ቅዱሳን ኅሩያን የዲ°ን ዮርዳኖስ ትምህርቶች
4.78K subscribers
773 photos
5 videos
17 files
239 links
የዲ.ን ሄኖክ ሀይሌን ስብከት በድምጽ እንለቃለን
ለአስተያየት @EMNE_TSYON @unitte_bot
በቴሌግራም ከፈለጉን @henokhailee
በfacebook ከፈለጉን https://www.facebook.com/tewahidosewhone/
በyoutube ከፈለጉን https://youtube.com/channel/UCq2ueVG6O3ZuKHJ485y7hfg
Download Telegram
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ ታኅሳስ24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞✞✞

✞✞✞ እንኩዋን ለቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት: ቅዱስ አግናጥዮስ እና ቅድስት አስቴር ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ  ✞✞✞

+*" ቅዱስ  #‎ተክለ_ሃይማኖት  ሐዋርያዊ "*+

*ልደት*

=>መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ:  #‎ጸጋ_ዘአብ  ካህኑና  #‎እግዚእ_ኃረያ  ናቸው:: እርሱ በክህነቱ: እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል::

+በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው  #‎ቅዱስ_ሚካኤል : ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል:: በኋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል::

+አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24, በ1206 (1196) ሲሆን የተወለዱት ታሕሳስ 24, በ1207 (1197) ዓ/ም ነው:: በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል::

*ዕድገት*

=>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው " #‎ፍሥሃ_ጽዮን " ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ  #‎አባ_ጌርሎስ  ተቀብለዋል::

*መጠራት*

=>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት  #‎ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ  አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::

+የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ:

"ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በኋላሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ::

*አገልግሎት*

=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ ( #‎ጽላልሽ ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ:: ያንጊዜ  #‎ኢትዮዽያ  2 መልክ ነበራት::

1.ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል::

2.ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር::

+ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት  #‎ሐዲስ_ሐዋርያ  አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል::

*ገዳማዊ ሕይወት*

=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::

+እነዚህም በአቡነ  #‎በጸሎተ_ሚካኤል  ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ  #‎ኢየሱስ_ሞዐ_ዘሐይቅ  ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ  #‎ዮሐኒ  ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል::

+በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በኋላም ወደ ምድረ ሽዋ  #‎ዞረሬ  ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል::

*ስድስት ክንፍ*

=>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ  #‎እሥራኤል  የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::

+የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት  #‎አባ_ሚካኤል  ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በኋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር::

+ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
¤በቤተ መቅደስ ብስራቱን
¤በቤተ ልሔም ልደቱን
¤በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
¤በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
¤በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር::

+የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደሆነው  #‎ቀራንዮ  ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ::
በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ  #‎እመቤታችን_ድንግል_ማርያም  ፈጥና ደርሳ ጻድቁን ወደሰማይ አሳረገቻቸው::

+በዚያም:-
¤የብርሃን ዐይን ተቀብለው
¤6 ክንፍ አብቅለው
¤የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
¤ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
¤ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
¤ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
¤"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል::

*ተአምራት*

=>የጻድቁ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል
*ድውያንን ፈውሰዋል
*አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል
*በክንፍ በረዋል
*ደመናን ዙፋን አድርገዋል::

+ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና::

*ዕረፍት*

=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24, በ1306 (1296) ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::

=>የጻድቁ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የቅድስናና የክብር ስሞች :-

1.ተክለ አብ: ተክለ ወልድ: ተክለ መንፈስ ቅዱስ
2.ፍስሐ ፅዮን
3.ሐዲስ ሐዋርያ
4.መምሕረ ትሩፋት
5.ካህነ ሠማይ
6.ምድራዊ መልዐክ
7.እለ ስድስቱ ክነፊሁ (ባለስድስት ክንፍ)
8.ጻድቅ ገዳማዊ
9.ትሩፈ ምግባር
10.ሰማዕት
11.የኢትዮዽያ መነኮሳት አለቃ
12.ፀሐይ ዘበፀጋ
13.የኢትዮዽያ ብርሃኑዋ
14.ብእሴ እግዚአብሔር (የእግዚአብሔር ሰው)
15.መናኒ
16.ኤዺስ ቆዾስ (እጨጌ)

=>እነዚህ የአባታችን ስሞች እንደዘመኑ ሰው ለመሞጋገስ የወጡ ሳይሆኑ ሁሉም በትክክል ሥራዎቹንና ለቤተ ክርስቲያን የሆነላትን የሚያዘክሩ ናቸው:

+" ቅዱስ አግናጥዮስ "+

=>ይህ ቅዱስ ሰው ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የጠገበ በመሆኑ በመላው ዓለም ዝነኛ ነው:: እርሱ:-
*በክርስቶስ እጅ ተባርኩዋል
*ፈጣሪውን ፊት ለፊት አይቷል
*ሐዋርያትን አገልግሏል
*ከምሥጢር አባት ከዮሐንስ ወንጌላዊ እግር ተምሯል
*ስለ ክርስትና ለአንበሶች ተጥሎ በመገደሉ "ምጥው ለአንበሳ" ይባላል::
#ሚያዝያ_3
#አንድ_አምላክ_በሆነ_በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ_ስም
ሚያዝያ ሦስት በዚች ቀን የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ የከበረ አባት #አባ_ዮሐንስ አረፈ፣ የከበረ አባት በእስክንድርያ ለተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አንደኛ የሆነ #አባ_ሚካኤል አረፈ፣ ክርስቲያናዊ ነጋዴ #ቅዱስ_መርቄ አረፈ፣ በተጨመሪም #እግዚአብሔር በእግር የሚራመዱ በክንፍ የሚበሩና በልብ የሚሳቡ በየብስ የሚኖሩ ፍጥረታትን ፈጠረ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ዮሐንስ

ሚያዝያ ሦስት በዚች ቀን የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ የከበረ አባት አባ ዮሐንስ አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ የኦሪት ምሁራን የሆኑ አዋቂዎች ነበሩ የኦሪትን ሕግ ትምህርቶችንም እያስተማሩት አሳደጉት።

ክርስቲያኖችን በጸና ልቡና የሚከራከራቸውና የሚጣላቸው ነበር መጻሕፍትን አዘውትሮ ከመመርመሩ የተነሣ የ ክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ወደ ዓለም እንደመጣና ሰውም እንደሆነ በሞቱም ዓለምን እንደ አዳነ አመነ። እርሱም የ#ባሕርይ_አምላክ እንደሆነ አምኖ በኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ በአባ ዮስጦስ እጅ ተጠመቀ ዲቁናም ሾመው ከዚያም በኢየሩሳሌም ሀገር ኤጲስቆጶስነት ለመሾም እስቲገባው ድረስ በበጎ ስራና በዕውቀት አደገ።

ኤልያስ የሚባለው እንድርያኖስም በነገሠ ጊዜ ከኢየሩሳሌም ሀገር የፈረሰውን ሕንፃ ሁሉ እንዲያንፁና በስሙ ኤልያስ ተብሎ እንዲጠራ አዘዘ። ከዚህም በአይሁድ ምኲራብ ደጃፍ ላይ ታላቅ ግምብ ሠሩ ከከበረ ድንጊያም ሠሌዳ ሠርቶ በላዩም ስሙን ኤልያስን ጽፎ በመግቢያው አኖረው በዘመኑም ኢየሩሳሌም አሕዛብንና አይሁድን ተመላች ሠለጡኑባትም።

ክርስቲያኖችም ሊጸልዩ ወደ ጎልጎታ ሲመጡ በአዩአቸው ጊዜ አሕዛብ ይከለክሉአቸው ነበር በዚያ ዝሁራ በሚባል ኮከብ ስም መስጊድ ሠርተው ነበርና። ስለዚህም #ክርስቲያኖችን በዚያ እንዳያልፉ ይከለክሏቸው ነበር።
በዚህም አባት ላይ ከአሕዛብ ታላቅ መከራና በምድር ላይም ጐትተውታልና አጐሳቁለውታልና እርሱም ነፍሱን ወደርሱ ይቀበል ዘንድ የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስን ለመነው ጌታም ልመናውን ሰምቶ በሰላም አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ሚካኤል_ዘእስክንድርያ

በዚህችም ቀን ደግሞ የከበረ አባት በእስክንድርያ ለተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አንደኛ የሆነ አባ ሚካኤል አረፈ። ይህ አባት ከታናሽነቱ ጀምሮ የምንኲስና ልብስ ሊለብስ ወደደ በአስቄጥስ ገዳም በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን መንኲሶ እስከ ሸመገለ ድረስ በዚያ ኖረ።

በብዙ መነኰሳትም ላይ አበ ምኔት ሆኖ ተሾመ በዘመኑ ሁለየ መልካም ተጋድሎ በመጋደል #እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው። በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስና ለመሾም እስቲገባው ድረስ ፍጹም ተጋድሎ በመጋደል ደከመ።

ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ገብርኤል በአረፈ ጊዜ የወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ያለ ሊቀ ጳጳሳት አራት ወር ኖረ ለዚች ሹመት የሚሻል ሲመረምሩና ሲመርጡ ብዙ ደከሙ። ከብዙ ድካምም በኃላ ሦስት የገዳም ሰዎችን መርጠው ስማቸውን በሦስት ክርታስ ጻፉ የክብር ባለቤት የ#ጌታችንን_ኢየሱስ_ክርስቶስንም ስም በአንዲት ክርታስ ጽፈው እየአንዳንዳቸውን አሽገው በመሠዊያው ውስጥ አኖሩአቸው። ቸር ጠባቂ ይሾምላቸው ዘንድ ኤጲስቆጶሳቱና ካህናቱ እስከ ሦስት ቀን እየጸለዩና እየቀደሱ #እግዚአብሔርን በመማለድ ኖሩ።

ከሦስት ቀኖችም በኃላ አንድ ታናሽ ብላቴና ጠርተው ከእነዚህ ከሦስቱ ስሞች አንዱን አንሥተህ ስጠን አሉት። ያም ብላቴና የዚህን አባት የአባ ሚካኤል ስም ያለበትን ያንን ክርታስ አወጣ። ሁሉም እግዚአብሔር እንደመረጠው አውቀው ይገባዋል ይግባዋል ይገባዋል እያሉ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እርሱም በሹመቱ ላይሆኖ እንደሚገባ በመልካም አመራር ሥራውን መራ።

የሚጽፍለትም ጸሐፊ መረጡለት ስለ ምእመናን አጠባበቅና ስለማስተማር ወደ ሀገሮች ሁሉና ወደ ኤጲስቆጶሳቱ መልእክትን ይልክ ነበር። እርሱም ከኃጢአታቸው ተመልሰው ንሰሐ እንዲገቡ ሕዝቡን ይመክራቸውና ይገሥጻቸው ነበር እግዚአብሔርን ይፈሩት ዘንድ።

ንጽሐ ነፍስ ንጽሐ ልቡና ያለው ሆነ የዚህን አለም ጣዕም ያለውን ምግብ አይሻም አይመኝም ክብሩንም ቢሆን ወይም ጥሪቱን ድኆችንና ችግረኞችን አስቦ ይመጸውታቸው ነበረ እንጂ፡፡ ከእነርሱ የሚተርፈውንም ለቤተ ክርስቲያን ማሠሪያ ያደረገው ነበር። ይህ አባት ሙሉ ዓመት አልኖረም ከዚያ የሚያንስ ነው እንጂ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_መርቄ_ጻድቅ

በዚህችም ቀን ዳግመኛ ክርስቲያናዊ ነጋዴ መርቄ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከአንጾኪያ ሰዎች ወገን ነው ጉዝፋርም ጣዖት የሚያመልክ ከሀዲ ነው ከሃይማኖት በቀር በምንም በምን አይለያዩም። ከዕለታትም በአንዲቱ መርቄና ጉዝፋር ነበግዱድ ወደሚባል አገር ለንግድ ሒደው ሰው በሌለበት በበረሀ ውስጥ አምስት ቀን ተጓዙ ክርስቲያናዊ መርቄም ባለጸጋ ነው ከእርሱ ጋርም አርባ ልጥረ ወርቅ ነበረ።

በጐዳና በጉዞ ላይም እያሉ ለሞት የሚያደርስ ደዌን መርቄ ታመመ ከዚያም ራሱን አጽናንቶ እንዲህ ብሎ ጻፈ። "ከባሪያህ ልጅ ከባሪያህ መርቄ ለእኔ ያለ በጥቁር በቅሎ የተጫነ አርባ ልጥረ ወርቅ ለአንተ ይሁን #ጌታ_ኢየሱስ_ክርስቶስ የሕያው #እግዚአብሄር_ልጅ የክብር ባለቤት ሆይ ስለ በደሌ ይቅር ብለኸኝ መንግሥተ ሰማያትን ትሰጠኝ ዘንድ ለልጆቼ ለሚስቴም ወይም ለዘመዶቼ አይሁን ብዬአለሁ።"

ይቺን ደብደቤ ጠቅልሎ ወዳጄ ጉዝፋርን ጠራው የሚለውን ሁሉ ያደርግለት ዘንድ አማለው። ከዚያም በምሞትበት ጊዜ አትንካኝ ግን ይህን አርባ ልጥረ ወርቅ እንደተጫነ ከበቅሎው ጋራ ወስደህ የክብር ባለቤት ለሆነ ለሕያው #እግዚአብሔር_ልጅ_ለጌታዬ_ኢየሱስ_ክርስቶስ በእጁ ስጠው። ለልጆቼ እንዳትሰጥ ከእርሱ በቀር ለማንም ቢሆን አትስጥ አለው።

ጉዝፋርም እንዲህ ብሎ መለሰለት አንተ ራስህ ሞቶ ተነስቶ ወደ ሰማይ ወጣ የምትል አይደለምን እኔ ወደ ሰማይ ወጥቼ ልሰጠው እችላለሁን። መርቄም እንዲህ አለው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒድ ራሱ ወደ አንተ ይመጣል እጅ በእጅ ስጠው።

ከዚህ በኃላ መርቄ ለመሞት ሲቃረብ ራቀወ ብሎ በመቀመጥ ጉዝፋር መሞቱን ይጠብቅ ነበር። ወደርሱም መላእክት የብርሃን ልብስ ይዘው ሲወርዱ አየ ከእርሳቸውም ጋራ ጻድቃን ሰማዕታት አሉ ዳዊትም በመስንቆ ያመሰግን ነበር መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በስጋው ላይ ሦስት ጊዜ ዞረ ያንጊዜም የመርቄ ነፍስ ከሥጋዋ ተለይታ ወደ ሰማይ እንዲህ ባለ ሁኔታ ዐረገች። ሁለት አንበሶችም መጡ ምድሩንም ቆፍረው ቀበሩት።

ጉዝፋርም ተነሣ የመርቄንም ወርቅ ጭኖ ስለአየው ሁሉ እያደነቀ ሔደ። አንጾኪያም በደረሰ ጊዜ የቤተ ክርስቲያኑን አስተዳዳሪ ቀሲስ ታዴዎስን አግኝቶ መርቄ እንዳለው ነገረው። ቀሲስ ታዴዎስም ሊረከበው ወደ ጉዝፋር ሔደ። ግን የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለማንም አልሰጥም ወዳጄ መርቄ እንዳማለኝ እጅ በእጅ እሰጠዋለሁ እንጂ ብሎ ከለከለው።

ከዚያም ሒዶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጽር ግቢ ገባ።ቀሲስ ታዴዎስም ደጁን ከፈተለት የተጫነውንም ወርቅ አውርዶ በፊቱ አኑሮ በዚያ ቆመ። ከሌሊቱ እኩሌታ ላይ እንደ ነጐድጓድ ድምፅ ያለ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሰማ። ታላቅ ብርሃንም ወጣ #ጌታችንም ከሰማይ ወርዶ በመሠዊያው ላይ ተቀመጠ መላእክትም ከእርሱ ጋር አሉ።