ቅዱሳን ኅሩያን የዲ°ን ዮርዳኖስ ትምህርቶች
5.85K subscribers
1.06K photos
7 videos
37 files
247 links
የዲ.ን ዮርዳኖስ አበበ ስብከት በድምጽ እንለቃለን
ለአስተያየት @EMNE_TSYON @unitte_bot
በቴሌግራም ከፈለጉን @henokhailee
በfacebook ከፈለጉን https://www.facebook.com/tewahidosewhone/
በyoutube ከፈለጉን https://youtube.com/channel/UCq2ueVG6O3ZuKHJ485y7hfg
Download Telegram
#ነቢይ_ወሰማዕት_ቅዱስ_ኤርምያስ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

“ኤርምያስ” ማለት “እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ያደርጋል” ማለት ነው፡፡ ከአራቱ ዓበይት ነቢያት አንዱ ሲኾን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን አባቱ “ኬልቅያስ” ይባላል፡፡ እናቱ ደግሞ “ማርታ” እንደምትባል የቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ትውፊት ያስረዳል፡፡ አገሩ በኢየሩሳሌም አቅራቢያ ካለው ከተማ ከ“ዓናቶት” ነው፤ ትውልዱም ከካህናት ወገን እንደነበረ ተጽፏል /ኤር.፩፡፩/፡፡

#ነቢዩ_ኤርምያስ ለነቢይነት የተለየው ከእናቱ ማኅፀን ዠምሮ ነው /ኤር.፩፡፮/፡፡ ይኸውም እንደ ነቢዩ ሳሙኤል፤ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ ማለት ነው፡፡ አንድም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፡- “በእናቴ ማኅፀን ሳለኹ የለየኝ …” እንዳለው ነው /ገላ. ፩፡፲፭/፡፡
#ነቢዩ_ኤርምያስ ለእስራኤል ብቻ ሳይኾን ለአሕዛብም ጭምር ነቢይ እንዲኾን በተጠራ ጊዜ ደንግጧል፤ “ሕፃን አንድም ሕፃነ አእምሮ ነኝና ወዮልኝ” በማለትም አመንትቷል፡፡ በዃላ ግን እግዚአብሔር፡- “እስራኤልና አሕዛብን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር፣ ከገቢረ ኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ ትመልሳቸዋለኽና ሕፃን ነኝ አንድም ሕፃነ አእምሮ ነኝ አትበል” ተብሎ በተሰጠው ተስፋ መሠረት በረታ፡፡

#በነቢዩ_ዘመን በይሁዳ ነግሠው የነበሩት ነገሥታት አምስት ናቸው፡፡ እነርሱም፡-
1, ባዕድ አምልኮን ለማስወገድ፣ የእግዚአብሔርን ቤትና አምልኮ ለማሳደስ ብዙ የደከመው፣ በመሞቱም ነቢዩ ያለቀሰለት /፪ኛ ዜና ፴፬-፴፭/ ኢዮስያስ፤
2, በነገሠ በ፫ኛው ወር የግብጽ ንጉሥ አስሮ የወሰደው የኢዮስያስ ልጅ ኢዮአክስ (ሰሎም) /፪ኛ ዜና ፴፮፡፩-፬፣ ኤር.፳፪፡፲-፲፪/፤
3, ፈርዖን ኒካዑ በወንድሙ በኢዮአክስ ምትክ በይሁዳ ያነገሠው፣ አስቀድሞ ለግብጽ በኋላም ለባቢሎን የተገዛው /፪ኛ ዜና ፴፮፡፬-፰/፣ በ፲፩ የንግሥና ዘመኑ እጅግ ክፉ የነበረው /ኤር.፳፪፡፲፫-፲፱/፣ የእግዚአብሔርን ቃል በመናቅ ኤርምያስን የተቃወመው መጽሐፉንም ያቃጠለበት /ኤር.፴፮/ ኢዮአቄም፤
4, ከአባቱ ከኢዮአቄም በኋላ በኢየሩሳሌም ለሦስት ወራት የነገሠ፣ በ፭፻፺፯ ከክ.ል.በ. ላይ ከቤተሰቦቹና ከአለቆቹ በጠቅላላ ከዐሥር ሺሕ ሰዎች ጋር ወደ ባቢሎን ተማርኮ የሔደው /፪ኛ ነገ.፳፬፡፰-፲፯፣ ኤር.፳፪፡፳፬-፴/ ዮአኪን (ኢኮንያን)፤
5, ከኢዮስያስ ልጆች ሦስተኛ የኾነው፣ የወንድሙ ልጅ ዮአኪን በተማረከ ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ከ፭፻፺፯-፭፻፹፯ ከክ.ል.በ. በይሁዳ ያነገሠው፣ ከነቢዩ ኤርምያስ ምክር ላይጠቀምበት ምክርን ይጠይቅ የነበረው፣ በክፋቱ የጸና፣ ከአራት ዓመት በኋላ ወደ ባቢሎን ተወስዶ የተመለሰው /ኤር.፶፩፡፶፱/፣ በኋላ ላይ በግብጽ ተማምኖ ባቢሎን ንጉሥ ላይ ያመፀው፣ ከዓመት ተመንፈቅ በኋላ ተይዞ የተማረከና ዕዉር ኾኖ በግዞት ቤት ሳለ የሞተው ሴዴቅያስ ናቸው፡፡

#ነቢዩ_ኤርምያስ የነበረበት ነባራዊ ኹኔታ....

#ነቢዩ_ኤርምያስ አገልግሎቱን የዠመረው የይሁዳ ንጉሥ ኢዮስያስ (ከ፮፻፵-፮፻፱ ከክ.ል.በ.) በነገሠ በ፲፫ኛው ዓመት ላይ ነበር፡፡ ይኸውም በ፮፻፳፮ ከክ.ል.በ. መኾኑ ነው፡፡ ይኽ ዓመት ደግሞ እጅግ በጣም ወሳኝ የኾነ ወቅት ነበር፡፡ በአንድ በኵል ንጉሥ ኢዮስያስ ባዕድ አምልኮን ለማስወገድ፣ የ #እግዚአብሔርን ቤትና አምልኮ ለማሳደስ ከዠመረ አንድ ዓመት ኾኖታል፡፡ በሌላ በኵል ደግሞ ባቢሎናውያን ከአሦር አገዛዝ ነፃ ለመውጣት አንድ ዓመት ይቀራቸው ነበር፡፡ ስለዚኽ ነቢዩ ኤርምያስ አገልግሎቱን የዠመረው በቤተ ክህነቱም በፖለቲካውም ወሳኝ ኩነቶች የሚፈጸሙበት ሰዓት ላይ ነበር ማለት ነው፡፡ ከዚኹ ጋር በተያያዘ የሰሜኑ ክፍል ሕዝብ ወደ ሶርያ ተማርኮ ከፈለሰ ገና ፻ ዓመቱ ነው (የተማረኩት በ፯፻፳፪ ከክ.ል.በ. መኾኑ ከዚኽ በፊት መነጋገራችን ያስታውሱ)፡፡
የሕዝቡን ግብረ ገብነት ስንመለከት ደግሞ፥ #በቤተ_መቅደስ ሔደው መሥዋዕት ስላቀረቡ ብቻ #እግዚአብሔርን ከልባቸው ያመለኩት ይመስላቸው ነበር፡፡ #እግዚአብሔር ግን ከመሥዋዕት ይልቅ #ልብን ነው የሚፈልገው፡፡ ይኸውም ሊቁ #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ፡- “እግዚአብሔር ከወርቃማ ምሥዋዕት ይልቅ ወርቃማ ነፍሳትን ይሻል” እንዳለው ነው፡፡ #ነቢዩ_ኤርምስያስ ይኽን የግብዝነት ምልልሳቸውን እንዲያስተካክሉ ነገራቸው፡፡ መፃተኛውን፣ ድኻ አደጉን፣ መበለቲቱን እየበደሉ እልፍ ጊዜ መሥዋዕት ማቅረባቸው ቤተ መቅደሱን የወንበዴዎች ዋሻ ማድረግ እንደኾነ አሳሰባቸው /ኤር.፯፡፰-፲/፡፡ ካልተመለሱ ግን እነርሱ በባዕድ ንጉሥ እንደሚማረኩ፥ ቤተ መቅደሱም እንደሚፈርስ በቤተ መቅደሱ በር ኾኖ በመጮኽ በግልጽ ነገራቸው /ኤር.፯፡፬/፡፡ ሕዝቡና ካህናቱ ግን አላመኑትም፡፡ ይባስ ብለዉም
#መቱት /ኤር.፳፡፪/፤
#በእግር ግንድ ያዙት፤
#በጭቃ ጕድጓድ ጣሉት፤
#ኹለት ጊዜ አሰሩት /ኤር.፴፯፡፲፫-፳፩/፤ #አብዷል አሉት /ኤር.፳፱፡፳፮/፡፡
ተወዳጆች ሆይ! እኛስ? እኛስ መፃተኛውን አልበደልንምን? ድኻ አደጉን አላንከራተትንምን? መበለቲቱን አላስከፋታንምን? ይኽን እንድናስተካክልስ እግዚአብሔር ስንት ጊዜ ተናገረን? ታድያ ቤተ መቅደሱ ሰውነታችን እስኪፈርስ ድረስ እየጠበቅን ነው? ወይስ እንደ ነቢዩ ቃል ተመልሰናል? እግዚአብሔር እስከ ዛሬ ድረስ የጠበቀን ከኀጢአታችን ጋር ተስማምቶ ሳይኾን የንስሐ ጊዜ ሲሰጠን ነው፡፡

#ነቢዩ_ኤርምያስ ልዩ ባሕርያት👇

1, በ #መጽሐፍ_ቅዱስ ውስጥ ስለ ደረሰበት መከራ እንደ ኤርምያስ ያለቀሰ ሰው የለም፡፡ በስነ መለኮት ምሁራን ዘንድ፡- “ #አልቃሻው_ነቢይ” እየተባለ መጠራቱም ይኽን ባሕርዩን የሚያመለክት ነው፡፡ ሰቆቃወ ኤርምያስ ማንበብም ይኽን ሐሳብ ግልጽ ያደርግልናል፡፡

2, የ #ጸሎት_ነቢይ ነው፡፡ ነቢዩ ኤርምያስ ከሌሎች ነቢያት ለየት የሚያደርገው ሌላኛው ነጥብ ከእግዚአብሔር ጋር የሚነጋገረው በጸሎት መኾኑ ነው፡፡ ትንቢቱን፣ ራዕዩን የሚገለጽለት ሲጸልይ ነው፡፡ ሲከፋው የሚያወያየው ወዳጅ ሚስት የለውም፤ አላገባምና፡፡ ልጅም የለውም፡፡ ስለዚኽ ሲከፋው፣ የወንድሞቹን ስቃይ ሲያይ፣ ቤተ መቅዱስን መፍረስ ሲመለከት ያለቅሳል፡፡ #እግዚአብሔርም ያናግሯል፡፡

3, #ነቢዩ ምንም እንኳን ኢየሩሳሌምንና ሕዝቡን ቢወድም /ኤር.፰፡፲፰-፱፡፩/፣ ፲፫፡፲፯/ መማረካቸው እንደማይቀር ሊነግራቸው ተገድዷል፡፡ ከዚኽም በላይ፡- “ለባቢሎን ንጉሥ እጅ ስጡ፤ ተገዙም፤ ምርኮኞችም እስከ ፸ ዓመት ድረስ አይመለሱም” ብሎ የተገለጠለትን የ #እግዚአብሔርን ቃል ስለተናገረ ተጠላ፡፡ ብዙዎችም ሊገድሉት አሰቡ /ኤር.፲፩፡፳፩፣ ፳፮፡፲፩፣ ፴፮፡፲፮፣ ፴፰፡፮-፲/፡፡ #ተመታ /ኤር.፳፡፪/፤ #በእግር ግንድ ተያዘ ፤ #በጭቃ ጕድጓድ ተጣለ፤ #ኹለት ጊዜ ታሰረ /ኤር.፴፯፡፲፫-፳፩/፤ #አብዷል ተባለ /ኤር.፳፱፡፳፮/፡፡ ስለዚኽ ነቢዩ በራሱ መጽሐፍ ላይ ስለ ራሱና ስለደረሰበት መከራ ብዙ ስለ ጻፈ ከሌሎች ነቢያት ይልቅ ጠባዩና ኹኔታው ተገልጿል፡፡

4, ከዚኹ ኹሉ ጋር ለሕዝቡ ምልክት እንዲኾን ሚስት እንዳያገባ፣ ወደ ግብዣ ወይም ወደ ልቅሶ እንዳይሔድ ተከልክሏል /ኤር.፲፮/......።

#ትንቢተ_ኤርምያስ
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
#ሐምሌ_23_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበቡት_መልእክታት👇
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
2ኛ ቆሮ 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ እንግዲህ እንደ በረከት ሆኖ ከስስት የማይሆን ይህ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ አስቀድመው ወደ እናንተ መጥተው፥ አስቀድማችሁ ተስፋ የሰጣችሁትን በረከት አስቀድመው እንዲፈጽሙ ወንድሞችን እለምን ዘንድ እንዲያስፈልገኝ አሰብሁ።
⁶ ይህንም እላለሁ፦ በጥቂት የሚዘራ በጥቂት ደግሞ ያጭዳል፥ በበረከትም የሚዘራ በበረከት ደግሞ ያጭዳል።
⁷ እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም።
⁸-⁹ በተነ፥ ለምስኪኖች ሰጠ፥ ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ እግዚአብሔር፥ ሁልጊዜ በነገር ሁሉ ብቃትን ሁሉ አግኝታችሁ ለበጎ ሥራ ሁሉ ትበዙ ዘንድ፥ ጸጋን ሁሉ ሊያበዛላችሁ ይችላል።
¹⁰ ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱም የምትዘሩትን ዘር ይሰጣችኋል ያበረክትላችሁማል፥ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያሳድጋል፤
¹¹ በእኛ በኩል ለእግዚአብሔር የምስጋና ምክንያት የሚሆነውን ልግስና ሁሉ እንድታሳዩ በሁሉ ነገር ባለ ጠጎች ትሆናላችሁ።
¹² የዚህ ረድኤት አገልግሎት ለቅዱሳን የሚጎድላቸውን በሙሉ የሚሰጥ ብቻ አይደለምና፥ ነገር ግን ደግሞ በብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር ይበዛል፤
¹³ በዚህ አገልግሎት ስለ ተፈተናችሁ፥ በክርስቶስ ወንጌል በማመናችሁ ስለሚሆን መታዘዝ እነርሱንና ሁሉንም ስለምትረዱበት ልግስና እግዚአብሔርን ያከብራሉ፥
¹⁴ ራሳቸውም ስለ እናንተ ሲያማልዱ፥ በእናንተ ላይ ከሚሆነው ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሣ ይናፍቁአችኋል።
¹⁵ ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ያዕቆብ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?
¹⁵ ወንድም ወይም እኅት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ፥
¹⁶ ከእናንተ አንዱም፦ በደኅና ሂዱ፥ እሳት ሙቁ፥ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል?
¹⁷ እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።
¹⁸ ነገር ግን አንድ ሰው፦ አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ፤ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ፥ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል።
¹⁹ እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ፤ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።
²⁰ አንተ ከንቱ ሰው፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን?
²¹ አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን?
²² እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደ ነበረ፥ በሥራም እምነት እንደ ተፈጸመ ትመለከታለህን?
²³ መጽሐፍም፦ አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ።
²⁴ ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ።
²⁵ እንደዚሁም ጋለሞታይቱ ረዓብ ደግሞ መልእክተኞቹን ተቀብላ በሌላ መንገድ በሰደደቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን?
²⁶ ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ሐዋርያት 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ በሰንበት ቀንም ከከተማው በር ውጭ የጸሎት ስፍራ በዚያ መሆኑን ስላሰብን ወደ ወንዝ አጠገብ ወጣን፤ ተቀምጠንም ለተሰበሰቡት ሴቶች ተናገርን።
¹⁴ ከትያጥሮን ከተማም የመጣች ቀይ ሐር ሻጭ እግዚአብሔርን የምታመልክ ልድያ የሚሉአት አንዲት ሴት ትሰማ ነበረች፤ ጳውሎስም የሚናገረውን ታዳምጥ ዘንድ ጌታ ልብዋን ከፈተላት።
¹⁵ እርስዋም ከቤተ ሰዎችዋ ጋር ከተጠመቀች በኋላ፦ በጌታ የማምን እንድሆን ከፈረዳችሁልኝ፥ ወደ ቤቴ ገብታችሁ ኑሩ ብላ ለመነችን፤ በግድም አለችን።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

#ሐምሌ_23_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበበው_የሚዜመው_የቅዳሴ_ምስባክ👇

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
"ኢይቀሥፍ ወትረ ወኢይትመዓዕ ዘልፈ። አኮ በከመ ኃጢአትነ ዘገብረ ለነ። ወኢፈደየነ በከመ አበሳነ"። መዝ 102፥9-10 ።
"ሁልጊዜም አይቀሥፍም፥ ለዘላለምም አይቈጣም። እንደ ኃጢአታችን አላደረገብንም፥ እንደ በደላችንም አልከፈለንም"። መዝ 102፥9-10 ።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

#ሐምሌ_23_ቀን_የእለቱን_ወንጌል_እናንብብ📖👇
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ዮሐንስ 19
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³¹ አይሁድም የማዘጋጀት ቀን ስለ ሆነ ያ ሰንበት ትልቅ ነበረና ሥጋቸው በሰንበት በመስቀል ላይ እንዳይኖር፥ ጭናቸውን ሰብረው እንዲያወርዱአቸው ጲላጦስን ለመኑት።
³² ጭፍሮችም መጥተው የፊተኛውን ጭን ከእርሱም ጋር የተሰቀለውን የሌላውን ጭን ሰበሩ፤
³³ ወደ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን እርሱ ፈጽሞ እንደ ሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም፤
³⁴ ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጎኑን በጦር ወጋው፤ ወዲያውም ደምና ውኃ ወጣ።
³⁵ ያየውም መስክሮአል፤ ምስክሩም እውነት ነው፤ እናንተም ደግሞ ታምኑ ዘንድ እርሱ እውነት እንዲናገር ያውቃል።
³⁶ ይህ የሆነ፦ ከእርሱ አጥንት አይሰበርም የሚል የመጽሐፉ ቃል እንዲፈጸም ነው።
³⁷ ደግሞም ሌላው መጽሐፍ፦ የወጉትን ያዩታል ይላል።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
የሚቀደሰው ቅዳሴ የ #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ ወይም #እግዚእነ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️