ቅዱሳን ኅሩያን የዲ°ን ዮርዳኖስ ትምህርቶች
5.85K subscribers
1.06K photos
7 videos
37 files
247 links
የዲ.ን ዮርዳኖስ አበበ ስብከት በድምጽ እንለቃለን
ለአስተያየት @EMNE_TSYON @unitte_bot
በቴሌግራም ከፈለጉን @henokhailee
በfacebook ከፈለጉን https://www.facebook.com/tewahidosewhone/
በyoutube ከፈለጉን https://youtube.com/channel/UCq2ueVG6O3ZuKHJ485y7hfg
Download Telegram
#ሚያዝያ_2
#አንድ_አምላክ_በሆነ_በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ_ስም
ሚያዝያ ሁለት በዚህችም ቀን የቃይናን ልጅ #የቅዱስ_መላልኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፣ ፊቱ እንደ ውሻ የሆነ #ቅዱስ_ክርስትፎሮስ በሰማዕትነት አረፈ፣ የሐሊባ ሃገር ሰው የከበረ አባት #ስምዖን ዕረፍቱ እነረደሆነ ስንክሳር በስም ይጠቅሰዋል።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_መላልኤል

ሚያዝያ ሁለት በዚህችም ቀን የቃይናን ልጅ የመላልኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፡፡ መላልኤልም መቶ ስልሳ አምስት ዓመት ኖረ ያሬድንም ወለደው።

መላልኤልም ያሬድን ከወለደው በኃላ ሰባት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ። የመላልኤልም መላ ዘመኑ ሁሉ ስምንት መቶ ዘጠና አምስት ዓመት ነው። ቅዱስ መላልኤልም ሚያዝያ ሁለት ቀን በእሑድ ዕለት ሞተ በማከማቻም ውስጥ ቀበሩት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ክርስቶፎሮስ (ሐዋርያና ሰማዕት)

በዚችም ቀን ፊቱ እንደ ውሻ የሆነ ቅዱስ ክርስትፎሮስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ ሰውን ይበሉ ከነበሩ ሰዎች ሀገር ነው በጦርነትም ማረኩት አባቱም በሐዋርያ ማትያስ እጅ ያመነ ነው። በማረኩትም ጊዜ ቋንቋቸውን አያውቅም ነበር የክብር ባለቤት ወደሆነ እግዚአብሔርም ማለደ ቋንቋቸውንም ገልጦለት እንደርሳቸው ተነሰገረ የክርስቲያን ወገኖችን የሚያሠቃዩአቸውንም ገሠጻቸው የጦር ሠራዊቱንም የሚመራ መኰንን ጽንዕ ግርፋትን ገረፈው። ቅዱስ ክርትፎሮስም መኰንኑን የጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዙ ኃይሌን ባትይዘኝና ባታስታግሠኝ አንተና ሠራዊትህ ከእኔ እጅ ባልዳናችሁ ነበር አለው።

መኰንኑም ስለ ርሱ ወደ ንጉሥ ላከ ከእርሱ የሆነውንም ነገረው። ንጉሡም ወደ ርሱ እንዲያመጡት ሁለት መቶ ወታደሮችን ላከለት እርሱም ያለ መፍራት ያለ ማፈግፈግ አብሮአቸው ሔደ። በእጁ በትር ነበረች በላይዋ በጸለየ ጊዜ በቀለችና አበበች። እነዚያ ወታደሮች ተርበው የሚበሉት እንጀራ በአጡ ጊዜ ቅዱስ ክርስትፎሮስ ጸለየ በእነርሱ ዘንድ እንጀራ በዝቶ ተትረፈረፈ እጅግም አድንቀው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። አባ ጳውሎስ እጅ የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቁ።

ወደ ንጉሡም ፊት በደረሱ ጊዜ ንጉስ ዳኬዎስ ሊያስፈራውና ሊሸነግለው ጀመረ ደግሞ እጅግ መልከ መልካም የሆኑ ሁለት አመንዝራ ሴቶችን ወደርሱ ሰደደ እነርሳቸው እንደሚያስቱትና በኀጢአት እንደሚጥሉት አስቧልና። እርሱ ግን ገሠጻቸው አስተማራቸውም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በደማቸው ምስክር ሁኑ። እንዲሁም እነዚያ ሁለት መቶ ወታደሮች በንጉሡ ፊት በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ራሶቻቸውንም በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነትንም በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ።

ቅዱስ ክርስትፎሮስም ንጉሡን አንተ የሰይጣንን ሥራ የምትቀበል ማደሪያው የሆንክ ብሎ ዘለፈው ንጉሡም ተቆጥቶ በትልቅ ብረት ምጣድ ውስጥ እንዲጨምሩትና ከበታቹ እሳትን እንዲያነዱ አዘዘ። እንዲሁም አደረጉበት ነገር ግን ከጉዳት እንዳሰቡት ምንም የደረሰበት የለም። ጤነኛ ሆኖ ሰዎችን አስተማራቸው እንጂ።እጅግም አድንቀው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ቅድሱንም ከእርሷ ሊአወጡት ወደዚያች ብረት ምጣድ ቀረቡ ንጉሡም አንገቶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧቸው አዘዘ የሕይወት አክሊልንም ተቀበሉ። ከዚያም በኃላ ታላቅ ደንጊያ በአንገቱ አንጠልጥለው ከጥልቅ ጉደረጓድ እንዲጨምሩት ንጉሡ አዘዘ በጨመሩትም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በጤንነት አወጣው። ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ አንገቱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ ንጉሡ አዘዘ። ቅዱሱም በእግዚአብሔር መንግስት የድል አድራጊነትን አክሊል ተቀዳጀ፡፡

ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡

#ሚያዝያ_1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1, ቅዱስ ክርስቶፎሮስ (ሐዋርያና ሰማዕት)
2, አባ ስምዖን ዘሃገረ ሐሊባ
3, ቅዱስ መላልኤል (የያሬድ አባት - ከአዳም ፭ኛ ትውልድ)
4, እግዚአብሔር ፀሐይን፣ ጨረቃን፣ ከዋክብትን ፈጠረ

#ወርኃዊ_በዓላት
1, ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
2, ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ
3, ቅዱስ ኢዮብ ጻድቅ ተአጋሲ
4, ቅዱስ አቤል ጻድቅ
5, ቅዱስ አባ ጳውሊ ገዳማዊ (ታላቁ)
6, ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
7, አባ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ

ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ። ልባሞች እንደ መሆናችሁ እላለሁ፤ በምለው ነገር እናንተ ፍረዱ። የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? አንድ እንጀራ ስለ ሆነ፥ እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ ነን፤ ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና። 1ኛ ቆሮንቶስ 10÷14—18

ወስብሐት ለእግዚአብሔር✝️
ከመላእክትም አንዱ ከሀዲ ጉዝፋር ከዚህ ለምን ቆምክ አለው። እርሱም ወዳጁ መርቀፀ ለክብር ባለቤት #ለጌታ_ኢየሱስ_ክርስቶስ እንጂ ለሌላ እንዳይሰጥ ብሎ እንዳማለው ነገረው። መልአኩም የክብር ባለቤት የሕያው #እግዚአብሔር_ልጅ_ጌታ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ይህ ነውና ና ስገድ አለው።

ጉዝፋርም ሰገደ ደብዳቤውንም ሰጠው።እየተንቀጠቀጠም የክብር ባለቤት #ጌታዬ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ሆይ አመንኩብህ አለ። ጌታም ያንን ወርቅ ይመዝኑ ት ዘንድ አዘዘ። አርባ ልጥርም ሆነ ጉዝፋርንም ከቀሲስ ታዴዎስ ዘንድ እንዲጠመቅ አዘዘው። ከቤተሰቡ ሁሉ ጋር ተጠመቀ የተጠመቁትም ሰባ አምስት ነፍስ ሆኑ።

ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡

#የዕለተ_ሐሙስ_ፍጥረታት

#ሐሙስ፡- የሚለው የዕለቱ ስም ሀምሰ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ነው #አምስተኛ ማለት ነው፡፡ አምስተኛነቱም እግዚአብሔር ፍጥረታትን መፍጠር ከጀመረበት ከዕለተ እሑድ ጀምሮ ያለው ቀን ማለት ነው፡፡

  #የሐሙስ_ፍጥረታት
እግዚአብሔር ሐሙስ በቀዳማይ ሰዓት ለሊት “#ውሃ_ሕያው_ነፍስ_ያላቸው_ተንቀሳቃሾች_ታስገኝ” ብሎ በማዘዝ ሦስት አይነት ፍጥረታትን ፈጠረ፡፡ ዘፍ 1፡20 በዕለተ ሐሙስ የተፈጠሩት ሦስት ፍጥረታት ዘመደ እንስሳት የሚባሉት አሣዎች፣ ዘመደ አራዊት የተባሉት ኣዞ፣ጉማሬ፣ አሳነባሪ፣ ዘመደ አዕዋፍ የሚባሉት ደግሞ ዳክዬዎች ናቸው፡፡ 
#በዕለተ_ሐሙስ_የተፈጠሩት_ፍጥረታት_ተፈጥሮአቸው_ከአራቱ_ባሕሪያተ_ስጋ /መሬት፣ ውሃ ፣ነፋስና፣ እሳት/ ነው፡፡ አካላቸው ሥጋና ደም፣ አፅምና ጅማት ሲሆን በደም ነፍስ ይንቀሳቀሳሉ የደመ ነፍስ እውቀት አላቸው ደመነፍስ ማለትም በደም ነፍስነት፣ ኃይልነት የሚንቀሳቀሱ፣ የደም ነፍስ ያላቸው፣ ደማቸው ሲቆም እንቅስቃሴያቸውም የሚቆም ማለት ነው፡፡
   #የሐሙስ_ፍጥረታት_በአካሄዳቸው_በአኗኗራቸው_አንፃር_በሦስት_ይከፈላሉ በአካሄዳቸው በልብ የሚሳቡ፣ በእግር የሚሽከረከሩ፣ /የሚሄዱ/፣ በክንፍ የሚበሩ ይባላሉ፡፡

#በአኗኗራቸውም አንጻር በባህር ውስጥ ተፈጥረው በረው ወደ የብስ፣ ወደ ደረቁ መሬት የወጡ፣ በዚያው በተፈጠሩበት በባህር ውስጥ የቀሩ፣ ወጣ ገባ እያሉ ማለት ከባህር ወደ የብስ፣ ከየብስ ወደ ባሕር ወጣ ገባ እያሉ የሚኖሩ ይባላሉ፡፡ ከእነዚህም ፍጥረታት የሚበሉና የማይበሉ ለሰው የሚገዙና፣ የማይገዙም አሉ፡፡
    
#የሐሙስ_ፍጥረታት_ምሳሌነት

#በባሕር_ውስጥ_የሚኖሩት_ምሌሳነታቸው፡-

በእግዚአብሔር አምነው በስሙ ተጠምቀው በዚያው ፀንተው የሚኖሩ ሰዎች፤
በሕገ እግዚአብሔር ፀንተው በትዳር ተወስነው በሀብት በንብረታቸው መልካም ስራ እየሠሩ ዓሥራት አውጥተው፣ በዓላትን አክብረው የሚኖሩ የሕጋውያ ሰዎች፤
ግብራችንን አንተውም ብለው ሲሰርቁ ሲቀሙ፤ ሲምሉና ሲገዘቱ የሚኖሩ የኃጥአን ምሳሌ ናቸው፡፡

#ወጣ_ገባ_እያሉ_የሚኖሩት_ምሳሌነታቸው
  አንድ ጊዜ ወደ ዓለም አንድ ጊዜ ወደ ገዳም ሲመላለሱ የሚኖሩ መነኮሳት፣
አንድ ጊዜ ወደ ሀይማኖት አንድ ጊዜ ወደ ክህደት የሚወላውሉ ሰዎች፤
#በባሕር_ተፈጥረው_በረው_ወደ_የብስ_የሄዱት
ከዘመድ አዝማድ ተለይተው ርቀው ከበረሃ ወድቀው ደምፀ አራዊቱን ፀብአ አጋንንቱን ግርማ ለሊቱን ታግሰው የሚኖሩ የመናንያን ምሳሌ ናቸው፡፡
አንድም በባህር ተፈጥረው በረው ወደ የብስ የሚኖሩት የከሀዲዎች ምሳሌ ነው በሀይማኖት ኖረው በኋላ ይክዳሉና
           
#አካሄዳቸውም 
#በልብ_የሚሳቡ፡- የመንግስት ምሳሌ ናቸው እነዚህ በልብ (በደረት) ተስበው ስራቸውን ፈቃዳቸውን እንዲፈፅሙ መንግስትም በልቡ ያሰበውን ይሠራል ይፈፅማል፡፡
#በእግር_የሚሽከረከሩ
“ያላችሁን ትታችሁ ተከተሉኝ” ባለው አምላካዊ ቃል መሠረት ሁሉን ትተው ከሴት ከወንድ እርቀው ድንግልናቸውን ጠብቀው ከትሩፋት ወደ ትሩፋት እየተሸጋገሩ የሚኖሩ የመናንያን ምሳሌ፡፡

#በክንፋቸው_የሚበሩት፡- ሥጋችሁን እንጂ ነፍሳችሁን ለመግደል የማይችሉትን አትፍሩ ባለው አምላካዊ ቃል ተመርተው ሳይፈሩ ዓላውያን ነገስታት ካሉበት ገብተው ሃይማኖታቸውን በመመስከር ሰማዕታትነታቸውን የሚፈፅሙ ሰማዕታት ምሳሌ ናቸው፡፡
  #ሰው_የሚባላቸውና_ለሰው_የሚገዙት፡- ለእግዚአብሔርና ለሰው በፍቅር በትሕትና የሚገዙ፣ የእግዚአብሔርን ፍቃድ የሚፈፅሙ የፃድቃን ምሳሌ ናቸው፡፡
#ሰው_የማይበላቸው_ለሰው_የማይገዙት ለእግዚአብሔርም ለሰውም የማይገዙ፣ አንገዛም አንታዘዝም ብለው በትዕቢት በዓመፅ የሚኖሩ የሃጣን ምሳሌ ናቸው፡፡
እግዚአብሔር ከአንድ ባሕር ሦስት ወገን የሆኑ ፍጥረታትን ፈጠረ፡፡ ከአንድ ማየገቦ ሦስት ትውልድ፡- ትውለደ ሴም፣ ትውልደ ያፌት፣ ትውልደ ካም ይጠመቁ ዘንድ መሰጠቱን  ያሳያል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ልጅነት በአብ‹ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቀው ለመሰጠቷም ምሳሌ ነው፡፡
  በዕለተ ሐሙስና በዕለተ ዓርብ የተፈጠሩት ፍጥረታት “እንስሳት” በመባል አንድ ቢሆኑም በአኗኗራቸውና በግብራቸው ይለያያሉ፡፡ የሐሙስ ፍጥረታት ከባሕር ተለይው በየብስ /በምድር/ መኖር አይችሉም የፀሐይ ሙቀት ሲነካቸው ይሞታሉ፡፡
  የግብር ፍጥረታትም ከምድር ተለይተው በባህር ውስጥ መኖር አይችሉም የባህር ውርጭ ቅዝቃዜ ይገድላቸዋልና፡፡

#ሚያዝያ_1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩, ቅዱስ መርቄ ጻድቅ (ክርስቲያናዊ ነጋዴ)
፪, ቅዱስ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም
፫, አባ ሚካኤል ዘእስክንድርያ
፬, #እግዚአብሔር በእግር የሚራመዱ በክንፍ የሚበሩና በልብ የሚሳቡ በየብስ የሚኖሩ ፍጥረታትን ፈጠረ

#ወርኃዊ_በዓላት
፩, በዓታ ለእግዝእትነ #ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
፪, ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
፫, ቅዱሳን ሊቀ ካህናት አበው (ዘካርያስና ስምዖን)
፬, አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
፭, አቡነ ዜና ማርቆስ
፮, አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል

እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም። መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል። መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።(ማቴ. ፭÷፲፬-፲፮)

        ✝️ወስብሐት ለ#እግዚአብሔር✝️
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ያሬድ ከአኵሱም ወደ ማይኪራህ አምርቶ እመቤታችን ቅዱስ ኤፍሬምን በአካለ ነፍስ ከሶርያ አባ ሕርያቆስ ከብሕንሳ አምጥታ ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን ንባቡን እየነገሩት በዜማ እንዲደርስላት አድርጋለች። ከዚህም አያይዞ ለሥጋ ወደሙ ጸሎት የሚያገለግሉትን ንባቡ የሌሎች ሊቃውንት ድርሰት የሆኑትን ዐሥራ አራቱን ቅዳሴዎች በዜማ አዘጋጀ።

ከዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ ሰሜን ተራሮች ጸለምት ሔዶ ምዕራፍ የተባለውን ድርሰቱን ደረሰ። ከዚህ በኋላ አገው፣ ፎገራ እና ወደ ሌሎችም ቦታዎች እየዞረ አስተማረ።

ቅዱስ ያሬድ በቅድስት አኵሰም ወንበር ዘርግቶ፣ ጉባኤ አስፍቶ ደቀ መዛሙርቱን እያስተማረ ሲኖር በጾመ፵ ሱባኤ ላይ ሳለ አንድ ቀን በምኵራብ ሰሞን ስለምናኔው እያስታወሰ በተመስጦ ሲዘምር የዜማው ጣዕም እንኳን ሌላውን ራሱን እጅግ ይመሥጠው ነበር። በጣዕመ ዝማሬው ተመሥጦ ሲያዳምጥ የነበረው ኢትዮጵያዊው ንጉሥ የዐፄ ገብረ መስቀል ዐይን ዐይኑን እየተመለከተ ሳይታወቀው በመስቀል ስላጢኑ (በበትረ መንግሥቱ ዘንግ) ጫፍ የቅዱስ ያሬድን እግር ወጋው። ቅዱስ ያሬድ ግንቀጠለ፤ ከሰማያት የተገኘች ቃለ ማሕሌቱን እስኪፈጽም ድረስ ከቆመበት ሳይንቀሳቀስ ሕመሙ ሳይታወቀው ደሙም ያለማቋረጥ ፈሰሰ።

ቅዱስ ያሬድ የጀመረውን በፈጸመ ጊዜ ንጉሡ ደንግጦ በትሩን ከቅዱስ ያሬድ እግያሬድን ቢነቅለው ደሙ በኃይል ይፈስ ጀመር። ያን ጊዜ ንጉሡ ዐፄ ገብረ መስቀል የቅዱስ ያሬድን ትዕግሥት ባለ ጊዜ በመደነቅ፣ በመገረምና በመደንገጥ ዝም በማለት አፉን ይዞ ቆመና ምድራዊ ዋጋ የሚፈልግ መስሎት "ካህን ያሬድ ሆይ የምትፈልገውን ዋጋ ጠይቀኝ" አለው። ቅዱስ ያሬድ መልሶ "የፈለግኹትን እንዳትከለክለኝ ቃል ኪዳን ግባልኝ" አለው። ንጉሡም የጸና ቃል ኪዳን ለቅዱስ ያሬድ ገባለት። ቅዱስ ያሬድም " ከዚህ ሐላፊ ዓለም ክብር ተለይቼ መናኝ ሆኜ እንድኖር ተወኝ ያሬድ አሰናብተኝ" ብሎ አሳብን ገለጸለት። ከዚህም በኋላ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል ካህን የጠየቀውን እንዳይከለክለው ከአፉ የወጣውን መሐላ አስቦ በምናኔ አሰናበተው እንጂ ሊከለክለው አልቻለም።

ቅዱስ ያሬድ ካህንም የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ታቦት ወዳለችበት ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ሁለት እጆቹን በታቦተ ጽዮን ላይ አኑሮ "ቅድስት ወብፅዕት፣ ስብሕት ወቡርክት፣ክብር ወልዕልት አንቀጸ ብርሃን መዓርገ ሕይወት" ብሎ በደረሰው አንቀጸ ብርሃን ጸሎት እመቤታችንን አመሰገነ። በዚህ ጊዜ እጁ በታቦተ ጽዮን ላይ ረቦ በመንፈስ ቅዱስ እየተቃኘ ስለነበር ከመሬት አንድ ክንድ ከፍ ከፍ ብሎ ይታይ ነበር። እስከመጨረሻው በከፍተኛ ቃል በዕዝል ዜማ እየዘመረ እግዚአብሔር እና እመቤታችንን ከአመሰገነ በኋላ እመቤታችን በጸሎት መንገድ እንድትመራውና እስከ ፍጻሜ ገድሉ ትረዳው ዘንድ በጸሎት ለመናት። እመቤታችንም መልሳ "ሰማያዊት ጽዮን ያደረግኻት መቅደሴን፣ በመዝሙር በማሕሌት ምስጋና የኪሩቤልና የሱራፌል ወገን ሰማያውያን ያደረግኻቸው ልጆቼ ካህናትን እንዴትድረስ ትተህ ትሔዳለህ" ብላ ቃል በቃል አነጋገረችው። የመንገዱን ስንብት እስክትፈቅድለት በለቅሶና በእንባ ዳግመኛ ለመናት እርሷም እንዲሔድ ፈቀደችለት።

የቅዱስ ያሬድ ምናኔ፦ ወደ ገዳም ሊሄድ ተዘጋጀ በዚህ ጊዜ የሚወዱት ካህናት፣ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ተከትለውት እስከ ተከዜ ወንዝ ድረስ ሸኙት። ከእርሱ በሚለዩበትም ጊዜ "ሰላመ ነሳእነ ወሰላም ኃደግነ ለክሙ ወሰላመ እግዚአብሔር የሀሉ ምስለ ኩልክሙ፤ ሰላምን ከእናንተ ተቀበልን ለእናንተም ሰላምን ተውንላችሁ የእግዚአብሔር ሰላምም ከሁላችሁ ጋራ ይኹን" ብሎ በዜማ ተሰናበታቸው። ዳግመኛ "ወሰላም እግዚአብሔር እንተ ኵሉ ባቲ ተሀሉ ወትረ ምስለ ኵልክሙ፤ ፍቅርና ስምምነት ሁሉ ያለበት የእግዚአብሔር ሰላምታ ሁል ጊዜ ከሁላችሁ ጋራ ትኑር" ብሎ በጣዕ ዜማው መረቃቸው። ካህናቱም ይህን ሰምተው አለቀሱ። እርሱም ከእርሱ ጋራ አለቀሰ። በዚሁ ጣዕመ ዜማው የመጨረሻ ቡራኬውን ሰጣቸውና እርስ በእርሳቸው ተሳስመው ተነሰነባብተው ከእርሱ በመለየታቸው እያዘኑና እየተከዙ ወደ አገራቸው አኵሱም ተመለሱ። እርሱ ግን የተከዜን ወንዝ ተሻገረ። የወንዙ ፏፏቴና ጎርፍ እንሚጮህ አንበሳ ሲጮህ በሰማ ጊዜ "አኅለፍኮሙ በእግር እንተ የብስ ማእከለ ባሕር ተከዜ...፤ በተከዜ ባሕር መካከል በእግር እንደሚሻገር በደረቅ አሻገርካቸው..." እያለ በረቀቀ ምስጢር እግዚአብሔርን በማመስገን እየዘመረ ሲሒድ አንዲት ሴት ውሃ ቀድታ ወደ ቤቶ ስትመለስ ድምፁን ሰምታ ወይ ቃል! ወይ ቃል! እንዴት አንጀት ይበላል! ምንኛስ ያሳዝናል! ብላ ደጋግማ በማድነቅ ስለ ተናገረች ቅዱስ ያሬድ ቆሞ የዘመረባት ቦታ "ወይ ቃል" ተብላ ተጠራች። ዛሬ ይህች ቦታ ጎንደር ክፍለ አገር ደባርቅ አካባቢ "ወይ ቃል" ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ተብላ ትጠራለች።

ቅዱስ ያሬድ ወደ ሰሜን ተራሮች ሔዶ  ጸለምት ወጥቶ ብርድ በጸናበት በረዶ በተከማቸበት ሳኔር ተብሎ በሚጠራ በሐዊ ዐምባ ጽመና ይዞ ተቀመጠ። በዚያም በብዙ ትጋት በጾምና በጸሎት ይልቁንም በስብሐት እግዚአብሔር ብቻ ተወስኖ ጉባኤ ዘርግቶ፣ ትምህርት አስፍቶ ከሱራፌል መላእክት እንደተማረው አድርጎ ከጸለምት፣ ከስሜን፣ ከአገውና ከሌላ አገር ወደ እርሱ የሚመጡትን ሰዎች ሁሉ ማሕሌተ እግዚአብሔር እያስተማረ ኖረ።

ቅዱስ ያሬድ ከትውልድ አገሩ አኵሱም መንኖ ከወጣ በኋላ ትዕግሥቱን እያዘወተረ ወደ እርሱ የመጡትን ሁሉ በማስተማር በገዳመ ስሜን ኖረ። ቅዱስ ቍርባን ለመቀበልና ቅዱሳት ገዳማትን ለመሳለም በፈለገ ጊዜ በሠረገላ ብርሃን ተጭኖ አኵሱም ደርሶ ቅዱስ ቍርባን ተቀብሎ ሌሎች ገዳማትንም ይሳለም ነበር።

በመጨረሻ ቅዱስ ያሬድ ካህን ዘመኑን ሁሉ በመላእክት ማኅሌት እግዚአብሔርን በማገልገልና ይህን ማኅሌት ለሚከተሉት ደቀ መዛሙርት በማስተማር ዘመኑን ፈጽሞ ለሃያ ሁለት ዓመታት በላይ በምናኔ ታግሦ በገድሉና በጣዕመ ዜማው ፀላኤ ሠናያትን ድል አድርጎ ከዚህ ዓለም ድካምና መከራ የሚያርፍበት፣ የሚሰወርበት ቀንና ሰዓት መድረሱን በጸጋ በዐወቀ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን ሰብስቦ "ይቤ ጳውሎስ ኃላፊ ንብረቱ ለዝንቱ ዓለም አኃውየ አስተፋጥኑ ገቢረ ሠናየ አነሰ በድረየኒ ፈጸምኩ ወሃይማኖትየኒ ሠለጥኩ እንከሰ ጽኑሕ ሊተ አክሊል ዘየዓሥየኒ መኰንነ ጽድቅ"  2ጢሞ4፥7-8 እያለ በሚያራራ ቃል ምክሩን ሰጥቶ ተሰናበታቸው። እነርሱም ምክሩን ተቀብለው "አባ አቡነ፣ አባ መምህርነ አይቴ ተሐውር ወለመኑ ተኀድገነ፤ አባታችን መምህራችን ወደ የት ትሔዳለኽ? ለማንስ ትተወናለኽ? እያሉ ሲያዝኑ ሲያለቅሱ በአንድ ዋሻ ውስጥ ገብቶ ግንቦት11 ቀን በ571ዓ.ም ተሰወረ። (ምንጭ፦ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን ቅዱስ ያሬድና የቅዱስ ያሬድ ታሪክ ከሚሉት መጻሕፍት።)

ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡

#ሚያዝያ_5_ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩, #እግዚአብሔር ሰንበትን ቀደሰ
፪, ቅዱስ ሕዝቅኤል ነብይ
፫, ቅዱስ ዲዮስቆሮስ (ክፉ ላለመናገር ድንጋይ ጎርሶ የኖረ አባት)
፬, ቅድስት ታኦድራ
፭, ቅዱስ አርሳኒ
፮, ቅዱስ ያሬድ ካህን ልደቱ

#ወርኃዊ_በዓላት
፩, ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፪, ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ
፫, አቡነ #ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ ጻድቅ (አባ ገብረ ሕይወት)
፬, ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮጵያዊ
፭, ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ