ቅንጭብጭብ
7.66K subscribers
408 photos
9 videos
1 file
497 links
ካየሁት 👀 አስገራሚ
ከሠማሁት 👂 መሣጭ
ካነበብኩት 📖 አስተማሪ
ካሠብኩት ♀🅱 ልዩ ልዩ

እነሆ #ቅንጫቢ

ፅሁፎቻችሁን በ @bcrAzykid አካፍሉን።

ለማንኛውም አስተያየት ጥያቄ እና ጥቆማ @bcrAzykid ይጠቀሙ።
Download Telegram
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

#ቃል < #ስሜት!
.
.
እንዲህ ነው እምወዳት
እንዲያ ነው እሚያደርገኝ
ብየ ለማስቀመጥ
ቃላት ባመራርጥ
ስሜት ነው እሚተርፈኝ
ቃል ሁሌ ነው እሚያንሰኝ..

መስከረም 27/2014 ዓ.ም

✍️ Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

@kinchebchabi
@kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
!!︎!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

#ለእኒያ_ሰባኪዎች¡¡¡
.
.
በከንፈር ፍሬያቸው
የአገሬን ነፃ አውጮች፡እስካሁን ሳቃቸው
ሲገቡ እንደ እንጀራ
ላፍ ጣፍጠው ተስማምተው
ሲወጡ እንደ እዳሪ ሸተውና ገምተው፤
ነበር እስከ ዛሬ መንበር ላይ ሲነግሱ
አንጀት እየበሉ አንጀት ሚበጥሱ፤
አሁን ግን ዘንድሮ
በሆድ በአንጀት አልፈው ተገፍተው ሳይወጡ፤
ገና ከአፍ ጀምረው መግማማት አመጡ፤
ግን
ግን
ግን
ይኸው ግማታቸው ካለ ሚስማማቸው
ሀገሬ እዳሪ ቤት አትሆንም በሏቸው።
ለእኒያ ሰባኪዎች!!!🗣😑

Jonas_Yotode
thanks for sharing your poem😊🙏

የልብዎን ድርሰት፣ ግጥም፣ ፍልስፍና፣ ስዕል፣ አባባል፣ ተረት፣ ታሪክ..ያጋሩ አሁኑኑ ይቀላቀሉ!!😊🙏
👇👇👇👇 👇👇👇👇
@YelbeDrset @YelbeDrset
@YelbeDrset @YelbeDrset
✉️✉️✉️✉️✉️✉️✉️✉️✉️
inbox me @amanYTZ23
✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️✍️
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
.
.
.
በህይወት የተሞላ ተፈጥሮ ለአንድ አፍታ ቢያስተዉሉት ፍፁም ድንቅ የሆነ..አመሻሽ ላይ ፀሐይ አዘቅዝቃለች ሰዉነቶ እንኳ አይታይም የእሳት መክብብ የመሰለው ብርሃኗ ግን ለሰማዩ ዉበትን ችሮታል ይሄን ብርሃን ሳይርቅ ሳይሰለብ ደርሸ ብነካው በህይወት የሚሞላኝ ይመስል ተነስና እሩጥ ተከተለው አለኝ ግን ከተጎለትኩበት ዝቅታ አልተንቀሳቀስኩም በአካቢው እየበረሩ የነበሩትን አእዋፋት ባረገኝ ብየ ተመኘሁ'ጂ..

ጥቅምት 5/2014 ዓ.ም

✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join join join
👇👇👇👇👇
t.me/YelbeDrset
t.me/YelbeDrset
t.me/YelbeDrset
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
#ግዕዝ_ክብር_ይእቲ
#ዘዘዮሐንስ (አለቃ)

መፈወስ ነፍስ ወይነ ለምንት ኢተኃሥሢ?
ዘታፈቅሪ ነፍስየጨቤተ መያሲ ትጊሢ
ወእንዘ ታነብቢ ዘልፈ ምዕዳነ ዳዊት ነጋሢ
እም እኩይ ግብር ለምንት ኢትትጋኀሢ?
.
.
.
ጠዋት በማለዳ
ወደ ጠጅ አደይ ቤት
የምትገሰግሺ አንቺ የኔ ነፍስ ሆይ!
ከጠጅ የተሻለ
ሕይወት የተሞላ ጥበብ የተሞላ
የሚፈዉስ ወይንን ለምን አትፈልጊም እሱ አይሻልም ወይ?
አዉቃለሁ ታዉቂያለሽ
የንጉስ ዳዊትን
ቅኔዉን ምክሩን ዞትር ታነቢያለሽ
ዞትር ትደግሚያለሽ።
ነገር ግን በተግባር
ወይንን ተጸይፈሽ እዛው ጠጅ ቤት ነሽ
ከማለዳ አንስቶ ጀንበር እስክትሸሽ።
ታዲያ!
ከቶ ምን ዋጋ አለው ቢያዉቁ ቢራቀቁ
ከመፅሐፍ ዉቂያኖስ ጫፍ ድረስ ቢጠልቁ
በሕይወት ካልታየ
የዕዉቀት ወሰኑ የዳዊት ድጋሙ
ጸሎትና ዕዉቀትሽ
ያለ'ካል የሚታይ ረጅም ጥላን ነው ሚሆነው ትርጉሙ
እባክሽ ነፍሴ ሆይ?

✍️ዉርስ ትርጉም
#በኤፍሬም_ሥዩም_ተሰማ

📚ምንጭ #ተዋነይ_ብሉይ_የግዕዝ_ቅኔያት_ፍልስፍና_ከቀደምት_የኢትዮጵያ_ነገሥታት_እና_ሊቃዉንት

join join join join
👇👇👇👇👇
@YelbeDrset
@YelbeDrset
@YelbeDrset
👆👆👆👆👆
📚📚📚📚📚📚📚📚
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
"..አመታት ከሚመስሉ ወር ከማይሞሉ ቀናት በኋላ አየኋት፣ ቀረብኳት፣ የምትተነፍሰዉን አየር እኩል ተነፈስኩኝ፣ ደግሞ እጆቿን ያዝኩ በስስት ተሳለምኩ አክየም አቀፍኳት ትንፋሽ እስከሚያጥራት ከንፈሯን ጎረስኩኝ አንገቷ ስር ገባሁ ጠረኗ አወደኝ! ሰከርኩ! ሰከርኩ! ሰከረኩ! ይባስ ናፈቀችኝ!..ከጎኔ እንዳትርቅ ካይኔ ሰር እንድትኖር ቃልኪዳን አሰብኩኝ..አስቤ አልቀርም..!!

✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join join join join
👇👇👇👇👇
@YelbeDrset
@YelbeDrset
@YelbeDrset
👆👆👆👆👆
📚📚📚📚📚📚📚📚
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
.
ካሜራ ማን ነኝ..!
ሁሌ ባጋጣሚ በመንገድ ላይ ሳያት
እድልም ብሎልኝ በድንገት ሳገኛት
ስትስቅ ነው ማስተዉላት
ስትስቅ ነው እምቀርፃት
በካሜራየ አይን በአልበም እማሰፍራት
ሰርክ አዲስ ፈገግታዋን በፎቶ ምይዛት
በአካል ግን በቅርበት
አልነካት አላቅፋት..
ዛሬም ከርቀት በጎዳናው ሽር ስትል
ካሜራየን አነጣጥሬ ልክ ልስላት ስል
አይኔን አላመንኩም ፈገግታዋ የለም
መልኳ ደማምኗል ዝም ብላለች ዝም..?!?
.
.
✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join join join join
👇👇👇👇👇
@YelbeDrset @YelbeDrset @YelbeDrset
🤫🤫🤫🤫🤫🤫🤫🤫🤫
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ


#ሰው_ከመሆን_ሰውሩኝ! ፬
.
.
"..ሰው ማለት ሰው የሚሆን ነው ሰው የጠፋለት ሲባል ሰምቻለሁ፤ ሰው ሆኘ ለሰው ካላዘንኩ ሰው ሆኘ ሰው ሲሞት ከእነገሌ ስለሆን የማይገደኝ ከሆነ ሰው ከመሆን ሰውሩኝ፤ ከሰው ተራ አውጡኝ።"

✍️Unknown
(ከነፃ ሃሳብ ጋዜጣ ላይ የተወሰደ)

join join join join
💔💔💔💔💔💔
@YelbeDrset @YelbeDrset @YelbeDrset
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
"በልቤም ሆነ በአዕምሮዬ አላፈቅርሽም። እንዲያው ምንአልባት ልብም መምታቱን ስለሚያቆም አዕምሮም ስለሚረሳ። በነብሴ አፈቅርሻለሁ። ነብስ በፍፁም አትቆምም ወይም አትረሳምና።"

✍️Rumi

join and share
@YelbeDrset @YelbeDrset @YelbeDrset @YelbeDrset
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

#አበባ_አየሁ

©ሲራክ ወንድሙ

እሩቅ ለሩቅ ሆነን
ይጠባል መስከረም ፥ ይታጠናል ህዳር
ፀደይ እየዳኸ
ክረምት ይጋልባል ፥ ተስፋዬን ሳሳምር

አምና በዚህ ሰዓት ፥ ጠበቅኩሽ በውርጩ
እስኪያልፍብኝ ሀሩር ፥ ወፎች እስኪንጫጩ

ጠበቅኩሽ ፥ ጠበቅኩሽ
የሌት ውብ እንቅልፌን ፥ በናፍቆት መጅ ድጬ
በመምጣትሽ እርሾ ፥ ልቤን አሳብጬ።

የአንቺ ሀገር ወዴት ነው የአድማስሽ አቀበት ?
እግሬን ላወላዳ ፥
ይቆምልኝ እንደው የልቤ ትኩሳት
ተይ ንገሪኝ ባክሽ ፥ ወዴት ነው ባዕቱ
ካቻምና ላይ ቆሜ ፥ መነነ ዘመኑ ከነፈ ጊዜያቱ

የተራራው ደረት በአደይ ፂም ጎልምሶ
የሀምሌ ጨለማ
ባባረረው ብርሃን ፥ ሲሄድ ተለሳልሶ
እንደው ለአዲስ ዓመት ፥ ትጋቴን አስታውሰሽ
ናፍቆት ፣ ተስፋ ፣ ፍቅርን - አንድ ላይ ታቅፈሽ
በሬን ከፍተሽ ግቢ ፥ አበባ - አየሁ ብለሽ
....
©ሲራክ @siraaq
https://t.me/kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ
.
.
#ከማስታዎሻየ_ማህደር!!
.
.
#ሌላ_ዓለም!!
(ክፍል አንድ)
.
.
.. ትናንት ህዳር 8/2015 ዓ.ም "አርባተንሳ" ክብረ በዓልን ልታደም ወደ ገጠራማው መንደር ካ'ንድ ወዳጄ በቀረበልኝ ጥሪ መሰረት ወርጀ ነበር። ወዳጀ ካለኝ ቦታ ደርሸ ካገኘሁት በኋላ ያው እንደተለመደው 'ቅርብ ነው ደርሰናል!' እያለ ሰፈር ለሰፈር ትንሽ ተጉዘን ከቤታቸው ደረስን የቤቱ ግቢ በላም በጥጃዎችና በእርሻ የተከበበ ነው። ግቢው በር ላይ የተቀመጡ ሰዎችን ሰላምታ ሰተን ወደ ቤቱ ዘለቅን.. የቤቱ አባወራ ከሳሎኑ ጥግ ይዘው ተቀምጠዋል..ቅድሚያ እርሳቸዉን ሰላምታ ሰተን በቤቱ ያሉ እንግዶችንም ጨበጥናቸው እና የበግ ቆዳ ከተጎዘጎዘበት መደብ ቁጭ አልን። ወዳጄ ቀልጠፍ አለና ወደ ኩሽናው ዘልቆ እህቱን ምግብ እንድታመጣ አዘዛትና "ክቡር ዘበኛ" እሚባለዉን ብርጭቆና በጆክ ጠላ ይዞ መቶ ከፊቴ ቆመ.. እኔም ከቤቴ እንደበላሁና ያው ጠላም እንደማልጠጣ በመናገር አስቤ የመጣሁት "ወተት ለመጠጣት!" እንደሆነ አስታወስኩት!😋 ቢሆንም 'ካልበላህ ወተት የለም!'😑 እሚል እይታ አሳይቶኝ ለራሱ ጠላዉን ቀድቶ ቁጭ አለ። በልቤም አንድ ቁርጥ አንስቼ እበላና ወተቴን እጠጣለሁ ብየ መጠበቅ ያዝኩ ታዲያ የወዳጄ እህት በሰሃን(ባቲ) የሰማይ ስባሪ እሚያክል እንጀራ በድንች በስጋ ወጥ ይዛ መታ አስረከበችኝ!! 'ኧረ በዝቷል ይተርፋል!' ብልም ሰሚ ስላላገኘሁ ወደ ወዳጄ አባት ፊቴን መልሸ 'አባት ይባርኩልኝ?' አላኳቸው(አክባሪ ለመባል) ምን ዋጋ አለው! 'ለወንድ አይባረክም! ዝም ብለህ ብላ!' ብለው ጨነገፉኝ።😬 ኩርኩሜን ተቀብየ ከወዳጀ ጋር የቀረበልኝን ምግብ መብላት ጀመርኩ.. ወዳጄ ምግቡን አቋርጦ ወደ ኩሽናው ተወነጨፈና በግራም ሰሃን እርጎ ይዞ መጣና እንጀራዉን መሸከም ያቃታት ሰሃን(ባቲ) ላይ እርጎዉን አጥለቀለቀው..😇 በላየላይ የወረደዉን መና እያጣጣምኩ በላሁ..😋 ታዲያ በየ መሃሉ አባወራው በመገረም ለምን ጠላ እንደማልጠጣ እየደጋገሙ ይጠይቁኛል! እኔም የተለያዩ መልሶችን እነግራቸዋለሁ.. ወዳጄና እህቱም እንጀራና ወጥ እያመጡ ጨምር እያሉ ከድንች በስጋው ወጥም ከእርጎና ከንጀራዉም ይከምሩብኛል..🙄'ኧረ በቃኝ!' ብልም የቤቱ አባዎራ ጨምሮ እንግዳቹ ሁሉ 'ትንሽ ብላ እንጅ!' እያሉ አጨናነቁኝ እኔ ግን ተሎ መሃላ ዉስጥ ገብቼ ድርቅ በማለት እጄን ታጠብኩና ቁጭ አልኩ..መቼም የገጠር ሰዎች እማይበላ እማይጠጣ አይወዱም።
.
.
ይቀጥላል..


✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join and share
@YelbeDrset
@YelbeDrset

inbox me @amanYTZ23
✍️✍️✍️✍️✍️✍️
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

#ከማስታዎሻየ_ማህደር!!
.
.
.
#ህይወት_የመኖር_እዳ!!
.
.
.. ከተወለድኩ ጀምሮ እድሜዬ በጨመረ ቁጥር ወደ ህይወት እየመጣሁ ይሆን ወይስ ወደ ሞት እየሄድኩ እንደሆን አላዉቅም! ስለ ህይወት እያወኩ ለመኖር እየጀመርኩ ግን ወደ ሞት እየሄድኩ ይመስለኛል! መኖር ታዲያ እንዴት ስጦታ ሊሆን ይችላል?? ሐይማኖተኛ ሰዎች አንደበት ላይ እማይጠፋ ቃል "በህይወት ስላለህ ብቻ አመስግን!!" እሚለው ነው!! ግን ለኔ አይታየኝም! መፈጠሬን እንደስጦታ አይቼ ለማመስገን ህይወት በቃኝ እስክል መኖር አለብኝ! ካልሆናማ እንዲሁ ወደ ህይወት እየመጣሁ ወደ ሞት ከሄድኩ ስጦታነቱ ቀርቶ ኑሮ እዳ ይሆንብኛል!! ሳልሞት በፊት ተሽቀዳድሜ መኖር ያለብኝ እዳ ሁኖ ይሰማኛል። ሰው ሳይኖርም ይሞታል!
   ህይወት ከፈጣሪ እምትሰጠን ብድር ትመስለኛለች ብድራችን ለመክፈል ስንፈጋ ስንታገል የተሰጠን የክፍያ የቀን ገደብ አልቆ እኛም በነፃነት ሳንኖር እምንነጠቃት ናት። የሰው ልጅ ሁሉ "የህይወት ግብ ደስተኛ መሆን ነው!" በምትለው ህግ ይተዳደራል! ይሄን ህግ ሐይማኖተኞች ቢያጥላሉትም በነሱ ልብ እንደማያምኑበት ቢናገሩም እነሱም በሆነ የህይወት ዘመናቸው ይከተሉታል። ሁሉም ሰው በራሱ ዛቢያ ኑሮን ለማሸነፍ ይሽከረከራል፤ ኑሮን ማሸነፍ ያው ሀፍታም መሆን ነው! ብሎ አዕምሮው ላይ በሰቀለው ሃሳብ ይነዳል። መፈጠሩን እንደ እዳ ለማየት ወይንም እንደ ስጦታ ለመቀበል በቀላሉ በአኗኗር ዘይቤው ይወስናል፤ ብዙዉን ጊዜ ሀፍትን ካካበተ ስጦተነቱን በተቃራኒው በድህነት ከተሰቃየ ደግሞ እዳነቱን ይቀበላል፤ እዚህ ላይ አንዳንድ ነገረኛ አንባቢ "ታዲያ አንተ በድህነት ተሰቃይተህ ነው! ህይወት የመኖር እዳ ናት የምትል" ይል ይሆናል! ግን ህይወት እንዳለህ ሀብት ወይም እዉቀት የምትወሰን ናት በሚለው አልስማማም!! ምክኒያቱም ህይወት አወቅንም አላወቅን ሀፍታም ሆን ወይ ፀደቅን እስክንሞት ድረስ እዳ ናት!! አዋቂው ህይወትን ተረዳኋት ባላት መጠን ሲያብራራና ሲያወጣ ሲያወርዳት ትንሽ በተጠጋት ቁጥር እማያዉቀው እልፍ መሆኑን እየተረዳ አለማወቁን አዉቆ እንኳ እረፍት ሳያገኝ የእዉቀት ጥሙን ሳያረካ ያርፋል!! አላዋቂዉም መኖር ባለማወቅ የሰጠችዉን ሰላም ተቀብሎ መኖሩ ሳይታወቅ በሚራመድበት መሬት የሆነ መስመር የእግሩ አሻራ ሳይታይ ይሞታል!! ሀፍታሙ ሃፍቱን የደከመበትን ያህል ሳያጣጥመው ወይ ደግሞ በሀፍቱ ልክ ደስተኛነቱ የወረደ ሲሆንበት! ወይ ሀፍቱ እረፍት እንደነሳው ሌላ አስደሳች ግብ ወይ ምላሽ ሲፈልግ ያልፋል!! ፃዲቁ ደግሞ የፈጣሪው ፍርድ እያስፈራው በአካባቢው ያሉ ሰዎች ኑሯቸዉን በሐጢያታቸው እየለካ የመኖር ጣእሙን እርግፍ አድርጎ ትቶ ሞቱ እንዲቀርብለት እየፀለየ ይኖራል!? መፈጠሩ ስጦታ ነው ብሎ ግን መኖሩን ከመሞት በላይ አይወደዉም! ስጦታ ብሎ የተቀበለዉን ህይወት በሞት መነጠቅን ይናፍቃል እንደናፈቀዉም አይቀርምና ያገኘዉና ይቀበላል!!
   በነዚህ ሁሉ መሃል እኛ "ሁሉን ቀመስ!" እምንባል አይነት ሰዎች አለን!! የማህል ዳኛ ማለት ነን፤ ሌሎች በተለያየ አቅጣጫ የመኖራችን ግብ ብለው ያመኑበትን ሲያስቆጥሩ እምናጨበጭብ አንዳንዶች ደግሞ ሲደናቀፉም (ፋዎል) ሲሰሩ እምንታዘብ!! አለን። ለኛ ህይወት ጥያቄ እንጅ መልስ ሁና እማታዉቅ!! ህይወት የመኖር እዳ እንጂ ስጦታ ሁና እማትታየን!! ብዙ የገባን ይመስለናል ግን አንዳች ነገር አንፈታም! እምናምን ግን ደግሞ እማናምን! ወደ ህይወት እንመጣል ግን ደግሞ እማንደርስ! ወደ ሞት እምንሄድ!! እዉቁ ፈላስፋ.. "ያልተመረመረ ህይወት ለመኖር ያልተገባ ነው!" እንዳለው የኛ እዳ ጥያቄ የሆነ ነን። የናንተስ የመኖር እዳ ምንድን ነው?? እዳ ካልሆነ ስጦታነቱን በምን አመናቹህ? ስጦታነቱ ምኑ ላይ ነው? ተሰቶ እሚነጠቅ ስጦታ መሆኑንስ እንዴት ታዩታላቹህ? ወደ ህይወት እየመጣቹህ ነው ወይስ ወደ ሞት እየሄዳቹህ??
.
.
.
ህዳር 28/2015 ዓ.ም

✍️Aman😑 YTZ
@amanYTZ23

join 👇👇👇
@YelbeDrset
@YelbeDrset

inbox me @amanYTZ23


@kinchebchabi @kinchebchabi
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ ተመልሷል። 🙏