መዝገበ ቅዱሳን
24.2K subscribers
1.97K photos
9 videos
6 files
26 links
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው! መ/ሳ 1÷7
Bewust mesimer lemanegager
@Yesadkusitota
የሰማነውን እንናገራለን
ያየነውን እንመሰክራለን
Download Telegram
#ጥር_21

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን ለእመቤታችን ለከበረች #ድንግል_ማርያም የእረፍቷ መታሰቢያ ነው፣ የከበረች #ቅድስት_ኢላርያ አረፈች፣ የባስልዮስ ወንድም የከበረ #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ የእረፍቱ መታሰቢያ ነው፣ የካህኑ ኬልቅዩ ልጅ ታላቁ #ነቢይ_ኤርምያስ መታሰቢያው ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#በዓለ_አስተርዕዮ_ማርያም

ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለድች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በአል መታሰቢያ ነው።ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃበሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም አለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኃላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።

በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦ "ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሩዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሀንስን በዚች ሰአት አምጣው።እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሀዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።

በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሀንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ አለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ህይወት ትሄጂአለሽና። ይህም ስሙ ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኃላ ነው።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላትእግዚአብሄርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።

በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሀዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።

ወዲያውኑ ሁሉም ሀዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት አምላከችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆን ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ አለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት።

በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሀዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኃችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም አለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ።

ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት።

እመቤታችንም ማርያምም ይህን ነገር ከሀዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ።የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።

ፀሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሀዋርያትን እንዲህ አለቻቸው እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረገ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለቸወበት ቤት በቀረብ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።

ከዚህም በኃላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም አላት።

ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሀወሰርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጃዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሀዋርያትን አዘዛቸው።

ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት።

እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።

ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም አለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።

እመቤታችንም ከአረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሄር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።

ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሀዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።

በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።

ሀዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሀዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።
#ጥር_22

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም

ጥር ሃያ ሁለት በዚች ቀን የሊቀ መላእክት #ቅዱስ_ዑራኤል በዓለ ሲመቱ ነው፣ የከበረና የገነነ የመነኰሳት ሁሉ አባት አባት #ቅዱስ_እንጦንስ አረፈ፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ዑራኤል_ሊቀ_መላዕክት

ጥር ሃያ ሁለት በዚህች ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል በዓለ ሲመቱ ነው፡፡

ኢዮር፣ ራማ እና ኤረር የተባሉ ሦስት የመላእክት ከተሞች አሉ፡፡ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክት ከፈጠራቸው በኋላ በነገድ 100 በአለቃ 10 አድርጎ በሦስቱ ሰማያት አስፍሯቸዋል፡፡ ኢዮርን በ4፣ ራማን በ3፣ ኤረርንም በ3 ከፍሎ ነው በዐሥሩ ከተማ ያሰፈራቸው፡፡

በዚህም መሠረት ኢዮርን ላይና ታች አድርጎ በ4 ከተማ ከፍሏታል፡፡ በእርሷ ያሉትን መላእክትን በ40 ነገድ 4 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያው ነገድ ‹‹አጋእዝት›› ይባላሉ፡፡ አለቃቸው ሣጥናኤል ነበር፤ እርሱም የመላእክትን ሁሉ ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርግ ነበር፡፡ ከክብሩ ሲዋረድ ቅዱስ ሚካኤል በምትኩ ተሹሞበታል፡፡ ሁለተኛው ነገድ ‹‹ኪሩቤል›› ይባላሉ፡፡ እነርሱም መንበረ ሥላሴን ይሸከማሉ፡፡ የቀሳውስት አምሳል ናቸው፡፡ አለቆቻቸው ገጸ ሰብና ገጸ አንበስ ናቸው፡፡ በሦስተኛው ከተማ በኢዮር ያሉት ሱራፌል ይባላሉ፡፡ የዲያቆናት አምሳል ናቸው፡፡ በትንቢተ ኢሳያስ በምዕራፍ 6 ላይ የተገለጹትና ኢሳያስን ከለምጹ እንዲፈወስ ያደረጉት ናቸው፡፡ አለቆቻቸው ገጸ ላህምና ገጸ ንስር ናቸው፡፡ (በነገራችን ላይ ‹‹ከሩቤል›› ወይም ‹‹ሱራፌል›› የሚባሉ የግለሰብ መጠሪያ ስሞች ስህተት ናቸው፡፡ አንደኛ እነዚህ ስሞች የብዙ መላእክት መጠሪያን የሚወክሉ ናቸው፡፡ ለአንዱ ሲሆን ‹‹ኪሩብ፣ ሱራፊ›› ይባላል፡፡ ‹ኪሩቤል› ወይም ‹ሱራፌል› ማለት ግን የብዙ ቁጥራቸው መጠሪያ ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የቅዱሳን መላእክትን ስም እንዳለ በቁሙ ወስዶ ለግል መጠሪያ ስም ማዋል ተገቢ አይደለም፡፡ ‹‹ወለተ ሚካኤል፣ ክንፈ ገብርኤል….›› እየተባሉ ይሰየማሉ እንጂ ቀጥታ ‹ሚካኤል›፣ ‹ገብርኤል› እያሉ ሰዎችን መሰየም ስህተት ነው፡፡ 4ኛው ከተማ በኢዮር ያሉት ኃይላት ይባላሉ፡፡ የእሳት ሰይፍ ይዘው በሥሉስ ቅዱስ ፊት የሚቆሙ ናቸው፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት የዛሉና የደከሙ ክርስቲያኖችን የሚያበረታቱ ናቸው፡፡ አለቃቸውም ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡)

ዳግመኛም እግዚአብሔር በራማ ያሉትን መላእክት በ30 ነገድ በ3 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ‹‹አርባብ›› ይባላሉ፡፡ የሥላሴ እልፍኝ አስከልካዮች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔርን መንበር በክንፎቻቸው ይሸፍናሉ፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ሁለተኞቹ በራማ ከተማ ያሉት ‹‹መናብርት›› ይባላሉ፡፡ ለእግዚአብሔርን እጅግ ቅርብ የሆኑ ናቸው፡፡ የመብረቅ ጋሻቸውን የእሳት ጦራቸውን ይዘው የሥላሴ ጋሻ ጃግሬዎች ሆነው በተጠንቀቅ ይቆማሉ፡፡ የሰውን ችግር ለእግዚአብሔር ያቀርባሉ፡፡ መዝ. 88፡6፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ሦስተኞቹ በራማ ከተማ ያሉት ‹‹ሥልጣናት›› ይባላሉ፡፡ መላውን ፍጥረት ለመጠበቅ ሥልጣን የተሰጣቸውና የምጽአት ዕለት አዋጅ ነጋሪዎች ናቸው፡፡ ዳን. 12፡1፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሱርያል ነው፡፡

ዳግመኛም እግዚአብሔር በኤረር ያሉትን መላእክት በ30 ነገድ በ3 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ‹‹መኳንንት›› ይባላሉ፡፡ የስላሴ የእሳት ባለ ቀስት ናቸው፡፡ የሰው ልጅ ልዩ ጠባቂዎች ናቸው፤ በተለይ በአደጋ ጊዜ ሎጥን እንዳዳኑት ፈጥነው ይደርሳሉ፡፡ በዕለተ ምጽዓት የሰውን ሁሉ ዐፅም ሰብስበው ለትንሣኤ ዘጉባኤ ያበቃሉ፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሰዳካኤል ነው፡፡ ሁለተኛዎቹ ‹‹ሊቃናት›› ይላሉ፡፡ የሥላሴ የእሳት ፈረሶች ናቸው፡፡ በእሳት ፈረስ ይመላለሳሉ፡፡ እነዚህም 24ቱ ካህናተ ሰማይ ሲሆኑ አለቃቸው ቅዱስ ሰላታኤል ነው፡፡ በኤረር ከተማ የሰፈሩት ሦስተኛዎቹ ‹‹መላእክት›› ይባላሉ፡፡ ፍጥረትን ሁሉ የሚጠብቁ ናቸው፡፡ አለቃቸው ቅዱስ አናንኤል ነው፡፡ በእነዚህ የማይጠበቅ ፍጥረት የለም፡፡ ከአዝርእት ጀምሮ ሁሉን ይጠብቃሉ፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ 7 መላእክትን አየሁ›› (ራዕ. 8፡2) እንዳለ ሊቃነ መላእክት በቁጥር 7 ናቸው፡፡ እነርሱም፡- ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱስ ሩፋኤል፣ ቅዱስ ራጉኤል፣ ቅዱስ ዑራኤል፣ ቅዱስ ፋኑኤል እና ቅዱስ አፍኒን ናቸው፡፡ ‹‹ዑራኤል›› የሚለው ስም ‹ዑር› እና ‹ኤል› ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው፡፡ ‹‹ዑራኤል›› ማለት ትርጉሙ ‹‹የብርሃን ጌታ፣ የአምላክ ብርሃን›› ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው፡፡ በመሆኑም መጽሐፈ ሄኖክ እንደሚገልጸው መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል፡፡ ምሥጢረ ሰማይንና ሰማያዊውን ዕውቀት ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራው ይኸው ገናና መልአክ ነው፡፡ መጽሐፈ ሄኖክ 28፡13፡፡

መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨው ይኸው ገናና መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡

ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ዕውቀት ተሠውሮበት ለነበረው ለኢትዮጵያዊው ሊቅ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም በእመቤታችን ትእዛዝ ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ‹‹ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ፡፡›› መጽሐፈ ዕዝራ 2፡1፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር የሕይወትና የይቅርታ ዝናም በምድራችን ላይ ያዘንብ ዘንድ እንዲሁም የእርሻችንን አዝመራ በዝናም አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ ለምግብነት እንዲበቃ ከፈጣሪ ዘንድ ምሕረትን የሚለምን መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡

ሊቁ አባ ጊዮርጊስም በመልአኩ አማላጂነት እጅግ ብዙ ድርሰቶችን የደረሱት መልአኩ ጽዋ ሕይወትን ካጠጣቸው በኋላ ነው፡፡ በመጀመሪያም አባ ጊዮርጊስ የተወለዱት በቅዱስ ዑራኤል አብሳሪነት ነው፡፡ በቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ የተመሠረቱ አብዛኞቹ ቅዱሳት ገዳማት በቅዱስ ዑራኤል መሪነት ነው፡፡ ድርሳኑ ላይ የማይጠቅሳቸው የሀገራችን የከበሩ ቅዱሳት ገዳማትና ቅዱሳን ነገሥታት የሉም፡፡

የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክን ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ስትሰደድ መንገድ እየመራ ወደ ግብጽ እና ወደ አገራችንን ኢትዮጵያ ያመጣቸው ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ እመቤታችንን ከተወደደ ልጇ ጋር በደመና ጭኖ መላ ኢትዮጵያን ካስጎበኛት በኋላ ቅድስት አገራችንን ለእመቤታችን የዓሥራት አገር እንድትሆን ያደረገው መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡

መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል በዓመት 3 ዓበይት በዓላት አሉት፡፡ ጥር 22 በዓለ ሲመቱ ነው፡፡ መጋቢት 27 የጌታችንን ክቡር የሆነ ወርቀ ደሙን ለዓለም የረጨበት ነው፡፡ ሐምሌ 22 ቀን ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የዕውቀትን ጽዋ ያጠጣበት ዕለት ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_እንጦንስ_ርዕሰ_መነኮሳት

በዚችህ ቀን በግብፅ አገር ከአቅማን ከተማ የከበረና የገነነ የመነኰሳት ሁሉ አባት በገዳም ለሚኖር እንደ ኮከብ የሚያበራላቸው አባት እንጦንዮስ አረፈ።
#ጥር_23

#ሐዋርያው_ቅዱስ_ጢሞቴዎስ

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ ሦስት በዚች ዕለት አሕዛብን ለሚያስተምር ለከበረ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ የሆነ የከበረ ሐዋርያ ጢሞቴዎስ በሰማዕትነት ሞተ። የዚህም ቅዱስ ልደቱና እድገቱ ልስጥራን ከሚባል አገር ነው አባቱም ከዋክብትን የሚያመልክ ዮናናዊ ነው እናቱ ግን በኦሪት ሕግ ጥላ ሥር ያለች ናት።

የከበረ ሐዋርያ ጳውሎስም በልስጥራን ሀገር በሰበከ ጊዜ ይህ ጢሞቴዎስ ስብከቱንና ትምህርቱን ሰማ እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያደርጋቸውን ድንቆች ተአምራቶችን አይቶ እሊህም ተአምራቶች አስተዋዮችና ጥበበኞች የሚደነግጡባቸው ናቸው ስለዚህም ወደ ሐዋርያ ጳውሎስ ሒዶ በእርሱ ትምህርት በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቆ የሐዋርያ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ ሆነ ወደ ብዙ አገሮችም ተከትሎት በመሔድ ከእርሱ ጋር ደከመ ታላቅ መከራና ብዙ ኀዘንም ደርሶበታል ሐዋርያው ጳውሎስም በኤፌሶን ውስጥ በአንዲት አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾመው።

በዚያንም ጊዜ ወደርሷ ገብቶ ለሰዎቿ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከ ብዙዎችንም ወደ ቀናች ሃይማኖት መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው ከዚህም በኋላ በዙሪያዋ ወዳሉ ብዙዎች አገሮች በርቀትም ለሚገኙ አገሮችም የከበረ ወንጌልን ሰበከላቸው።

የከበረ ሐዋርያ ጳውሎስም ሁለት መጻሕፍቶችን ጽፎ ወደርሱ ልኳል እርሳቸውም ሕዝቡን የሚያስተምርባቸው ራሱም ከቢጽ ሐሳውያን የሚጠበቅባቸው ቅስና ወይም ዲቁና ሊሾም የሚገባውንና የማይገባውን የሚለይበት ክህነት በማይገባው እጁን እንዳይጭን የሚያስጠነቅቁ ናቸው ጢሞቴዎስን ደግሞ ለርሱ ተወዳጅ ልጁ አድርጎ ይጠራዋል መልእክቶቹንም በእርሱ እጅ ወደ አገሮች ልኳል።

በላያቸው የተሾመባቸውን የክርስቶስን መንጋዎች ፈጽሞ በጠበቀ ጊዜ በትምህርቶቹ በተግሣጾቹና በድርሰቶቹ ልቡናቸውን ብሩህ አደረገ አይሁድንና ዮናናውያንን ይገሥጻቸውና ይዘልፋቸው ነበር እነርሱም ቀንተውበት ሁሉም በጠላትነት ተነሡበት ተሰብስበውም ገደሉት ምእመናንም ሥጋውን አንሥተው ቀበሩት ጻድቅ ቈስጠንጢኖስም እስከ ነገሠ በዚያው ኖረ እርሱም ስለ ሥጋው አስቦ ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ በጥር ወር በሃያ ሰባት ቀን አፈለሰው በዚያችም ቀን በዓል አደረገለት።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሱ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
#ጥር_24

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ አራት በዚህች ዕለት #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት በጸሎት ብዛት አንዲቱ የእግራቸው አገዳ የተሰበረበት (ስብረተ አፅማቸው) መታሰቢያ ነው፣ የከበረች ተጋዳይ #ግብጻዊት_ቅድስት_ማርያ አረፈች፣ የሸዋው #እጨጌ_መርሐ_ክርስቶስ ዕረፍታቸው ነው፡።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት

ጥር ሃያ አራት በዚህች ዕለት ''ሐዲስ ሐዋርያ'' ብሎ የሾማቸው የኢትዮጵያ ብርሃኗ የሆኑ የደብረ ሊባኖሱ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በጸሎት ብዛት አንዲቱ የእግራቸው አገዳ የተሰበረበትን (ስብረተ አፅማቸው) መታሰቢያ ታከብራለች።

እግዚአብሔር አምላካችን ለኢትዮጵያ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ የመረጣቸው ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ማለትም ‹‹አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነውታል፡፡ ወላጆቻቸውም ስማቸውን ፍሥሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ይኸውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ የወላጆቻቸው የቀድሞ ስማቸው ዘርዐ ዮሐንስና ሣራ ይባል ነበር፡፡

ቅዱሳን አባቶቻችን እነ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና እነ አቡነ ዜና ማርቆስ ሌሎቹም እነ አቡነ ሳሙኤል ዘወገግ፣ አቡነ ሕፃን ሞዐ፣ አቡነ አኖሪዮስ(ትልቁ)፣ አቡነ ገላውዲዮስ፣ አቡነ ማትያስ ዘፈጠጋርና አቡነ ቀውስጦስ ዘመሐግል የትውልዳቸው መሠረት ኢያሱ ለሌዋውያን ክፍል ትሆን ዘንድ ከለያት ከኢየሩሳሌም ነው፡፡ ስማቸውን የጠቀስኳቸው እነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን የወንድማማቾች ልጆች ሲሆኑ ከአዳም ጀምሮ 61ኛ ትውልድ ናቸው፡፡ ይኸውም እንዴት ነው ቢሉ ትውልዱ ከአዳም ጀምሮ በካህኑ አሮን በኩል የሆነውና የሌዋዊያን ሊቀ ካህን የነበረው የሳዶቅ ልጅ አዛርያስ በንጉሥ ሰሎሞን ዘመን ከታቦተ ጽዮንና ከብዙ ሌዋዊያን ካህናት ጋር ሊቀ ካህን ሆኖ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ አክሱም ተቀምጦ ኖረ፡፡ የኦሪትንም ሕግ እየዞረ ለኢትዮጵያ ሰዎች አስተማረ፡፡ ትውልዱም በአብርሃ ወአጽብሓና በአባ ሰላማ ዘመን እስከነበረው እንበረም የሚባለው ጻድቅ ድረስ ደረሰ፡፡ የእንበረምም ትውልድ ደገኛው ሕይወት ብነ በጽዮን ድረስ ደረሰ፡፡ ሕይወት ብነ በጽዮንም የደማስቆ ምድር ከሚሏት ከወለቃ ሀገር የመኮንን ልጅ የሆነችውን ወለተ ሳውልን አግብቶ አበይድላን ወለደ፡፡ አበ ይድላም በንጉሡ ድልዓዥን ዘመነ መንግሥት ለ150 ካህናት አለቃ ሆኖ በወለቃ ሀገር የክርስቶስን የወንጌል ሕግ እያስተማረ ብዙዎችን አጠመቀ፡፡ እስከ ሸዋ ምድር ድረስ እያስተማረ መጥቶ በሸዋ ምድር ተቀመጠ፡፡ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳነጸ፡፡ እጅግ አስደናቂ ተአምራትንም ያደርግ ነበር፡፡ ‹‹በሸዋ ጽላልሽ ተቀምጦ ሲያስተምርም በአንዲት ቀን እስከ ሁለት መቶ ሺህ ሕዝብ ያጠምቅ ነበር›› በማለት ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ይመሰክርለታል፡፡

አበይድላ በመጨረሻ በፈቃደ እግዚአብሔር ከሸዋ ጽላልሽ ምድረ ዞረሬ ሚስት አግቶ ሀበነ እግዚእን ወለደ፤ ሀበነ እግዚእም በኩረ ጽዮንን ወለደ፤ በኩረ ጽዮንም ሕዝበ ቀድስን ወለደ፤ እርሱም ነገደ እግዚእ የተባለ ነው፡፡ ሕዝበ ቀድስም ብርሃነ መስቀልን ወለደ፤ እርሱም ዐቃቢነ እግዚእ የተባለ ነው፡፡ ብርሃነ መስቀልም ሕይወት ብነን ወለደ፤ እርሱም ሴትን ወለደ፡፡ ሴትም ወረደ ምሕረትን ወለደ፡፡ ወረደ ምሕረትም ዘካርያስን ወለደ፡፡ ዘካርያስም የእነ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የሆኑ 6 ወንድማማች ልጆችን ወለደ፡፡ እነርሱም እንድርያስ፣ አርከሌድስ፣ ዘርዐ አብርሃም፣ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብ፣ ቀሲስ ዮሐንስና ቀሲስ ዮናስ ናቸው፡፡ እንድርያስም ሳሙኤል ዘወገግን ወለደ፤ አርከሌድስም ሕፃን ሞዐን ወለደ፤ ዘርዐ አብርሃምም ታላቁን አኖርዮስን ወለደ፤ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብም ተክለ ሃይማኖትን ወለደ፤ ቀሲስ ዮሐንስም ዜና ማርቆስን ወለደ፣ ቀሲስ ዮናስ ደግሞ የፈጠጋሩን ማትያስንና ገላውዲዮስን ወለዳቸው፡፡ ገላውዲዮስም የመሐግሉ ቀውስጦስን ወለደ፡፡ እነዚህ ደጋግ ቅዱሳን በእናታቸውም በኩል እንዲሁ በዝምድና የተሳሰሩ ናቸው:: ማቴዎስ የተባለው ደገኛ ክርስቲያን የሸዋ ገዥ የነበረ ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ መድኃኒነ እግዚእንና ሦስት ሴቶች ልጆችን ወለደ፡፡ ሶስቱ ሴቶች ልጆችም እምነ ጽዮን፣ ትቤ ጽዮንና ክርስቶስ ዘመዳ ይባላሉ፡፡ ሦስቱ እኅትማማቾችም ደጋጎቹን አባቶቻችንን ወለዱልን፡፡ እምነ ጽዮን የእነ ዜና ማርቆስን እናት ማርያም ዘመዳንና ወለደች፡፡ ትቤ ጽዮንም ሕፃን ሞዐን ወለደች፡፡ ክርስቶስ ዘመዳ ደግሞ ታላቁን አኖሬዎስን ወለደች፡፡ የፈጠጋሩ ገዥ መድኃኒነ እግዚእ ደግሞ የተክለ ሃይማኖትን እናት እግዚእ ኀረያን ወይም በሌላ ስሟ ሣራን ወለደ፡፡

አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከልጅነታቸው ጀምሮ በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በ15 እና በ22 ዓመታቸው ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ከአቡነ ቄርሎስ (ጌርሎስ) ዲቁናንና ቅስናን ተቀብለዋል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ያገለግሉ እንደነበር በዚህ ይታወቀል፡፡

ከዕለታት በአንዱ ቀን አባታችን ከጓደኞቻቸው ጋር ለአደን ወደ ዱር ሄደው ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ታያቸው፡፡ ቅዱስ አባታችንም ‹‹እንደዚህ ባለ ገናንነት የማይህ ጌታዬ ማነህ?›› ባሉት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ‹‹ዘወትር የምጠብቅህ ካንተ የማልለይ እናትህንና አባትህንም ስላንተ ከውኃ ስጥመትና ከምርኮ ያዳንኳቸው እኔ ሚካኤል ነኝ፡፡ ከእንግዲህ አውሬ አዳኝ አትሁን፤ ሰውን ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ ሰውን በትምህርት የምታድን ሁን እንጂ፡፡ እነሆ እግዚአብሔር ጽኑዕ ሥልጣን ሰጥቶሃልና፤ ሙት ታስነሣለህ፤ ድውያንን ትፈውሳለህ፤ አጋንንትም አንተን በመፍራት ይሸሻሉ፡፡ ስምህ ፍሥሐ ጽዮን አይሁን፤ ተክለ ሃይማኖት ይሁን እንጂ፡፡ ትርጓሜውም ተክለ አብ፥ ተክለ ወልድ፥ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው›› አላቸው፡፡

ቅዱስ ሚካኤል ይህን ሲነግራቸው ጌታችን በሥጋ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር እንደነበር ሆኖ መልከ መልካም ጎልማሳ መስሎ ታያቸው፡፡ ጌታችንም ‹‹ወዳጄ እንዴት ሰነበትክ? ቸር አለህን?›› አላቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ‹‹ጌታዬ ሆይ አንተ ማነህ?›› ብለው ሲጠይቁት ጌታችንም ‹‹እኔ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ነኝ፤ በናትህ ማኅፀን ፈጥሬህ ያከበርኩህ እኔ ነኝ፡፡ በተወለድክ በሦስተኛው ቀን አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብለህ ታመሰግነኝ ዘንድ የምስጋና ሀብት ያሳደርኩብህ እኔ ነኝ፡፡ በርሃብ ዘመን በቤት የሚያሻው ምግብ ሁሉ ቅቤው፣ የስንዴው ዱቄት በእናት በአባትህ ቤት ይመላ ዘንድ በእጅህ ሀብተ በረከት ያሳደርኩብህ እኔ ነኝ፡፡ ያንን ሰው አንተን በተጣላ ጊዜ በነፋስ አውታር የሰቀለኩት በመዓት ጨንገር የገረፍኩት እኔ ነኝ፡፡ ውኃ ጠምቶህ በለመንከኝ ጊዜ ከደረቅ መሬት የጣፈጠ ውኃ ያመነጨሁልህ እኔ ነኝ፡፡ ከልጅነትህ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ብዙ ተአምራት እያደረግሁ በአንተ እጅ የታመሙትን ያዳንኳቸው እኔ ነኝ፡፡ ወደፊትም አደርግልሃለሁ›› አላቸው፡፡ ይህንን ብሎ በእጆቹ ባረካቸውና ‹‹ንሣእ መንፈስ
#ጥር_25

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ አምስት በዚህች ዕለት ሰማዕቱ #ቅዱስ_መርቆሬዎስ በሥዕሉ ላይ አድሮ ቅዱሳን ባስልዮስንና ጎርጎርዮስን የረዳበት ዕለት ነው፡፡ በገድል የተጸመደ የከበረ #ቅዱስ_ጴጥሮስ አረፈ፣ የከበረ #ቅዱስ_ስብስትያኖስ ምስክር ሁኖ ሞተ፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_መርቆሬዎስ

ጥር ሃያ አምስት በዚህች ዕለት ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ በሥዕሉ ላይ አድሮ ቅዱሳን የሆኑ ባስልዮስንና ጎርጎርዮስን በመርዳት ከሃዲውን ንጉሥ ዑልያኖስን የገደለው በዚሁ ዕለት ነው፡፡

መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው፡፡ ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ወላጆቹ አስሊጥ ከምትባል ሀገር ቢሆኑም እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው፡፡ አያቱና አባቱ ሥራቸው አውሬ ማደን ስለነበር አንድ ቀን እንደልማዳቸው አውሬ ሲያድኑ ከገጸ ከለባት ወገን የሆኑ ሁለት ወንዶች አግኝተዋቸው የመርቆሬዎስን አያት በሉት፡፡ አባቱንም ሊበሉት ሲሉ የታዘዘ መልአክ ከለከላቸው፡፡ ዙሪያቸውንም በእሳት አጥሮ ከበባቸው፡፡ እነርሱም በተቸገሩ ጊዜ ለመርቆሬዎስ አባት ሰገዱለት፡፡ በዚያን ጊዜም እግዚአብሔር ፍጥረታቸውን ወደገራምነት ለወጠውና እንደበጎች የዋሆች ሆነው አብረውት ወደ መንደር ገቡ፡፡

ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ ተወለደና ስሙ ፒሉፓዴር ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸውም በእርሱ ዘንድ ብዙ ዘመናት ኖሩ፡፡ ከዚህም በኋላ ክርስቲያኖች ሆኑ፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም ወላጆች አስቀድመው አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትን በጸጋ ተቀበሉ፡፡ አባቱን ኖህ እናቱንም ታቦት ብለው ሰየሟቸው፡፡ ቀድሞ ፒሉፓዴር የነበረውም ስሙ ተለውጦ መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸው ግን መልአኩ በተገለጠላቸው ጊዜ እንደነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባትና የውሻ መልክ ያላቸውን ዜናቸውን ሲሰማ ወታደሮቹን ልኮ በፊቱ አቆማቸው፡፡ እግዚአብሔርም የቀድሞ ፍጥረታቸውን መልሶላቸው አራዊት አደረጋቸውና ንጉሡን እጅግ አስፈሩት፡፡ ንጉሡም የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት የአራዊት ተፈጥሮአቸውን ያርቅለት ዘንድ ለመነው፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም አባት በለመነ ጊዜ ተፈጥሮአቸውን መልሶላቸው ገራሞች ሆኑ፡፡

ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ገዥና የሠራዊቱ አለቃ አድርጎ ሾመው፡፡ የውሻ ፊት ያላቸውም አብረው ያገለግሉት ስለነበር ሁሉም ይፈራው ነበር፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ወደ ጦርነት ከላከው በኋላ ሳይመለስ ስለቀረ ሚስቱን ሊያገባት አሰበ፡፡ የመርቆሬዎስ አባትም የመርዶሳውያን አገሮች ሁሉ ገዢ በነበረው ንጉሥ ተይዞ ቢማረክም ገዥው ክርስቲያን መሆኑን አይቶ አከበረው፡፡ ቆይቶም በሀገሩ ላይ ሾመው፡፡ ሚስቱም ጠፍታ ከሀገሯ ወጥታ ሄዳ ስለነበር ከባሏ ተገናኝተው በዚያው መኖር ጀመሩ፡፡ መርቆሬዎስም አባቱና እናቱ ከሞቱ በኋላ ንጉሡ በአባቱ ፈንታ በመርዶሳውያን አገር ላይ ሾመው፡፡

መርቆሬዎስ መኰንንነት በተሾመም ጊዜ ገጸ ከለባቱ አብሮት ነበር፡፡ ለመዋጋትም በወጣ ጊዜ የቀድሞው የአራዊት የሆነ ተፈጥሮውን እግዚአብሔር ይመልስለት ስለነበር ማንም አይቋቋመውም ነበር፡፡ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠውና ዜናው በሁሉም ሀገሮች ተሰማ፡፡ በሮሜ ሀገር ጣዖትን የሚያመልከው ዳኬዎስ የተባለውም ንጉሥ የበርበር ሰዎች ጋር ጦርነት ሊገጥም በወጣ ጊዜ እጅግ ሲበዙበት ፈራ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በጦሩ መሀል የተሳለ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔርን መልአክ ስላየ ንጉሡን እግዚአብሔር ያጠፋቸዋልና አትፍራ›› አለው፡፡ መልአኩም ሰይፉን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰጠውና ‹‹ጦርነቱን ድል ባደረግህ ጊዜ እግዚአብሔርን አስበው›› አለው፡፡

ጦርነቱን ድል አድርጎ ሲጨርስም መልአኩ ድጋሚ ተገልጦለት ‹‹ለምን የፈጣሪህን ስም መጥራት እረሳህ?›› አለው፡፡ ከጦርነቱም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን አደረገ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በዚያ ስላልተገኘ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረጉ እንዳልተባበረ ንጉሡ ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስመጣው፡፡ ንጉሡም ‹‹ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም?›› ባለው ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ ትጥቁንና ልብሱን አውልቆ ከወረወረለት በኋላ ‹‹ክብር ይግባውና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ አልክደውም፣ ለረከሱ ጣዖቶችህም አልሰግድም›› አለው፡፡ ንጉሡም ተናዶ ልዩ ልዩ በሆኑ ሥቃዮችም እጅግ አሠቃየው፡፡

ንጉሡም ስለ መርቆሬዎስ ብለው የአገሩ ሰዎች እንዳይነሱበት ፈርቶ በብረት ችንካር ቸንክሮ የቀጵዶቅያና የእስያ ክፍል ወደሆነች ወደ ቂሳርያ ከደብዳቤ ጋር ላከው፡፡ በዚያም እጅግ ካሠቃዩት በኋላ ንጉሡ ዳኬዎስ እንዳዘዘ ኅዳር 25 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ፡፡ የሕይወትንም አክሊል ተቀዳጀ፡፡ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነጹለት፡፡ እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም አደረገ፡፡

ከብዙ ተአምራቱም አንዱ የቂሳርያውን ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስን እረድቶ ከሃዲውን ዑልያኖስን የገደለበት ነው፡፡ ዑልያኖስ ነግሦ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክዶ ጣዖታትን ማምለክና ክርስቲያኖችን ማሠቃየት ጀመረ፡፡ የቂሳርያው ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስም አስተምሮ ሊመልሰው ወደ ንጉሡ ቢመጣ ክብር ይግባውና ዑልያኖስ ጌታችንን ሰድቦ ባስልዮስንም አሰረው፡፡ ባስልዮስም በእሥር ቤት ሳለ በቅዱስ መርቆሬዎስ ሥዕል ፊት ጸለየ፡፡ ሥዕሉም ወዲያው ተሰወረው፡፡ ያንጊዜም ወደ ከሃዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ዘንድ ሄዶ በጦር ወግቶ ገደለውና ወዲያው ወደ ቦታው ተመለሰ፡፡ ከጦሩም አንገት ደም ይንጠፋጠፍ ነበር፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ከሃዲውን ንጉሥ እንደገደለው ዐውቆ ‹‹የክርስቶስ ምስክር ጌታዬ ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን?›› አለው፡፡ ሥዕሉም ያን ጊዜ አዎን እንደሚል ራሱን ዘንበል አደረገ፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ደስ ብሎት እግዚአብሔርን አመሰገነ፡፡

ሌላው ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በተአምሩ ከእስልምና እምነት መልሶ ክርስቲያን ያደረገው አንድ እስላም ሰው አለ፡፡ ይኸውም የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያኑ በተሠራችበት በምስር አገር የሚኖር ከመሳፍንት ወገን የሆነ ወጣት ነበረ፡፡ ከብዙ ሰዎችም ጋር ሆኖ ወደ መሐመድ መቃብር ለመሄድ እንዳሰበ ለአባቱ ሲነግረው ስንቅ ሰንቀው በሰላም ወደ መካ መዲና ሸኙት፡፡

መካ ደርሰውም ሥራቸውም ፈጽመው ወደቤታቸው እየተመለሱ ሰባት ቀን ተጓዙ፡፡ በሌሊትም ሲጓዙ ስለ ሥጋዊ ግዳጁ ያ እስላም ወጣት ከግመል ላይ ወርዶ ለመጸዳዳት ዘወር አለ፡፡ እነርሱም አብሯቸው የሚጓ መስላቸው ስለነበር ባልንጀሮቹም በበረሃው ውስጥ ትተውት ሄዱ፡፡ እርሱም ወዴት እንደሚሄድ ስላላወቀ አራዊትም እንዳይበሉት ፈርቶ እጅግ ደነገጠ፡፡

በዚያም ጊዜ በምስር አገር በአባቱ ቤት አቅራቢያ ያለች የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስን ቤተ ክርስቲያን አስታውሶ በልቡ ቅዱስ መርቆሬዎስን እንዲያድነው በመለመን ተሳለ፡፡ ወዲያውም ቅዱስ መርቆሬዎስ በፈረሱ ተቀምጦ ወደ እርሱ መጣና ‹‹ከወዴት ነህ? ከዚህ በረሃ ውስጥስ እንዴት ጠፋህ?›› አለው፡፡ ወጣቱ እስላምም የሆነውን ነገረው፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም ‹‹ና በኋላዬ በፈረሱ ላይ ተፈናጠጥ›› አለውና በአየር ላይ እየበረረ በምስር አገር ወዳለች የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ዐይን ጥቅሻ አደረሰውና እንደተዘጋች በውስጧ አስገባውና ከእርሱ ተሰወረ፡፡ ይህም ወጣት በኋላ አምኖ ተጠምቆ ብዙ ሰማዕትነት ተቀብሏል፡፡ ገዳምም ገብቶ ብዙ
#ጥር_26

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ ስድስት በዚህች ቀን #ቅድስት_አንስጣስያ አረፈች፣ የከበሩ #አረጋውያን_መነኰሳት ከንጉሥ መልእክተኛ ከልጁም ጋር በሰማዕትነት አረፉ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_አንስጣስያ

ጥር ሃያ ስድስት በዚህች ቀን ከቍስጥንጥንያ ቤተ መንግሥት ታላላቆች የአንዱ ልጅ የሆነች ቅድስት አንስጣስያ አረፈች። እርሷም በላሕይዋ በደም ግባቷ እጅግ ያማረች ናት ንጉሥ ብስጥያኖስም ሊአገባት ፈለገ እርሷ ግን ይህን በልቧ አልወደደችም የንጉሡም ሚስቱ በሕይወት ነበረች ንጉሡ እንደሚሻትም ለንግሥት ሚስቱ አስረዳቻት በዚያንም ጊዜ ንግሥቲቱ ወደ ግብጽ በመርከብ አሳፍራ በሥውር ሸኘቻት ከእስክንድርያም ከተማ ውጭ ገዳም አሠራችላት በዚያም ኖረች ያም ገዳም በስሟ ተጠራ።

የከበረች እንስጣስያም በግብጽ አገር እንዳለች ንጉሥ በአወቀ ጊዜ ፈልገው ወደርሱ ያመጧት ዘንድ መልእክተኞችን ላከ ይህንንም ነገር ተረድታ ተነሣች የወንዶችንም ልብስ ለብሳ መስፍንን መሰለች ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔዳ ወደ አበ ምኔቱ ወደ አባ ዳንኤል ገባች ምሥጢሯን ሁሉ ገለጠችለት ።

እርሱም ወስዶ በዋሻ ውስጥ ለብቻዋ አኖራት እርሷም ሴት እንደሆነች ማንም አላወቀም በየሳምንቱም በእንስራ ውኃ ቀድቶ ከዚያ ዋሻ ደጃፍ እንዲያኖር አንዱን ደግ አረጋዊ አባ ዳንኤል አዘዘው ያም ሽማግሌ አያውቅም ይችም ቅድስት አንስጣስያ በጸሎት በጾምና በመስገድ በመትጋትም እየተጋደለች ሃያ ስምንት ዓመት ኖረች ።

ውኃ ሲቀዳላት የነበረ ያ ሽማግሌ በአረፈ ጊዜ አባ ዳንኤልም ያ ሽማግሌ ሲሠራ እንደ ነበረ ይሠራ ዘንድ ረዳቱን አዘዘው ቅድስት አንስጣስያም ሀሳቧን በገል ላይ እየጻፈች በበዓቷ ደጃፍ ታኖረው ነበር ረድኡም ወደ መምህሩ ወደ አባ ዳንኤል ይወስደዋል። የምትጽፈውንም ምን እንደሆነ አያውቅም ።

በአንዲት ዕለትም የጻፈችበትን ገል አመጣ አባ ዳንኤልም በአነበባት ጊዜ አለቀሰ ረድኡንም ልጄ ሆይ ተነሥ የዚያን ቅዱስ ሰው ሥጋ ሒደን እንቅበር እርሱ ከዚህ ዓለም ይለያልና አለው ። በሔዱም ጊዜ ወደ በዓቷ ገብተው ከእርሷ ተባረኩ እርሷም አባ ዳንኤልን አባቴ ሆይ ስለ እግዚአብሔር ብለህ በላዬ ካለው በቀር በምንም ልብስ እንዳትገንዘኝ አለችው ከዚህም በኋላ የከበረች አንስጣስያ ተነሥታ ጸለየች እኔ በእግዚአብሔር ዘንድ አደራ አስጠበቅኋችሁ አለችና በምድር ላይ ተቀምጣ አረፈች በላይዋም አለቀሱ ሊቀብሩዋትም አስበው ረድኡ ይገንዛት ዘንድ ሲቀርብ እንደ በለስ ቅጠሎች ደርቀው ጡቶቿን ተመለከተ። ከተጋድሎ ብዛትም የተነሣ እንዲህ ሁኗልና አባ ዳንኤልም አይቶ በማድነቅ ዝም አለ ።

ከቀበርዋትም በኋላ ወደ በዓታቸው ተመለሱ ረድኡም ወደ አባ ዳንኤል ቀርቦ ሰገደለትና እንዲህ ሲል ለመነው ስለ እግዚአብሔር ብለህ የዚችን ቅድስት ዜናዋን ንገረኝ ሴት እንደሆነች አይቻለሁና።

አባ ዳንኤልም የገድሏን ዜና ሊነግረው ጀመረ እንዲህም አለው እርሷ ከቍስጥንጥንያ አገር ከመንግሥት ታላላቅ ወገኖች ውስጥ የሆነች ስትሆን ሰውነቷን ለክርስቶስ ሰጥታ የዚህን የኃላፊውን ዓለም ክብር ሁሉ ተወች። ሰይጣንን ከተዋጋችበት ከዚህ ከታላቅ ተጋድሎዋ ለእኛ ለወንዶች መመከሪያ ሊሆነን ይገባል ከእርሷም የሴቶችን ደካማነት አርቃ የኃይለኞች ወንዶችን ብርታት ገንዘብ እስከማድረግ ደርሳ እግዚአብሔርን አገለገለችው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

፵፱ አረጋውያን ሰማዕታት

በዚህችም ቀን የጻድቅ አርቃዴዎስ ልጅ በሆነ በጻድቁ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግሥት አርባ ዘጠኝ የሆኑ የከበሩ አረጋውያን መነኰሳት ከንጉሥ መልእክተኛ ከልጁም ጋር በሰማዕትነት አረፉ።

የሰማዕትነታቸውም ምክንያት ቴዎዶስዮስ ልጅ አልነበረውም በአስቄጥስ ገዳም ወደ ሚኖሩ አረጋውያን መነኰሳት ልጅን ይሰጠው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንዲማልዱለት እየለመናቸው መልእክትን ላከ ከውስጣቸውም ስሙ ቢስዱራ የሚባል አንድ ታላቅ አረጋዊ አለ እርሱም ወደ ንጉሥ እንዲህ ብሎ ጻፈ ከአንተ በኋላ ከሚነሡ መና*ፍቃን ጋር አንድ እንዳይሆን ልጅን ይስጥህ ዘንድ እግዚአብሔር አልወደደም። መልእክቱን በአነበበ ጊዜ ንጉሡ ደስ ብሎት እግዚአብሔርን አመሰገነው ሃሳቡንም አሳረፈ።

ዳግመኛም ግብዞች ሰዎች ሌላ ሚስት አግብቶ ከእርሱ በኋላ በዙፋኑ የሚቀመጥ ልጅን ይወልድ ዘንድ መከሩት እርሱም የትሩፋታቸው ዜና በዓለም ዳርቻ ሁሉ ደርሷልና በአስቄጥስ ገዳም ከሚኖሩ ከቅዱሳን አረጋውያን ትእዛዝ በቀር ምንም ምን አላደርግም ሲል መለሰላቸው።

ስለዚህም አረጋውያንን ይጠይቅ ዘንድ ንጉሥ መልእክተኛውን ዳግመኛ ላከ ለንጉሡም መልእክተኛ ልጅ ነበረው ልጁም በረከታቸውን ይቀበል ዘንድ ከእርሱ ጋር ወደ አረጋውያን እንዲወስደው አባቱን ለመነው መልእክተኛውም ከልጁ ጋር ወደ አረጋውያን በደረሰ ጊዜ የንጉሡን ደብዳቤ ሰጣቸው እነርሱም አነበቧት ያን ጊዜ ግን አባ ቢስዱራ ስለሞተ አልተገኘም አረጋውያንም የንጉሡን መልእክተኛ የአባ ቢስዱራ ሥጋ ወዳለበት ወሰዱትና አደረሱት ሥጋውንም አባታችን ሆይ እነሆ የንጉሥ መልእክት ወደ እኛ ደረሰ እኛም የምንመልስለትን አናውቅም አሉት። በዚያንም ጊዜ አረጋዊ አባ ቢስዱራ ተነሥቶ እግዚአብሔር ልጅን ሊሰጥህ አልፈቀደም አላልኩህምን አለ በሉት ለንጉሥ አሁንም ከዓላ*ውያን ጋር አንድ ሁኖ እንዳይረክስ ሌሎች ሴቶችንም ቢአገባ ልጅን አይሰጠውም ይህንንም ተናግሮ ተመልሶ ተኛ።

አረጋውያንም ይህን ቃል በክርታስ ጽፈው ለንጉሥ መልእክተኛ ሰጡት እርሱም ወደ አገሩ ሊመለስ በተነሣ ጊዜ እነሆ የበርበር አረ*ማውያን ደረሱ አባ ዮሐንስ የሚባል አረጋዊም ቁሞ ወገኖቹን እንዲህ አላቸው እነሆ የበርበር ሰዎች ይገ*ድሉን ዘንድ መጡ ምስክርነት የሚሻ ከእኔ ጋር ይቁም የሚፈራ ግን ወደ ግንብ ሒዶ ይሠወር አለ።

የሸሹም አሉ ከአባ ዮሐንስ ጋርም የቀሩ አርባ ዘጠኝ አረጋውያን መነኰሳት የንጉሥ መልእክተኛም ልጅ ከጎዳና ጉዞ ላይ ዘወር ሲል በአረጋውያን ሰማዕታት ራሶች አክሊላትን ሲያኖሩ መላእክትን አያቸው የዚያም ጎልማሳ ስሙ ድያስ ነው አባቱንም እነሆ በአረጋውያን ራሶች ላይ አክሊላትን ሲያኖር ረቂቃን መላእክትን አያለሁ አሁንም እንደርሳቸው አክሊልን ለመቀበል እኔ እሔዳለሁ አለው አባቱም ልጄ ሆይ እኔም ከአንተ ጋር እሔዳለሁ አለው።

በዚያችም ጊዜ አረጋውያን መነኰሳት ለአረ*ማውያን ተገለጡላቸው አረ*ማውያንም ገ*ደሏቸው የምስክርነት አክሊልንም ተቀበሉ። አረ*ማውያንም ከሔዱ በኋላ መነኰሳቱ ከተሠወሩበት ግምብ ወርደው የሰማዕታትን ሥጋቸውን ሰበሰቡ ገንዘውም በበዓት ውስጥ አኖሩዋቸው በእርሳቸውም ዘንድ ሌሊቱን ሁሉ የሚጸልዩና የሚዘምሩ ከእርሳቸውም የሚባረኩ ሆኑ የአባ ዮሐንስንም ሥጋ ሰዎች ሰርቀው ባታኑን ወደሚባል አገር ወሰዱት ከእርሳቸውም ዘንድ ጥቂት ቀኖች ኖረ ከዚህም በኋላ ቅዱሳኑ ወደቦታው መለሱት።

ሌሎችም ከሀገረ ፍዩም የጎልማሳውን ሥጋ ሰርቀው ወደ ፍዩም አገር ሲአደርሱት የእግዚአብሔር መልአክ ነጥቆ ወደ አባቱ ሥጋ መለሰው መነኰሳቱም ብዙ ጊዜ ፈተኑት የወጣቱን ሥጋ ከአባቱ ሥጋ የሚለዩት ሁነው ነበር። በጥዋትም በአንድነት ያገኙአቸዋል ከመነኰሳቱም አንዱ እንዲህ የሚለውን እስኪያይና እስኪሰማ ድረስ። "ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛ በሕይወተ ሥጋ ሳለን እርስበርሳችን አልተለያየንም በጌታችን ክርስቶስም ዘንድ አልተለያየንም እናንተ እርስ በርሳችን ለምን ትለያዩናላችሁ!" ከዚያችም ቀን ወዲህ የለያቸው የለም።
#ጥር_27

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ ሰባት በዚህች ቀን #የቅዱስ_ሱርያል ሊቀ መልአክ በዓል ነው፡፡ የያሬድ ልጅ #ቅደስ_ሄኖክ_ነቢይ የተሰወረበት ነው፣ የከበረ #ቅዱስ_ሰራብዮን በሰማዕትነት ሞተ፣ የከበረ ሐዋርያ #ቅዱስ_ጢሞቴዎስ የሥጋው ፍልሰት ሆነ፣ የከበረ #ቅዱስ_ቢፋሞን በሰማዕትነት ሞተ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ሱርያል_ሊቀ_መላእክት

ጥር ሃያ ሰባት በዚህች ቀን የሊቀ መልአክ ሱርያል በዓል ነው፡፡ እርሱም ከሊቃናት አንዱ ነው፡፡ ቅዱስ ሱርያል ክብሩ ብዙ ቢሆንም ብዙ ምዕመናን አያውቁትም:: የመላእክት መዓርግ ሲነገር ሚካኤል፣ ገብርኤል፣ ሩፋኤል ብሎ ቀጥሎ የሚመጣው ሱርያል ነው::

በሦስቱ ሰማያት ካሉት ዘጠኙ ዓለመ መላእክት የአንዱ (የሥልጣናት) መሪ (አለቃ) ነው:: መልአኩ እጅግ ርሕሩሕ እና ተራዳኢ ነውና አንዘንጋው:: ለኖኅ መርከብን ያሳራው: ከጥፋት ውኃም ያዳነው፣ ከነቢይ እዝራ ጋር የኖረ የተሠወረ ምሥጢርንም የገለጠለት ነው እና ስለ ሰው ልጆች ወደ እግዚአብሔር የሚለምን ነው ይህ ቅዱስ መልአክ ነው::

በገድለ ሰማዕታትም ላይ እንደተጠቀሰው የሰማዕታት ረዳትና አዳኝም ነው:: ቅዱስ ሱርያል በሌላ ስሙ "እሥራልዩ" ይባላል:: "የእሥራኤል ረዳት" እንደ ማለት፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ሄኖክ_ነቢይ

በዚህችም ዕለት የያሬድ ልጅ ሄኖክን የመላልኤል ልጅ የቃይናን ልጅ የኄኖስ ልጅ የሴት ልጅ የአዳም ልጅ ኄኖክን መላእክት ይዘው አሳረጉት ይኸውም በመባርቅትና በነፋሳት ላይ ተጭኖ በመብረር ወደ ሰማይ ወስደው ከረቂቃን መላእክት ጋር አኖሩት የእግዚአብሔርም ትእዛዝ ጸሐፊ ተባለ።

እንዲህም አለ ከማደሪያው ከሚወጣው ከቅዱሱና ከገናናው በጸናች ኃይሉ ከሠራዊቱ ጋር በሲና ተራራ ከሚገለጠው ጋር በመነጋገር ተመላለስኩ። ሁሉም ይፈሩ ነበር በውኃ ዳርም ሳለሁ የልመናቸውን መታሰቢያ ጻፍኩ እስከ አንጎላቸሁና ሕልም እንደሚያይ እስከምሆን ይችም በአርሞን ግራና ቀኝ ያለች አገር ናት።

በደብር ቅዱስ ለነበሩ ለኃጢአት ለሚተጉ ለሴት ልጆች ይዘልፋቸው ዘንድ ቃል እንደጠራውና እንዳሳየው ተናገረ። እንዲህ አለ በበረድ ደንጊያ ወደ ተሠራ ታላቅ ቤት ቀረብኩ በበረድ ደንጊያ የተሠራ የዚያ ቤት ግድግዳ እንደ ሳንቃ ልዝብ ነው ከዚህ ቤት የሚበልጥም ሌላ ቤት አየሁ ደጃፉም የተከፈተ ነው በእሳት ቅጽርም የተሠራ በክብር ከሁሉ የሚበልጥ ነው።

በውስጡም ከፍ ያለ የእግዚአብሔርን ዙፋን አየሁ መልኩም እንደ ውርጭ ነው አጎበሩም እንደሚያበራ ፀሐይ ነው ከዙፋኑም በታች የኪሩቤል ድምፅ ይሰማል። ዳግመኛም ወደ ሰባት ተራራዎች ደረስኩ ሦስቱ በምሥራቅ በኵል ሦስቱ በአዜብ በኵል ናቸው የመካከለኛው ግን ሰማይ ጠቀስ ነው የመላእክትም ጌታ በላዩ አለ።

ሌሎች አራት ገጾች ኪሩቤልን አየ ስለ ክርስቶስም እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ የዘመናት አለቃ ወደ ሆነው የሰው ልጅ ተጠራ ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ የነበረ ሆነ ሁለተኛም ለጻድቃን የጽድቅ በትር ለአሕዛብም ብርሃን ተስፋ ለሌላቸውም አለኝታ ይሆናል አለ።

በሰማይ ገጽ ስለሚመላለሱ ብርሃናት እንዲህ አለ አንዱም አንዱ በየወገናቸው በሠለጠኑበትና በተሠየሙበት ጸንተው ይኖራሉ ስለ ነፋሳትም መውጫዎች እንዲህ ብሎ ተናገረ ሦስቱ በሰማይ ገጽ ሦስቱ በምድር ገጽ ሦስቱ በቀኝ ሦስቱ በግራ ናቸው። ስለ አዳምም እንዲህ አለ እነሆ በሬ ከምድር ወጣ ፀዓዳም ሆነ ስለ ሔዋንም ደግሞ ሴት እምቦሳ ከርሱ ወጣች አለ።

ስለ ምኵራብም ያንን አሮጌ ቤት እስከሚአሳንሰው ድረስ አየሁ አለ ምሰሶዎቹንም ከውስጡ አወጣ። ሰለ ቤተክርስቲያንም ጌታ አዲስ የበጎች ቤት አምጥቶ እስቲሠራ ድረስ አየሁ ከቀድሞውም ቤት የበለጠ ነው በጎችም ሁሉ በውስጧ ይሠማራሉ አለ። ስለ ምእመናንም የእሊህም በጎች ፀጕራቸው ንጹሕ ነጭ ነው የተበተኑትም ከአራዊት ጋራ ይሠማራሉ ሁሉም በአንድነት ተሰብስበው ገራሞች ሆነዋልና።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ሰራብዮን_ሰማዕት

በዚህች ዕለት ከግብጽ ደቡብ ከታችኛዪቱ ምስር አውራጃ በብኑዲ ከምትባል መንደር የከበረ ሰራብዮን በሰማዕትነት ሞተ። ለዚህም ቅዱስ ብዙ የገንዘብ ጥሪት እንስሳትም አሉት አብዝቶ መመጽወትንም የሚወድ ነው ስደትም በሆነ ጊዜ የክርስቲያን ወገኖችን ፈልጎ ያሠቃይ ዘንድ መኰንኑ ኄሬኔዎስ በየሀገሩ እንደሚዞር ሰማ ለርሱም ስማቸው ቴዎድሮስና ሁለተኛውም በግ አርቢ ሰርማ የሚባሉ ወዳጆች ነበሩት እነርሱም ተከተሉት ይህም ቅዱስ መኰንኑን ሊገናኘው ከሀገሩ ወጣ መኰንኑንም በአገኘው ጊዜ በፊቱ ቁሞ ከወገኖቹ ጋር በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ መኰንኑም ሁሉንም አሠራቸው።

የሀገር ሰዎችም በሰሙ ጊዜ ሁሉም ተሰብሰቡ መኰንኑን ገድለው ቅዱስ ሰራብዮንን ከእጁ ሊወስዱ ሽተው የጦር መሣሪያ በመያዝ ለጦርነት የተሰለፉ ሠራዊት ሁነው ደረሱ ቅዱሱ ግን ከለከላቸው እንዲህም አላቸው እኔ በጌታዬ ክርስቶስ ስም ደሜን አፈስ ዘንድ በፈቃዴ የመጣሁ አይደለምን መኰንኑም በመርከብ ተሳፍሮ ከዚያ ሔደ ቅዱሳኑም አብረውት ሔዱ።

ወደ እስክንድርያ አገርም በደረሰ ጊዜ የከበረ ሰራብዮንን በመንኰራኵር ውስጥ ጽኑዕ ሥቃይን እንዲአሠቃዩት ወደ እሳት ማንደጃም ይጨምሩት ዘንድ አዘዘ። ከዚህም በኋላ ከነዳጅ ድፍድፍና ቅመማቅመም ጋር በወጭት ውስጥ ቀቀሉት የሥጋውንም ሥሮች ቆረጡ በብረት ዐልጋ ላይም አስተኝተው በችንካር ቸነከሩት ይህን ሁሉ ሥቃይም የሚታገሥ ሆነ የእግዚአብሔርም መልአክ ሥቃዩን ከላዩ ይቀበልለት ነበር።

ከዚህም በኋላ ከእንጨት ላይ ሰቅለው በፍላፃዎች ነደፉት የእግዚአብሔርም መልአክ እርሱን ከተሰቀለበት አውርዶ በእርሱ ፈንታ መኰንኑን አሥሮ ሰቀለው። የከበረ ሰራብዮንም እንዲህ አለው ሕያው እግዚአብሔርን በክርስቶስ ስም የታሠሩትን ሁሉንም እስከምታወጣቸውና የሞታቸውን ፍጻሜ እስከምታዝዝ አንተ ከእዚህ ከተሰቀልክበት ዕንጨት እንደማትወርድ ዕወቅ። በዚያንም ጊዜ ሁሉንም አውጥተው ራሶቻቸውን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ የእነዚህም ሰዎች ቊጥራቸው አምስት መቶ አርባ ነፍስ ሆነ።

ከዚህም በኋላ የከበረ ሰራብዮንን ወደ ሀገሩ ከእርሱ ጋር ወስዶ ያሠቃየው ዘንድ ከኀሳቡም ካልተመለሰ እራሱን በሰይፍ ይቆርጥ ዘንድ ኄሬኔዎስ አንዱን መኰንን አዘዘው። መኰንኑም ከርሱ ጋር በመርከብ ወሰደው ሌሊትም በሆነ ጊዜ ወደ አንድ ወደብ ደርሰው በዚያ ተኙ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ያቺ መርከብ ወደ ቅዱስ ሰራብዮን አገር ደረሰች በጥዋትም በነቁ ጊዜ የመሔጃቸው አቅጣጫ ተለውጦ አገኙ እጅግም አደነቁ ወደ ሰራብዮንም እነሆ ይቺ ሀገርህ ናት የሚል ቃል ከሰማይ መጣ ከመርከብም አውርደው ታላቅ ሥቃይን አሠቃይተው ራሱን በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። መኰንኑም ልብሶቹን አውጥቶ ገንዞ ለዘመዶቹ ሰጠው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ጢሞቴዎስ_ሐዋርያ

በዚህችም ቀን የከበረ ሐዋርያ ጢሞቴዎስ ከኤፌሶን አገር ወደ ቍስጥንጥንያ ከተማ የሥጋው ፍልሰት ሆነ። ጻድቁ ቈስጠንጢኖስም መንግሥትን በያዘ ጊዜ የከበሩ የሐዋርያትን ሥጋቸውን ከሰማዕታትም ብዙዎችን ከቦታው ሁሉ ወደ ቊስጥንጥንያ አፈለሳቸው ስለ ሐዋርያ ጢሞቴዎስም ሥጋ በኤፌሶን አገር እንዳለ ሰምቶ ካህናትንና ምእመናንን ላከ እነርሱም አፍልሰው ወደ ቊስጥንጥንያ አድርሰው በከበሩ ሐዋርያት ቤተ መቅደስ ውስጥ አኖሩት።
(ሙሉ ታሪኩ የጥር 23 ስንክሳር ይመልከቱ)
#ጥር_28

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ ስምንት በዚህች ቀን #ጌታችን_ተአምራትን በማድረግ ሰባት እንጀራና ጥቂት ዓሣ አበርክቶ ብዙ ሰዎችን ያጠገበበት መታሰቢያ ነው፣ የከበረ #ቅዱስ_ቀሌምንጦስ በሰማዕትነት ሞተ፣ #መነኰስ_ቅዱስ_አካውህ በሰማዕትነት ሞተ፣ የከበረ አይሁዳዊ የማኀው ልጅ የእመቤታችን ወዳጅ #ቅዱስ_ዮሴፍ አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#የጌታ_ተአምር

(ጌታችን 5 እንጀራ 2 ዓሣ አበርክቶ 5 የገበያ ሕዝብ እንደመገበ)

ጥር ሃያ ስምንት በዚህች ቀን ጌታችን ተአምራትን በማድረግ ሰባት እንጀራና ጥቂት ዓሣ ቆራርሶ አበርክቶ ብዙ ሰዎችን ያጠገበበት መታሰቢያ ነው።

በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመዘገበው ይህ የጌታችን ተአምር በውስጡ ብዙ ምሥጢራትን የያዘ ነው እንጂ ስለ ሥጋዊ ምግብ ብቻ የተነገረ አይደለም፡፡ ማቴ 14፡13-23፡፡ የተመገቡትና የተቆጠሩት አምስት ሺህ ወንዶች ብቻ ናቸው እንጂ ሴቶችና ሕጻናት አልተቆጠሩም፡፡ ይህስ ለምን ነው ቢሉ ሴቶች በአደባባይ ሲበሉ በሃፍረት ዳር ዳር ስለሚሉ ነው፡፡ ሕጻናት ደግሞ ከሚበሉት የሚፈረፍሩት ይበዛልና ነው፡፡

ጌታችን ያንን ሁሉ ሕዝብ በመንደር አጠገብ ሊመግባቸው ሲችል ለምን አርቆ ወደ ምድረ በዳ ወሰዳቸው ከተባለ ስለ ሁለት ምክንያት ነው፡፡

አንድም ‹‹ጥንት አባቶቻችሁን ከመንደር (ከግብጽ) አውጥቼ አርባ ዘመን ሙሉ መና የመገብኳቸው እኔ ነኝ፤ አሁንም በሥልጣኔ በተአምራቴ መገብኳችሁ›› ሲላቸው ነው፡፡

አንድም ጌታችን ተአምራቱን ከመንደር አጠገብ አድርጎት ቢሆን ኖሮ ሁልጊዜ ክፋትንና ጠማማ ነገርን ማሰብ ለአይሁድ ልማዳቸው ነውና ‹‹ፈጣን ፈጣን ደቀ መዛሙርቱን በጎን ወደ መንደር እየላከ ያስመጣው ነው›› ይሉት ነበር፡፡ ስለሆነም ጌታችን ለጥርጥር ምክንያት እንዳይኖራቸው አድርጎ ነው ተአምራቱን የገለጠላቸው፡፡ ጊዜውም አመሻሽ ላይ ነበርና ምሽት ላይ ያደረገበትም ምክንያት ጠዋት ላይ ቢሆን ኖሮ ‹‹የበላነው ሳይጎድል ነው ያበላን›› ብለው ከማመን ይርቁ ነበር፡፡

በተጨማሪም በበረሃ ያውም በምሽት ሕዝቡን በውኃ አጠገብ በሣር ላይ አስቀምጧቸው መመገቡ ‹‹በፍጻሜው ዘመን በምቹ ስፍራ በመንግሥተ ሰማያት መንፈሳዊ ምግብ እመግባችኋለሁ፤ በውኃ (በጥምቀት) በሚገኝ ክብርም አከብራችኋለሁ›› ሲላቸው ነው፡፡ ተአምራቱን ከውኃ ዳር ማድረጉ ‹‹መታጠቢያ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን›› እንዳይሉ ነው፡፡ ሳር የበዛበት ቦታ ላይ ማድረጉም ‹‹መቀመጫ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን›› እንዳይሉ ነው፡፡

አምስቱ እንጀራ የአምስቱ አዕማደ ምሥጢር ማለትም የምሥጢረ ሥላሴ፣ የምሥጢረ ሥጋዌ፣ የምሥጢረ ጥምቀት፣ የምሥጢረ ቁርባንና የምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ሁለቱ ዓሣ ደግሞ የፍቅረ እግዚአብሔርና የፍቅረ ቢጽ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ፍቅረ እግዚአብሔር ማለት እግዚአብሔር አምላክን በፍጹም ነፍስና በፍጹም ሐሳብ መውደድ ነው፡፡ ፍቅረ ቢጽ ደግሞ ባልንጀራን እንደራስ አድርጎ መውደድ ነው፡፡ አንድም ደግሞ እንጀራውና ዓሣው የቅዱስ ሥጋውና የክቡር ደሙ ምሳሌ ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ቀሌምንጦስ_ሰማዕት

በዚህች ቀን ኪራስ ከሚባል አገር ስሟ አክሮስያ የምትባል የመበለት ልጅ የከበረ ቀሌምንጦስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም የሆነ በገላትያ ነገሥት በአርአያኖስና በሉቅዮስ ዘመን ነው ከታናሽነቱም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሥርዓቷንና ሕጓንም እናቱ አስተማረችው ዕድሜውም ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲሆነው በጾምና በጸሎት መጋደል ጀመረ አገልግሎትንም አበዛ በእሳት የበሰለ ሥጋም ቢሆን አይበላም ነበር። እንደ ሠልስቱ ደቂቅ ጥሬ ባቄላ የሚመገብ ሆነ እንጂ ዲቁናም ተሾመ ጥበብና እውቀትም ተጨመረለት።

ወሬውም በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ በተሰማ ጊዜ ወደርሱ አስቀርቦ ብዙ ሸነገለው ለርሱም ልጁ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ትእዛዙንም ባልሰማ ጊዜ ታላቅ ሥቃይን አሠቃየው እግዚአብሔርም አጸናው ያለ ጉዳትም በጤንነት አስነሣው ከሀድያንንም አሳፈራቸው።

በዚያንም ጊዜ የምስክርነቱ ተጋድሎ በዲዮቅልጥያኖስ እጅ ሰባት እስቲደርስ አንድ ተብሎ ተቈጠረለት። ማሠቃየቱንም በደከመ ጊዜ ዲዮቅልጥያኖስ ወደ ሮም ንጉሥ ላከው እንዲህም ብሎ ጻፈ ይህ መሠርይ ከቶ እንደርሱ ያለ መሠርይ አላየሁም ለአማልክትም ይሠዋ ዘንድ ምናልባት ልቡን መመለስ ብትችል እነሆ ወዳንተ ላክሁት።

ወደ ሮሜው ንጉሥም በደረሰ ጊዜ የወርቅ ልብሶችን አመጡለት እርሱም ወደ ልብሶች አልተመለከተም ንጉሡም በእርሱ ላይ ተቆጣ ቊጣውንም አልፈራም በዚያንም ጊዜ በመንኰራኵር ታላቅ ሥቃይን አሠቃየው ገረፈውም ሕዋሳቱንም አስቆራረጠ እግዚአብሔርም እንደ ቀድሞው ያለ ጥፋት በጤንነት አስነሣው ይህም ሁለተኛ ምስክርነት ነው።

ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ወደ ኒቆምድያ ከተማ ወደ መክስምያኖስ ላከው በዚያም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃዩት ጌታችንም እንደቀድሞው በጤንነት አስነሥቶት ጠላቶቹን አሳፈራቸው ይህም ሦስተኛ ምስክርነት ነው።

ከዚህም በኋላ ወደ አደገባት ወደ ኪራስ ከተማ መለሱት በዚያም አሠቃዩት ጌታችንም በጤንነት ያለሥቃይ አስነሣው ይህም አራተኛ ምስክርነት ነው።

ዳግመኛም ወደ መክስምያኖስ መለሱት በዚያም ቅዱስ ከልከላዎስንና ብዙ ሰማዕታትን አግኝቶ እርስ በርሳቸው ተጽናኑ የከበረ ቀሌምንጦስንም ጽኑ ሥቃይን አሠቀዩት ጌታችንም እንደቀድሞው አዳነው ይህም አምስተኛ ምስክርነት ነው።

ከዚህም በኋላ ወደ መኰንን ሉቅዮስ ወሰዱትና በዚያ አሠቃዩት ጌታችንም አዳነው ይህም ስድስተኛው ምስክርነት ነው።

ሰባተኛውም ምስክርነት ብዙ ከአሠቃዩት በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጡ ሶፍያ የምትባል አማኒት ሴት መጥታ የቅዱሱን ሥጋ ወስዳ ገንዛ ቀበረችው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አካውህ_ሰማዕት

በዚህችም ቀን የከበረ መነኰስ አካውህ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ቅዱስ ፍዩም ከሚባል አገር ነው በምንኵስናውም ታላቅ ተጋድሎን ሲጋደል የኖረ ነው ሰይጣንም ተገልጦ መጣበት ቅዱስ አካውህም ሰይጣንን ይዞ በራሱ ጠጉር አሠረውና ሊቀጣው ጀመረ። ሰይጣንም ትለቀኝ ዘንድ በክርስቶስ መከራዎች አምልሃለሁ ብሎ ጮኸ በዚያንም ጊዜ ሰደደው እንደ ጢስም ተበተነ።

ከዚህም በኋላ በስደት ወራት ወደ ከሀድያን አደባባይ ሔደና እኔ ክርስቲያን ነኝ ብሎ ጮኸ ከሀድያንም ጽኑ ሥቃይን አሠቃይተው ራሱን በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። ከእርሱም ጋር ስምንት መቶ የሆኑ የቅዱስ አካውህ መኅበር በሰማዕትነት ሞቱ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ዮሴፍ_አይሁዳዊ (የእመቤታችን ወዳጅ)

በዚህችም ቀን የከበረ አይሁዳዊ የማኀው ልጅ ዮሴፍ አረፈ። ይህም ቅዱስ እስራኤላዊ ነው የአይሁድንም ሃይማኖት እየተማረ አደገ መጻሕፍቶቻቸውንም ተማረ።

በአንዲትም ዕለት እየተማሩ ሳለ የክርስቲያንን ልጆች አያቸው ከእርሳቸውም ጋር ትደምረው ዘንድ እናቱን ለመናት። በደመረችውም ጊዜ የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ሁሉ ተማረ የክርስቶስ ሃይማኖት ፍቅርም በልቡ አደረ ከዚህም በኋላ የቤተ ክርስቲያንን ሕግ ከሚወድና ከሚጠብቅ ከአንድ ክርስቲያናዊ ወጣት ጋር ተገናኘ እርሱም በቊርባን ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን ወሰደው ዮሴፍም ሥጋውንና ደሙን ተቀበለ።
#ጥር_29

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን መፃተኛ የሆነ የከበረች #ቅድስት_አክሳኒ አረፈች፣ተጋዳይ የሆነ #አባ_እስጢፋኖስ አረፈ፣ #አቡነ_ታዴዎስ_ዘጽላልሽ በሰማእትነት አረፉ፣ የጻድቃን #ቅዱሳን_ማኅበረ_ዶጌ #ከመድኃኔዓለም ጋር ማኅበር የጠጡ ቅዱሳን መታሰቢያቸው ነው፣ የከበሩ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ #አቡነ_ገብረ_ናዝራዊ_ዘቀወት አረፉ፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_አክሳኒ_ፈላሲት

ጥር ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን የስሟ ትርጓሜ መፃተኛ የሆነ የከበረች አክሳኒ አረፈች፡፡ እርሷም ከሮሜ አገር ለከበሩ ሰዎች ልጅ ናት ወላጆቿም ከርሷ በቀር ልጅ የላቸውም እርሷም የምትጋደል ሆነች በቀንና በሌሊትም ትፆማለች ትፀልያለች በሮሜ አገር ወዳለ የደናግል ገዳም በመሄድ ከእነርሱ ጋር ታገለግላለች ከአባቷ ቤት የሚያመጡላትን ምግብ ለድሆችና ለምስኪኖች ሰጥታ እርሷ ከደናግል ምግብ ትመገበለች የደናግል መነኮሳያትንም ጋር አንድ ያደርጋት ዘንድ እግዚአብሄርን አብዝታ ትለምን ነበር።

ከዚህም በኃላ ወላጆች ሊአጋቧት አስበው ከሮሜ አገር ታላላቆች ለአንዱ አጭዋት የወርቅ ልብሶችን ከወርቅና ከብር የተሰሩ የከበሩ ሽልማቶችንና ጌጦችንም አዘጋጁላት።

የጋብቻውም ቀን ሲደርስ እናቷን እናቴ ሆይ በምትጋቡኝ ጊዜ ወደ ደናግሉ መሄድ አይቻለኝም እኔ ዛሬ ሄጄ በረከታቸውን ተቀብዬ በረከታቸውን ተቀብዬ ሰላምታ ሰጥቻቸው ፈጥኜ መመለስ እሻለሁ አለቻት። እናቷም የነገስታት የሆነ የወርቅ ልብሶችን አልብሳ ሴቶች አገልጋዮችን ከእርሷ ጋር አድርጋ አሰናባተቻት።

እርሷ ግን ወደ ባህር ወደብ ተጉዛ መርከብንም አግኝታ ተሳፈረችና ወደ ቆጵሮስ ደሴት ሄደች።ወደ ከበረ ኤጲፋንዮስም ደርሳ ኀሳቧን ሁሉ አስረዳችው የከበረ ኤጲፋንዮስም ወደ እስክንድርያ አገር ሰደዳት ወደዚያም በደረሰች ጊዜ በህልሟ የከበረ ሀዋርያ ጳውሎስ ተገልፆ ስሙን ነገራትና የምትሰራውን ሁሉ አስተማራት።

በማግስቱም ወደ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ ገባች የራሷንም ጠጉር ተላጭታ የምንኩስና ልብስን ለበሰች ከርሷ ጋር ያሉ ሽልማቶችንና ጌጦችን የወርቅ ልብሶችንም ሸጠችና በሰማእታት መጀመሪያ በከበረ እስጢፋኖስ ስም ቤተ ክርስቲያን ሰራች አባ ቴዎፍሎስም ብዞዎች ደናግል መነኮሳይያትን ሰበሰበላትና በዚያ ገዳም ከርሷ ጋር የሚኖር ሆኑ።

ይቺም ቅድስት አክሳኒ ታላቅ ተጋድሎን ጀመረች እርሷ ከጥሬ ባቄላ በቀር በእሳት ያበሰሉትን አትቀምስና በምትተኛም ጊዜ ያለ ምንጠፍ በምድር ላይ ትተኛ ነበር እንዲህም እየተጋደለች ሀያ አመት ያህል ከዚያም የሚበዛ ኖረች ከዚህም በኃላ ጥቂት ታመመችና አረፈች።

ልኡል እግዚአብሄርም የሰጣትን ልእልና ሊገልጥ ወደደ። በአረፈችበትም አለት ሰዎች በቀትር ጊዜ የብርሀን መስቀል በሰማይ ውስጥ አዩ ብርሀኑም የፀሀይን ብርሀን ሸፍኖ ነበር የሚያበሩ ከዋክብትም አክሊላትም በዙሩያው ሆነው ስጋዋን ከደናግል ስጋ ጋር እስከ አኖሩ ድረስ የሚያበሩ ሆኑ ከዚያም በኃላ ተሰወረ ይህም ስለርሷ እንደተገለጠ ህዝቡ አወቁ።

በዚያንም ጊዜ እነዚያ ሁለቱ አገልጋዮቿ የዚችን ቅድስት አክሊኒ ከመጀመሪያው እስከ አረፍቷ ያለ ገድሏን ለሊቀ ጳጳሳቱና ለህዘቡ ሁሉ ስማቸውንም ለውጣ እህቶቿ እንዳለቻቸው እርሷንም እመቤታችን ማለት ሳይሆን እኅታችን እንዲሏት ምስጢሯንም ሁሉ እንዲሰውሩ እንዳማለቻቸው ተናገሩ። ሊቀ ጳጳሳቱና ህዝቡም ሁሉ አደነቁ ገድሏንም እስከመጨረሻ ፃፉ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_እስጢፋኖስ_ገዳማዊ

በዚህችም ቀን ተጋዳይ የሆነ አባ እስጢፋኖስ አረፈ፡፡ ይህም ቅዱስ ቅዱሳን ገዳማውያንን በመፈለግ በበረሀ ውስጥ ሲዞር የወደቀች የሰው ራስ አገኘ እርሷም ስጋ የሌላት አጥንት ብቻ ናት።

ስራዋንም ያስረዳው ዘንድ ወደ እግዚአብሄር ለመነ በዚያንም ጊዜ ከዚያች ራስ ውስጥ እንዱህ የሚል ቃል ወጣ እኔ በብዝበዛ ጭምር የማተርፍ ነጋዴ ነበርኩ መመፅወትንም አላውቅም በእኔ ዘንድ ካለው የገንዘብ ብዛትም አልጠግብም ነበር በአንዲትም እለት ወደ ንግድ ሩቅ ወደ ሆነ አገር ስጓዝ ውኃ ወደ ሌለበት በረሀ ደረስኩ የቀን ሀሩርም በፀና ጊዜ ግመሎቼ ሞቱ ባሮቼም ሸሹ ብቻዩንም ቀረሁ።

በሶስትኛውም ቀን አይኖቼ ከበዱኝ እንደፉጨትም ያለ ሰማሁ ያንጊዜ ነፍሴ ወጣች እንደስራዬም ቅጣቴን ልቀበል ወደ ስቃይ ቦታ ወሰዱኝ አንተም በለመንክ ጊዜ ስራዬን እነግርህ ዘንድ ወዳንተ አመጡኝ አሁንም ወደ ስቃይ ቦታ እንደይመልሱኝ እግዚአብሄርን ስለ እኔ ምህረትን ትለምነው ዘንድ እማልድሀለሁ አለው።

ቅዱሱም ወደ እግዚአብሄር ስለርሱ ለመነለት በዚያንም ጊዜ ስለአንተ ምሬዋለሁ የሚል ቃልን ሰማ ይህንንም ሰምቶ ወደ በዓቱ ሄደ እስከ አረፈ ድረስም እያለቀሰና ደረቱን እየደቃ ኖረ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_ታዴዎስ_ዘጽላልሽ

በዚህች እለት አቡነ ታዴዎስ ዘጽላልሽ በሰማእትነት አረፉ፡፡ አባታቸው ካህኑ ሮማንዮስ የደብረ ሊባኖሱ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት አጎት ሲሆኑ እናታቸው ማርታ ይባላሉ፡፡ የትልድ ቦታቸው ጽላልሽ ዞረሬ ነው፡፡ ሲወለዱ ዓምደ ብርሃን ተተክሎ የታየ ሲሆን እርሳቸውም በብርሃን ልብስ ተጠቅልለው ታይተዋል፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ለሊቀ ካህናቱ ለሕይወት ብነ በጽዮን ተሰጥተው ሃይማኖትን በሚገባ ተምረዋል፡፡

አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዳሞት ተሻግረው ሞተሎሚን አስተምረው ካሳመኑት በኋላ አቡነ ታዴዮስን ወደ እርሳቸው እንዲመጡ ልከውባቸው ሄደው አቡነ ተክለ ሃይማኖትን እያገለገሉ ዘጠኝ ዓመት ተቀመጡ፡፡ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ግን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አባ በጸሎተ ሚካኤል ሲሄዱ አቡነ ታዴዎስም ወደ ጽላልሽ ተመልሰዋል፡፡ ሁለቱም ከ32 ዓመት በኋላ ተመልሰው በጽላልሽ ተገናኘተው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለአቡነ ታዴዎስ ማዕረገ ምንኩስናን ሰጥተዋቸዋል፡፡

አቡነ ታዴዎስም በሥጋ ዕድሜ ታላቅ ቢሆኑም እንደታናሽ ብላቴና አቡነ ተክለ ሃይማኖትን እያገለገሉ በደብረ ሊባኖስ ተቀምጠዋል፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ ታዴዎስን ወደ ጽጋጋ እንዲሄዱ ነገሯቸው ምክንያቱም አቡነ አኖሬዎስ በዚያ ሲያስተምሩ ከሃዲያን ደብድበው አስረዋቸው ነበር፡፡ እሳቸውም ታስረው ሳለ ወደ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘንድ የሚላካቸው ሲያስቡ ቁራ መጥቶ ‹‹እኔ እላክሃለሁ›› ቢላቸው ‹‹ክፋትህ እንደ መልክህ ነው›› ብለው እምቢ አሉት፡፡ ርግብ መጥታ ‹‹እኔ እላክሃለሁ›› ብትላቸው ‹‹መጥተህ አድነኝ›› ብለው በክንፏ ላይ ጽፈው ልከዋት እርሷም መልእክቱን ለተክለ ሃይማኖት አድሳ ነበር፡፡ ስለዚህም ነው አቡነ ታዴዎስን ሕዝቡን ከኃጢአት ግዞት አኖሬዎስን ከእስራት እንዲያስፈቱ የላኳቸው፡፡

አቡነ ታዴዎስም በፋስ ሠረገላ ተጭነው መዩጥ ከተባለውና አኖርዮስን ካሰራቸው ንጉሥ ፊት ቢደርሱ ንጉሡ በግንጋጤ መልአክ የመጣበት መስሎት ሲፈራ ከሰው ወገን መሆናቸውን ነግረው ክርስትናን አስተማሩት፡፡ ጋኔን ከእሳት ጥሎት ሲሠቃይ የሚኖርና ሊሞት የደረሰ ልጁን ቢፈውሱለት በትምህርታቸውና በተአምራታቸው አምኖ ሕዝቡ ክርስትናን እንዲቀበል በአዋጅ አስነገረ፡፡ አፍጃል የሚባለው ባለጸጋ ወደ አቡነ ታዴዎስ ቀርቦ ሲማር ‹‹ባለጸጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ ይቀላል›› (ማቴ 19፡24፣ ማር 10፡25፣ ሉቃ 18፡25) የሚለውን የወንጌል ቃል ሲሰማ ለአእምሮው ረቆበት ‹‹እስቲ አድርገህ አሳየኝ?›› አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም እናቲቱን ግመል ከነጇ ቀጥሎም 28 ግመሎችን በየተራ በመርፌ ቀዳዳ እያሾለኩ አሳይተውታል፡፡ ሕዝቡ
#ጥር_30

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሰላሳ በዚህች ቀን #ቅድስት_ሶፍያ ከሦስት ድናግል ልጆቿ ጋር በሰማእትነት ሞቱ፣የከበሩ #አምስቱ_ደናግል_ሰማዕታት (ጤቅላ፣ ማርያ፣ ማርታ፣ ዓበያ፣ ዓመታ) በሰማዕትነት አረፉ፣ የሮም ንጉስ ልጅ የከበረች #ቅድስት_ኦርኒ በሰማዕትነት አረፈች፣ የመለኮትን ነገር የሚናገር #የቅዱስ_ጎርጎርዮስ መታሰቢያ ነው፣ ተጋዳይ የሆነ መነኰስ የከበረ #ቅዱስ_አክርስጥሮስ አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_ሶፍያና_ሦስቱ_ሰማዕታት_ልጆቿ

ጥር ሰላሳ በዚች ቀን የከበሩ ድናግል ጲስጢስ አላጲስና አጋጲስ በሰማእትነት ሞቱ የተባረከች አናታቸው ሶፍያም ከአንፆኪያ ከከበረ ወገኖች ውስጥ ናት።

እነዚህንም ሶስት ልጆች በወለደቻቸው ጊዜ በእሊህ ስሞች ጠራቻቸው ትርጓሜያቸውም ሀይማኖት ተስፋ ፍቅር ነው የራሷም ስም ትርጓሜው ጥበብ ማለት ነው።

ጥቂትም በአደጉ ጊዜ ወደ ሮሜ ከተማ ወስዳ በጎ አምልኮን እግዚአብሄርን መፍራትን የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት አስተማራቸው በከሀዲውም የሮሜ ንጉስ በአርያኖስ ዘንድ ወሬያቸው ተሰማ ወደርሱም የያመጡአቸው በማስተማር ትመክራቸውና ታፀናቸው ነበር። እንዲህም ትላቸዋለች ልጆቼ ተጠበቁ የዚህን የኃላፊውን አለም ክብር በማየት ልባችሁ እንዳይደክምና ከዘላለማዊ ክብር እንዳትርቁ ከሙሽራው ከክርስቶስ ጋር ሁናችሁ ወደ ሰማያዊ ሰርግ እንድትገቡ ጠንክሩ።እድሜያቸውም የታላቂቱ አስራ ሁለት የሁለተኛይቱ አስር የሶስተኛይቱ ዘጠኝ ነው።

እናታቸውም ወደ ንጉስ በአቀረበቻቸው ጊዜ ታላቂቱን ጲስጢስን እኔን ስሚ ከቤተ መንግስቴ ታላላቆች ለአንዱ አጋባሻለሁ ብዙ ስጦታም እሰጥሻለሁ ለአጵሎን ስገጂ አላት። እርሷም እርሱንና የረከሁ አማልክቶቹን ሰደበች እርሱም ተቆጥቶ በብረት ዘንጎች እንዲደበድቧት ጡቶቿንም እንዲቆርጡ እሳትንም ከብረት ምጣድ በታች በማንደድ ባሩድ ሙጫ ሰሊጥን በውስጡ አድርገው እጅግ አፍልተው ወደዚያ ይጨምሩዋት ዘንድ አዘዘ።

በጨመሩዋትም ጊዜ እየፀለየች በብረት ምጣዱ ውስጥ ቆመች ከቶ እሳት አልነካትም ።የምጣዱም ግለት ፀጥ ብሎ እንደ ጥዋት ጊዜ ጤዛ ቀዝቃዛ ሆነ ከዚያ ያሉ ሰዎችም አድነቀው እግዚአብሄርን አመሰገኑት ብዙዎችም በክብር ባለቤት እግዚአብሄር ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ራሶቻቸውንም ቆረጡዋቸውና በሰማእትነት ሞቱ።

ከዚህም በኃላ የቅድስት ጲስጢስን ራስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ምስክርነቷንም ፈፅማ የምስክርነት አክሊልን ተቀበለች እናቷም ስጋዋን አንስታ ወሰደች።ዳግመኛም ሁለተኛዋን አላጲስን አቀረቧትና ደበደቧት ፅኑእ ግርፋትንም ገረፏት ከጋለ ብረት ምጣድ ውስጥ ጨመርዋት በዚያንም ጊዜ ቀዝቅዞ እንደጥዋት ጤዛ ሆነ ንጉሱም ከዚያም እንዲአወጧትና ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ምስክርነቷንም አድርሳ በመንግስተ ሰማያት የህይወት አክሊልን ተቀበለች እናቷም ስጋዋን ወሰደች።

ቅድስት ሶፊያም ከስቃይ የተነሳ እንዳትደነግጥ ስለ ልጅዋ ስለ አጋጲስ ትፈራ ነበር ታፅናናትና እንድትታገስ ታደርጋት ነበር በዚያንም ጊዜ ወስደው ከመንኮራኩር ውስጥ ጨመርዋት እግዚአብሄርም መልአኩን ልኮ ያንን መንኮራኩር ሰበረው እርሷም ፊቷን በመስቀል ምልክት አማትባ ወደሚነደው እሳት ተወርውራ ገባች በዚያንም ጊዜ እሳቱ እንደ ጥዋት ውርጭ የቀዘቀዘ ሆነ ከዚያ ያሉትም ሰዎች ብርሀን የለበሱ ሁለት ሰዎች ከነጫጭ ልብሶች ጋር ሲጋራድዋት አይተው እጅግ አደነቁ ብዙዎችም በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ራሶቻቸውንም ቆርጠዋቸው በሰማእትነት ሞቱ ያቺንም የዘጠኝ አመት ልጅ የከበረች አጋጲስን ራሷን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ።ምክስርነቷንም ፈፀመች ሁሉም የማያልፍ የማይጠፋ ሰማያዊ መንግስትን ወረሱ።

የከበረች ሲፊያም የሶስት ልጆቿን ስጋቸውን ወስዳ ገነዘቻቸው ወደ ከተማውም ውጭ አድርሶ በዚያ ቀበረቻቸው በሶስተኛውም ቀን ወደ መቃብራቸው ሄዳ አለቀሰች ነፍሷንም ይወስድ ዘንድ ወደ እግዚአብሄር ለመነች ልምናዋንም ተቀብሎ ነፍሷን ወሰደ ምእመናን ሰዎችም መጥተው ገንዘው ከልጆቿ ጋር ቀበርዋት።

በከሀዲው ንጉስ ላይ ግን እግዚአብሄር ጭንቅ የሆነ ደዌ ላከ አይኖቹም ፈረጡ አጥንቶቹም እስከሚታዩ ስጋው ሁሉ ተሰነጣጠቀ እጆቹም ተቆራረጡ ከእርሱም ደምና መግል ፈሰሰ ትልም ይወድቅ ነበር ሁለመናውም ተበላሽቶ በክፉ ሞት ሞተ።ስለ እነዚያ ደናግል ጌታ ተበቅሎታልና።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አምስቱ_ደናግል_ሰማዕታት (ጤቅላ፣ ማርያ፣ ማርታ፣ ዓበያ፣ ዓመታ)

በዚችም እለት የከበረች ጤቀላ ከእርሷ ጋር ከሚኖሩ አራት ደናግል ጋር ፎላ በሚባል ኃጥእ ቄስ እጅ በሰማዕትነት ሞተች።

ይህም ፎላ የሚባል ቄስ በዓመፅ የሰበሰበው ብዙ ገንዘብ እንዳለው በከሀዲ መኮንን ዘንድ ነገር ሰሩበት መኮንኑም ገንዘቡን ሁሉ እንዲወርሱት አዘዘ ፎላም ወደ መኮንኑ ሄዶ ገንዘቡን እንዲመልስለት ማለደው። መኮንኑም ስለ እነዚህ ደናግል ሰምቶ ወደርሱ እንዲአመጡአቸው አዘዘ በመጡም ጊዜ ፎላን መኮንኑ ለፀሀይ ይሰግዱ ዘንድ እሊህን ደናግል ብትሸነግላቸው ገንዘብህን እመልስልሀለሁ አለው።

ፎላም ሊሸነግላቸው ጀመረ ደናግሉም አንተ የሰይጣን ልጅ የክብር ባለቤት ክርስቶስን እንክደው ዘንድ እንዴት ትፈትነናለህ አንተ ቀድሞ መምህራችን የነበርክ ስትሆን ብለው ዘለፉት።

መኮንኑም ቃላቸውን በሰማ ጊዜ በጅራፍ እንዲገርፏቸው አዘዘ እነርሱ ግን መናገራቸውን አልተውም ስቃይንም አልፈሩም። መኮንኑም ፎላን የበከተ ብትበላ ደምንም ብትጠጣ ገንዘብህን እመልስልሀለሁ አለው በሰማም ጊዜ ልቡናውን አፅንቶ ሊገድላቸው ሄደ እንደ አስቆሮቱ ይሁዳ ልቡ በገንዘብ ፍቅር ተነድፎዋልና።

ደናግሉም እንዲህ አሉት ከሀዲ ሆይ የመድኃኒታችንን ክርስቶስን ስጋውንና ደሙን በእጅህ ተቀብለን አልነበረምን ስለ ገንዘብ ፍቅር እኛን የክርስቶስን በጎች ታጠፋ ዘንድ እንዴት መጣህ እንዲህም እያሉ ሰልፍ እንደተማረ አርበኛ ሰው በሰይፍ ራሶቻቸውን ቆረጠ።

መኮንኑም የፎላን ብላሽነትና ድንቁርና አይቶ በሰይፍ ገደለው ነፍሱንም ገንዘቡንም ሀይማኖቱንም አጣ። የደናግሉም ስማቸው ጤቀላ፣ ማርያ፣ ማርታ፣ አመታ፣ ዓበያ ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_ኦርኒ_ሰማዕት

በዚችም ቀን ስሙ መርቅያኖስ የሚባል ለጣዖት የሚሰግድ የሮም ንጉስ ልጅ የከበረች ኦርኒ በሰማዕትነት አረፈች።የዚችም ቅድስት እናቷ ክርስቲያናዊት ናት አባቷም እልፍኝ ሰርቶላት በወርቅና በብር ልብሶች ከአጌጡ አስራ ሁለት ደናግል ጋር ወደዚያ አስገባት ከልጁ ጋር ይሰግዱላቸው ዘንድ አስራ ሰባት ጣዖታትን አወጣላቸው በላይዋም በሩን ዘጋ በዚያም ሰባት ዓመት ከስድስት ወር ኖረች።

በአንዲትም ዕለት ዐይኖቿን ወደ ምስራቅ ቀና በአደረገች ጊዜ ርግብን አየች በአፏም የዘይት ቅጠል ይዛ ነበር ከማዕድዋም ላይ ጥላው ወጣች ዳግመኛም ወደምእራብ ስትመለከት ቁራ መጣ በአፉም ከይሲ ይዞ ነበር ከማዕዷም ላይ ጥሎት ወጣ አደነቀችም።

በዚያንም ጊዜ አባቷ የሰጣት መምህርዋ መጣ ያንንም ራእይ አወራችለት እርሱም ሲተረጉምላት ርግብ የጥበብ ነገር ነው የዘይቱም ቅርንጫፍ በጥምቀት የሚገኝ ክብር ነው ቁራም ንጉስ ነው።ከይሲውም መከራ ነው አንቺም በርቺ ጠንካራ በክርስቶስ ስም መከራ ትቀበይ ዘንድ አለሽና የህይወት አክሊልንም ትቀበያለሽ አላት።

ከዚህም በኃላ በአደገች ጊዜ አባቷና እናቷ ወደርሷ ወጥተው ስለ ጋብቻ ተናገርዋት የከበረች ኦርኒም እስከ ሰባት ቀን ታገሱኝ አለቻቸው ከዚህም በኃላ እርሱ የመረጠውን መንገድ ይመራት ዘንድ ወደ እግዚአብሄር ፀለየች።
" #ጥር 1 "

<<< እንኩዋን ለቅዱስ "እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት" እና "ለአክሚም ሰማዕታት" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ >>>

+*" ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕት "*+

=>በሕገ ወንጌል (ክርስትና) የመጀመሪያው ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳሚው ሰማዕት ይህ ቅዱስ ነው:: ቅዱሱ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

+የቅዱስ እስጢፋኖስ ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም ይባላሉ:: (ሌሎች ናቸው የሚሉም አሉ) ገና ከልጅነቱ ቁም ነገር ወዳድ የነበረው ቅዱስ በሥርዓተ ኦሪት አድጐ እድሜው ሲደርስ ወደ ት/ቤት ገባ:: የወቅቱ ታላቅ መምሕር ገማልያል ይባል ነበር:: ይህ ሰው በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 5:33 ላይ ተጠቅሷል::

+በትውፊት ትምሕርት ደግሞ ይህ ደግ (ትልቅ) ሰው በርካታ ቅዱሳንን (እስጢፋኖስን : ዻውሎስን : ናትናኤልን : ኒቆዲሞስን . . .) አስተምሯል:: በጌታችን መዋዕለ ስብከት ጊዜም ከፈጣሪያችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ እየቀረበ ይጨዋወት ነበር:: በፍጻሜውም አምኗል::

+ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ እስጢፋኖስ ከዚህ ምሑር ዘንድ ተምሮ: ኦሪቱን ነቢያቱን ጠንቅቆ ወጣ:: ወቅቱ አስቸጋሪና ለኃጢአት ሕይወት የተመቸ ቢሆንም ቅዱሱ ግን የመሲህን መምጣት በጸሎትና በተስፋ ይጠባበቅ ነበር::

+በወቅቱ ደግሞ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ የንስሃ ጥምቀትን እየሰበከ መምጣቱን የተመለከተ ቅዱስ እስጢፋኖስ ነገሩን መረመረ:: ከእግዚአብሔር ሆኖ ቢያገኘው የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆነ:: ለ6 ወራትም በትጋት ቅዱስ ዮሐንስን አገለገለ::

+ለ6 ወራት ከቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ ከተማረ በሁዋላ ለስም አጠራሩ ስግደት ይድረሰውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠመቀ:: በወቅቱ
የተደረገውን ታላቅ ተአምር ልብ ያለው ቅዱስ እስጢፋኖስ
መምሕሩን ቅዱስ ዮሐንስን እንዲያስረዳው ጠየቀው::
"ከእኔ ይልቅ
ከፈጣሪው አንደበት ይስማው" በሚል ላከው:: ቅዱሱም
ከጌታ ዘንድ ሔዶ: እጅ ነስቶ ተማረ:: (ሉቃ. 7:18)
በዚያውም
የጌታ ደቀ መዝሙር ሆኖ ቀረ:: ጌታም ከ72ቱ አርድእት
አንዱ አድርጐት ለአገልግሎት ላከው:: አጋንንትም
ተገዙለት::
(ሉቃ. 10:17)

ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታችን መድኃኔ
ዓለም ከዋለበት እየዋለ: ካደረበት እያደረ ወንጌልን
ተማረ::
ምሥጢር አስተረጐመ:: ጌታ በፈቃዱ ስለ እኛ ሙቶ
ከተነሳ በኋላ ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን በአንብሮ እድ
ባርኳል:: በዚህ
ጊዜም ቅዱሱ እንደ ወንድሞቹ ሐዋርያት ቅስናን
(ዽዽስናን) ተሹሟል:: በበዓለ ሃምሳም መንፈስ ቅዱስ
በወረደ ጊዜ ከ72ቱ
አርድእት የእርሱን ያህል ልሳን የበዛለት:ምሥጢርም
የተገለጠለት የለም:: በፍጹም ድፍረትም ወንጌልን
ይሰብክ ገባ::

በመጀመሪያይቱ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከማዕድ ሥርዓት
ጋር በተያያዘ ፈተና ሲመጣ በመንፈስ ቅዱስ ምርጫ 7
ዲያቆናት
ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር:: አልፎም የ6ቱ ዲያቆናት
አለቃ እና የ8ሺው ማሕበር መሪ (አስተዳዳሪ) ሆኗል::
8ሺ ሰውን
ከአጋንንት ፈተና መጠበቅ ምን ያህል ከባድ እንደ ሆነ
ለማወቅ አባቶቻችንን መጠየቅ ነው::

አንድን ሰው
ተቆጣጥሮ
ለድኅነት ማብቃት እንኳ እጅግ ፈተና ነው:: መጽሐፍ
እንደሚል ግን 'መንፈስ ቅዱስ የሞላበት: ማሕደረ
እግዚአብሔር'
ነውና ለእርሱ ተቻለው:: (ሐዋ. 6:5) አንዳንዶቻችን ቅዱስ
እስጢፋኖስ 'ሊቀ ዲያቆናት' ሲባል እንደ ዘመኑ ይመስለን
ይሆናል:: እርሱ በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነው::
ዲቁናው ለእርሱ 'በራት ላይ ዳረጐት' ነው እንጂ እንዲሁ
ዲያቆን
ብቻ አይደለም::

ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በኋላ
ለ 1 ዓመት ያህል 8ሺውን ማኅበር እየመራ: ወንጌልን
እየሰበከ
ቢጋደል ኦሪት 'እጠፋ እጠፋ': ወንጌል ደግሞ 'እሰፋ እሰፋ'
አለች:: በዚህ ጊዜ 'ክርስትናን ለማጥፋት መፍትሔው
ቅዱስ
እስጢፋኖስን መግደል
ነው' ብለው አይሁድ በማመናቸው ሊገልድሉት አስበውም
አልቀሩ ገደሉት::

+እርሱ ግን ፊቱ እንደ እግዚአብሔር መልአክ እያበራ
ፈጣሪውን በብዙ ነገር መሰለው:: በመጨረሻውም ስለ
እነሱ ምሕረትን
እየለመነ በድንጋይ ወገሩት:: ደቀ መዛሙርቱም ታላቅ
ለቅሶን እያለቀሱ ቀበሩት::

*"ፍልሠት"*

+ቅዱስ እስጢፋኖስ ካረፈ ከ300 ዓመታት በኋላ
በኢየሩሳሌም የሚኖር አንድ ደግ ሰው ነበር:: ስሙም
ሉክያኖስ ይባል
ነበር:: በተደጋጋሚ በራዕይ ቅዱሱ እየተገለጠ "ሥጋየን
አውጣ" ይለው ነበርና ሒዶ ለዻዻሱ ነገረው:: ዻዻሱም
ደስ ብሎት
ካህናትና ምዕመናንን ሰብስቦ ወደ አጸደ ገማልያል
(የመምሕሩ ርስት ነው) ሔደ::

+ቦታውንም በቆፈሩ ጊዜ ታላቅ መነዋወጥ ሆነ::
መላእክት ሲያጥኑ በጐ መዓዛ ሸተተ:: ዝማሬ መላእክትም
ተሰማ:: ሕዝቡና
ዻዻሱም በቅዱስ እስጢፋኖስ ፊት ሰግደው: በታላቅ
ዝማሬና በሐሴት ዐጽሙን ከዚያ አውጥተው: በጽርሐ
ጽዮን (በተቀደሰችው
ቤት) አኖሩት::

እለ እስክንድሮስ የተባለ ደግ ሰውም ቤተ
ክርስቲያን አንጾለት ወደዚያ አገቡት:: ከ5 ዓመታት
በኋላም
እለ እስክንድሮስ ሲያርፍ በሳጥን አድርገው በቅዱሱ ጐን
ስለ ፍቅሩ አኖሩት::ሚስቱ ወደ ሃገሯ ቁስጥንጥንያ
ስትመለስ
የባሏን ሥጋ መስሏት የቅዱስ እስጢፋኖስን ቅዱስ ሥጋ
በመርከብ ጭና ወሰደችው:: መንገድ ላይ ከሳጥኑ ውስጥ
ዝማሬ ሰምታ
ብታየው ያመጣችው የቅዱሱን ሥጋ ነው:: እጅግ ደስ
አላት: አምላክ ለዚህ አድሏታልና::

እርሷም ወስዳ ለታላቁ
ንጉሥ
ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ አስረከበች:: በከተማውም ታላቅ
ሐሴት ተደረገ::ሥጋውን ሊያኖሩት በበቅሎ ጭነው
ሲወስዱትም በቅሎዋ
በሰው ልሳን ተናግራ ማረፊያውን አሳወቀች:: በዚያም ላይ
ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ታንጾለታል:: ቅዱስ እስጢፋኖስ
ሲመቱ
ጥቅምት 17: ዕረፍቱ ጥር 1:ፍልሠቱ ደግሞ መስከረም
15 ቀን ነው::

'' ሰማዕታተ አክሚም ''

+በቤተ ክርስቲያን የሐዲስ ኪዳን ታሪክ አሰቃቂ ጭፍጨፋ
ከተካሔደባቸው አካባቢዎች አንዷ ሃገረ አክሚም ናት::
አክሚም
ማለት የቀድሞ የግብጽ አውራጃ ናት:: በተለይ በ3ኛው
መቶ ክ/ዘመን በርካታ ክርስቲያኖች በፍቅር ይኖሩባት
ነበር::

በከተማዋ ውስጥ የሚኖሩ ክርስቲያኖች ጥቡዓን:
ታማኞች:ሥጋውን ደሙን የሚቀበሉና ዘወትር ቅዱስ ቃሉን
ለመስማት
የሚተጉ ነበሩ:: ለዚህም ደግሞ ከሊቀ ዻዻሱ አባ
ብኑድያስ ጀምሮ ካህናቱ: ዲያቆናቱ: ንፍቅ ዲያቆናቱ:
መጋቢዎቹ:
አናጉንስጢሶቹ (አንባቢዎቹ): መምሕራኑ: መሣፍንቱም
ሳይቀር ለክርስቶስ ፍቅር የተጉ መሆናቸው አስተዋጽኦ
ነበረው::
በተለይ ግን 2 ወንድማማቾች የነበራቸው ቅድስና
ብዙዎችን ስቧል:: እኒህ ቅዱሳን ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ
ይባላሉ::

ከባለ ጸጋና ባለ ስልጣን ቤተሰብ ቢወለዱም ክርስትናቸው
አልቀዘቀዘም:: የወጣትነት ስሜት ሳያሸንፋቸውም ወደ
በርሃ ተጓዙ::

+በዚያም በቅድስና ኑረው ለክህነት ማዕረግ በቅተዋል::
ቅዱሳኑ በገዳም ሳሉም መድኃኒታችን ክርስቶስ ተገልጦ
"ወደ ትውልድ ሃገራችሁ አክሚም ተመለሱ:: ክብረ ሰማዕታት