢረ ጸሎትን በጌቴ ሴማኒ ሲገልጽና ሲያሳይ አብሮ የተመለከተ በመሆኑና ለጌታ በጣም ቀራቢ በመሆኑና በወንጌልም ‹‹ጌታ ይወደዉ የነበረ ደቀ መዝሙር ››ተብሎ ስለ ተጠቀሰ የጌታ ወዳጅ ፍቁረ እግዚእ ይባላል፡፡ዮሐ 13፡ 23 ፡፡
ወልደ #ዘብድዮስ
ዮሐንስ #ነባቤ መለኮት ፥
ዮሐንስ #ቦኦርኔጌስ
ዮሐንስ #አብቀለምሲስ ፥ (ፍጥሞ በምትባል ደሴት ላይም ወደ ፊት የሚሆነዉን ነገር በራእይ ስለተገለጸለት በግሪክ ቋንቋ አቡቀለምሲስ ተብሏል፡፡ትጉሙም የራዕይ አባት ማለት ነዉ፡፡)
ዮሐንስ #ወንጌላዊ
ዮሐንስ #ድንግል
ዮሐንስ #ታዎሎጎስ ቅዱስ ዮሐንስ ምሥጢረ ሥላሴንና ምሥጢረ ሥጋዌን አስፍቶ በመጻፉ (ታዎሎጎስ) ተብሏል፡፡ትርጉሙም ነባቤ መለኮት (የመለኮትን ነገር የሚናገር)ማለት ነዉ፡፡

1. #ዮሐንስ_ብፁዕ (ብፁዕ ዮሐንስ)
2. ዮሐንስ ድንግል
3. #ዮሐንስ_ፍንው
4. #ዮሐንስ_ካህን
5. #ዮሐንስ_ኅሩይ
6. ዮሐንስ ሥርግው
7. #ዮሐንስ_ምዑዝ
8. ዮሐንስ ቅኑይ
9. #ዮሐንስ_ማኅቶት
10. ዮሐንስ ቤዛ ሰማይ
11. #ዮሐንስ_ክቡር
12. ዮሐንስ ጻድቅ
13. #ዮሐንስ_ረድእ
14. ዮሐንስ ማኅቶት
15. #ዮሐንስ_ድንግል
16. ዮሐንስ ንጹሕ
17. #ዮሐንስ_ለባዊ
18. ዮሐንስ መረግድ
19. #ዮሐንስ_ዕንቈ
20. ዮሐንስ መልአክ
21. #ዮሐንስ_ኪሩብ
22. #ቁጽረ ገጽ
ቅዱስ ዮሐንስ እስከ መስቀል ድረስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለዉን መከራ በማየቱ ከዚያ ዕለት ጀምሮ 70 ዘመን ሙሉ ፊቱ በኅዘን የተቋጠረ በመሆኑ (ቁጽረ ገጽ) ሆኖ ኖሯል፡

ዓለምን ዞሮ ካስተማረ ቦኃላ በመጨረሻም ደቀ መዝሙሩ አብሮኮስን ከወንድሞችም ሌሎች ሁለትን መቆፈሪያ ይዘው ይከተሉት ዘንድ አዘዘ ፡፡ ጕድጓድም እንዲቆፍሩ አዘዘ ከዚያም ወረዶ ቆመ ልብሱንም አስወገድ የበፍታ ቀሚስ በቀር ሌላ አላረገም እየጸለየ ወደ ከተማም አሰናበታቸው በክርስቶስ ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ለሕዝብ ይነግሩአቸው ዘንድ አዘዘ ሁሉም እንደየ ስራው ጌታ እንደሚከፍላቸው ነገራቸው ካዛም እንዲህ አለ እኔ ከሁላችሁም ደም ንፁሕ ነኝ ከእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ ሳልነግራቹ የተውኩት ምንም ምን የለምና እናንተም ከእንግዲህ ከቶ ፊቴን አታዩኝም ፡፡ እጅና እግሮቹን ስመውት ትተውት ሄዱ ሲመለሱም ልብስና ጫማ እንጂ ምንም አላገኙም እግዚአብሔርንም አመሰገኑት ፡፡ዘጠና ዓመትም ኖረ፤ እንደባላሟሎቹ ሐዋርያት በመሰየፍ ሞትን አለቀመሰም፡፡ ስለ ድንግልናውና ስለንጽሕናው ይህ ሁሉ ሆነ፡፡
በዚህ በከበረ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን አሜን

#share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ

✤✤✤✤በኢዲስ አበባ ማክበር ለምትፈልጉ✤✤✤✤
✤✤✤✤✤#ደብረ_ነጐድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስና_መካነ_ጎልጎታ_ማርያም_ቤ_ክ_ማዕከላ_ለአዲስ_አበባ /መሐል አዲስ አበባ ከራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል አጠገብ የሚገኝ፤ ታቦተ ሕጉ ከኢየሩሳሌም የመጣና በአዲስ አበባ ብቸኛው የወልደ ነጐጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ./፤ (አዲስ አበባና በአካባቢዋ ያላችሁ በዚሁ ደብር እንድንገናኝ ይሁን)

✤✤ሥርዓተ ማኀሌቱን ከታች ይመልከቱ::
#ጥር 4 (#የሐዋርያው የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዓመታዊ ክብረ በዓል ፤ የአባ ናርዶስ ዘደብረ ቢዘን እረፍቱ ፡፡ የጊዮርጊስ፤ የሊቀ ጳጳሳት ማርቴና፤ የሰማዕት ታኦድራ፤ የአባ ሊቃኖስ፤ የቀውስጦስ መታሰቢያቸውም ነው፡
@petroswepawulos