ቅዱሳን ኅሩያን የዲ°ን ዮርዳኖስ ትምህርቶች
4.84K subscribers
721 photos
5 videos
13 files
232 links
የዲ.ን ሄኖክ ሀይሌን ስብከት በድምጽ እንለቃለን
ለአስተያየት @EMNE_TSYON @unitte_bot
በቴሌግራም ከፈለጉን @henokhailee
በfacebook ከፈለጉን https://www.facebook.com/tewahidosewhone/
በyoutube ከፈለጉን https://youtube.com/channel/UCq2ueVG6O3ZuKHJ485y7hfg
Download Telegram
#ሚያዝያ_3
#አንድ_አምላክ_በሆነ_በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ_ስም
ሚያዝያ ሦስት በዚች ቀን የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ የከበረ አባት #አባ_ዮሐንስ አረፈ፣ የከበረ አባት በእስክንድርያ ለተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አንደኛ የሆነ #አባ_ሚካኤል አረፈ፣ ክርስቲያናዊ ነጋዴ #ቅዱስ_መርቄ አረፈ፣ በተጨመሪም #እግዚአብሔር በእግር የሚራመዱ በክንፍ የሚበሩና በልብ የሚሳቡ በየብስ የሚኖሩ ፍጥረታትን ፈጠረ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ዮሐንስ

ሚያዝያ ሦስት በዚች ቀን የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ የከበረ አባት አባ ዮሐንስ አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ የኦሪት ምሁራን የሆኑ አዋቂዎች ነበሩ የኦሪትን ሕግ ትምህርቶችንም እያስተማሩት አሳደጉት።

ክርስቲያኖችን በጸና ልቡና የሚከራከራቸውና የሚጣላቸው ነበር መጻሕፍትን አዘውትሮ ከመመርመሩ የተነሣ የ ክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ወደ ዓለም እንደመጣና ሰውም እንደሆነ በሞቱም ዓለምን እንደ አዳነ አመነ። እርሱም የ#ባሕርይ_አምላክ እንደሆነ አምኖ በኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ በአባ ዮስጦስ እጅ ተጠመቀ ዲቁናም ሾመው ከዚያም በኢየሩሳሌም ሀገር ኤጲስቆጶስነት ለመሾም እስቲገባው ድረስ በበጎ ስራና በዕውቀት አደገ።

ኤልያስ የሚባለው እንድርያኖስም በነገሠ ጊዜ ከኢየሩሳሌም ሀገር የፈረሰውን ሕንፃ ሁሉ እንዲያንፁና በስሙ ኤልያስ ተብሎ እንዲጠራ አዘዘ። ከዚህም በአይሁድ ምኲራብ ደጃፍ ላይ ታላቅ ግምብ ሠሩ ከከበረ ድንጊያም ሠሌዳ ሠርቶ በላዩም ስሙን ኤልያስን ጽፎ በመግቢያው አኖረው በዘመኑም ኢየሩሳሌም አሕዛብንና አይሁድን ተመላች ሠለጡኑባትም።

ክርስቲያኖችም ሊጸልዩ ወደ ጎልጎታ ሲመጡ በአዩአቸው ጊዜ አሕዛብ ይከለክሉአቸው ነበር በዚያ ዝሁራ በሚባል ኮከብ ስም መስጊድ ሠርተው ነበርና። ስለዚህም #ክርስቲያኖችን በዚያ እንዳያልፉ ይከለክሏቸው ነበር።
በዚህም አባት ላይ ከአሕዛብ ታላቅ መከራና በምድር ላይም ጐትተውታልና አጐሳቁለውታልና እርሱም ነፍሱን ወደርሱ ይቀበል ዘንድ የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስን ለመነው ጌታም ልመናውን ሰምቶ በሰላም አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ሚካኤል_ዘእስክንድርያ

በዚህችም ቀን ደግሞ የከበረ አባት በእስክንድርያ ለተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አንደኛ የሆነ አባ ሚካኤል አረፈ። ይህ አባት ከታናሽነቱ ጀምሮ የምንኲስና ልብስ ሊለብስ ወደደ በአስቄጥስ ገዳም በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን መንኲሶ እስከ ሸመገለ ድረስ በዚያ ኖረ።

በብዙ መነኰሳትም ላይ አበ ምኔት ሆኖ ተሾመ በዘመኑ ሁለየ መልካም ተጋድሎ በመጋደል #እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው። በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስና ለመሾም እስቲገባው ድረስ ፍጹም ተጋድሎ በመጋደል ደከመ።

ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ገብርኤል በአረፈ ጊዜ የወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ያለ ሊቀ ጳጳሳት አራት ወር ኖረ ለዚች ሹመት የሚሻል ሲመረምሩና ሲመርጡ ብዙ ደከሙ። ከብዙ ድካምም በኃላ ሦስት የገዳም ሰዎችን መርጠው ስማቸውን በሦስት ክርታስ ጻፉ የክብር ባለቤት የ#ጌታችንን_ኢየሱስ_ክርስቶስንም ስም በአንዲት ክርታስ ጽፈው እየአንዳንዳቸውን አሽገው በመሠዊያው ውስጥ አኖሩአቸው። ቸር ጠባቂ ይሾምላቸው ዘንድ ኤጲስቆጶሳቱና ካህናቱ እስከ ሦስት ቀን እየጸለዩና እየቀደሱ #እግዚአብሔርን በመማለድ ኖሩ።

ከሦስት ቀኖችም በኃላ አንድ ታናሽ ብላቴና ጠርተው ከእነዚህ ከሦስቱ ስሞች አንዱን አንሥተህ ስጠን አሉት። ያም ብላቴና የዚህን አባት የአባ ሚካኤል ስም ያለበትን ያንን ክርታስ አወጣ። ሁሉም እግዚአብሔር እንደመረጠው አውቀው ይገባዋል ይግባዋል ይገባዋል እያሉ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እርሱም በሹመቱ ላይሆኖ እንደሚገባ በመልካም አመራር ሥራውን መራ።

የሚጽፍለትም ጸሐፊ መረጡለት ስለ ምእመናን አጠባበቅና ስለማስተማር ወደ ሀገሮች ሁሉና ወደ ኤጲስቆጶሳቱ መልእክትን ይልክ ነበር። እርሱም ከኃጢአታቸው ተመልሰው ንሰሐ እንዲገቡ ሕዝቡን ይመክራቸውና ይገሥጻቸው ነበር እግዚአብሔርን ይፈሩት ዘንድ።

ንጽሐ ነፍስ ንጽሐ ልቡና ያለው ሆነ የዚህን አለም ጣዕም ያለውን ምግብ አይሻም አይመኝም ክብሩንም ቢሆን ወይም ጥሪቱን ድኆችንና ችግረኞችን አስቦ ይመጸውታቸው ነበረ እንጂ፡፡ ከእነርሱ የሚተርፈውንም ለቤተ ክርስቲያን ማሠሪያ ያደረገው ነበር። ይህ አባት ሙሉ ዓመት አልኖረም ከዚያ የሚያንስ ነው እንጂ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_መርቄ_ጻድቅ

በዚህችም ቀን ዳግመኛ ክርስቲያናዊ ነጋዴ መርቄ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከአንጾኪያ ሰዎች ወገን ነው ጉዝፋርም ጣዖት የሚያመልክ ከሀዲ ነው ከሃይማኖት በቀር በምንም በምን አይለያዩም። ከዕለታትም በአንዲቱ መርቄና ጉዝፋር ነበግዱድ ወደሚባል አገር ለንግድ ሒደው ሰው በሌለበት በበረሀ ውስጥ አምስት ቀን ተጓዙ ክርስቲያናዊ መርቄም ባለጸጋ ነው ከእርሱ ጋርም አርባ ልጥረ ወርቅ ነበረ።

በጐዳና በጉዞ ላይም እያሉ ለሞት የሚያደርስ ደዌን መርቄ ታመመ ከዚያም ራሱን አጽናንቶ እንዲህ ብሎ ጻፈ። "ከባሪያህ ልጅ ከባሪያህ መርቄ ለእኔ ያለ በጥቁር በቅሎ የተጫነ አርባ ልጥረ ወርቅ ለአንተ ይሁን #ጌታ_ኢየሱስ_ክርስቶስ የሕያው #እግዚአብሄር_ልጅ የክብር ባለቤት ሆይ ስለ በደሌ ይቅር ብለኸኝ መንግሥተ ሰማያትን ትሰጠኝ ዘንድ ለልጆቼ ለሚስቴም ወይም ለዘመዶቼ አይሁን ብዬአለሁ።"

ይቺን ደብደቤ ጠቅልሎ ወዳጄ ጉዝፋርን ጠራው የሚለውን ሁሉ ያደርግለት ዘንድ አማለው። ከዚያም በምሞትበት ጊዜ አትንካኝ ግን ይህን አርባ ልጥረ ወርቅ እንደተጫነ ከበቅሎው ጋራ ወስደህ የክብር ባለቤት ለሆነ ለሕያው #እግዚአብሔር_ልጅ_ለጌታዬ_ኢየሱስ_ክርስቶስ በእጁ ስጠው። ለልጆቼ እንዳትሰጥ ከእርሱ በቀር ለማንም ቢሆን አትስጥ አለው።

ጉዝፋርም እንዲህ ብሎ መለሰለት አንተ ራስህ ሞቶ ተነስቶ ወደ ሰማይ ወጣ የምትል አይደለምን እኔ ወደ ሰማይ ወጥቼ ልሰጠው እችላለሁን። መርቄም እንዲህ አለው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒድ ራሱ ወደ አንተ ይመጣል እጅ በእጅ ስጠው።

ከዚህ በኃላ መርቄ ለመሞት ሲቃረብ ራቀወ ብሎ በመቀመጥ ጉዝፋር መሞቱን ይጠብቅ ነበር። ወደርሱም መላእክት የብርሃን ልብስ ይዘው ሲወርዱ አየ ከእርሳቸውም ጋራ ጻድቃን ሰማዕታት አሉ ዳዊትም በመስንቆ ያመሰግን ነበር መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በስጋው ላይ ሦስት ጊዜ ዞረ ያንጊዜም የመርቄ ነፍስ ከሥጋዋ ተለይታ ወደ ሰማይ እንዲህ ባለ ሁኔታ ዐረገች። ሁለት አንበሶችም መጡ ምድሩንም ቆፍረው ቀበሩት።

ጉዝፋርም ተነሣ የመርቄንም ወርቅ ጭኖ ስለአየው ሁሉ እያደነቀ ሔደ። አንጾኪያም በደረሰ ጊዜ የቤተ ክርስቲያኑን አስተዳዳሪ ቀሲስ ታዴዎስን አግኝቶ መርቄ እንዳለው ነገረው። ቀሲስ ታዴዎስም ሊረከበው ወደ ጉዝፋር ሔደ። ግን የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለማንም አልሰጥም ወዳጄ መርቄ እንዳማለኝ እጅ በእጅ እሰጠዋለሁ እንጂ ብሎ ከለከለው።

ከዚያም ሒዶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጽር ግቢ ገባ።ቀሲስ ታዴዎስም ደጁን ከፈተለት የተጫነውንም ወርቅ አውርዶ በፊቱ አኑሮ በዚያ ቆመ። ከሌሊቱ እኩሌታ ላይ እንደ ነጐድጓድ ድምፅ ያለ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሰማ። ታላቅ ብርሃንም ወጣ #ጌታችንም ከሰማይ ወርዶ በመሠዊያው ላይ ተቀመጠ መላእክትም ከእርሱ ጋር አሉ።