ቅዱሳን ኅሩያን የዲ°ን ዮርዳኖስ ትምህርቶች
4.78K subscribers
773 photos
5 videos
17 files
239 links
የዲ.ን ሄኖክ ሀይሌን ስብከት በድምጽ እንለቃለን
ለአስተያየት @EMNE_TSYON @unitte_bot
በቴሌግራም ከፈለጉን @henokhailee
በfacebook ከፈለጉን https://www.facebook.com/tewahidosewhone/
በyoutube ከፈለጉን https://youtube.com/channel/UCq2ueVG6O3ZuKHJ485y7hfg
Download Telegram
#ሰሙነ_ሕማማት

ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ሰሙነ ሕማማት የጾመ ሁዳዴ የመጨረሻው ሳምንት፤ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማም የሚታሰብበት፤ ካህናትና ምእመናን በአጸደ ቤተክርስቲያን ተሰብስበው የሕማሙን ነገር የሚያወሳውን ዜማ የሚያዜሙበት፤ ግብረ ሕማም በመባል የሚታወቀውን መጽፍ የሚያነቡበትና የሚሰሙበት፤ በነግህ፣ በሠልስት፣ በስድስት፣ በተሰዓት /ዘጠኝ /ሰዓት፣ በሰርክ /በዐስራ አንድ/ ሰዓት እየመላለሱ የሚሰግዱበትና የሚጸለዩበት ልዩ ሳምንት ነው ከሆሳዕና ማግስት እስከ ትንሳኤ።

በዚህ ሳምንት በተለይ ካህናት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ ምክንያቱም ጌታችን የደረሰበትን መከራና ስቃይ እንዲሁም የሰው ልጅ ፭ ሺ ፭ መቶ ዘመን በጨለማ ግዞት ይኖር እንደነበር ለማዘከርም ጭምር ነው። የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራና ሕማም በጽኑ እንድናስበው ያስተማሩን ሐዋርያት ናቸው። ለእነርሱም የነገራቸው ደግሞ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

ሰሙነ ሕማማት የጌታችንን ሕማማት ከማሰብ ጋር በየዕለቱ በርካታ ድርጊቶች መፈጸማቸውን የምናስታውስበት ሳምንት ነው፦

#ሰኞ
#መርገመ_በለስ_የተፈጸመበት_ሰኞ_ይባላል
በዚህ ዕለት ጌታችን ከቢታኒያ ሲወጣ ተራበ ቅጠል ያለባትን በለስ ተመልክቶ ወደ በለሲቱ ቢቀርብ ከቅጠል በቀር ምንም ነገር ባለማግኘቱ “ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ምንም ካንቺ ፍሬ አይበላ” ማር ፲፩፥፲፬ በማለት ስለረገማት መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ ይባላል።

#አንጽሖተ_ቤተ_መቅደስ_ይባላል፡-
ጌታ ወደ ቤተመቅደስ ሄዶ በቤተመቅደሱ የሚሸጡትን እና የሚለውጡትን “ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች” ማቴ ፳፩፥፲፫ በማለት ከቤተመቅደስ ገርፎ አስወጥቷቸዋልና።

#ማክሰኞ
#የጥያቄ_ቀን_ይባላል
ሰኞ ዕለት በቤተመቅደስ ሲሸጡ እና ሲለውጡ የነበሩትን ሁሉ እየገረፈ በማባረሩ ምክንያት ለሰው ልጅ ሹመትንና ስልጣንን የሰጠ ጌታ “በምን ስልጣን ይህንን ታደርጋለህ?” ማቴ ፳፩፥ ፳፫ ተብሎ በፈሪሳውያን ተጠይቋልና የጥያቄ ቀን ይባላል።

#የትምህርት_ቀን_ይባላል፡-
በዚህ ዕለት በቤተመቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረም የትምህርት ቀን ይባላል። ሉቃ ፳፩ ፥፳፰ ፣ ማር ፲፪፥፪።

#ረቡዕ
#ምክረ_አይሁድ_ይባላል
ረቡዕ እለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል። ወቅቱ የፋሲካን በዓል የሚያከብሩበት ቀን በመሆኑ እና ብዙ ህዝብም ጌታን ይከተለው ስለነበር ሁከት እንዳይነሳ ስጋት ነበራቸው ። ነገር ግን ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ስለነገራቸው ሉቃ ፳፪፥፩-፮ ጭንቀታቸው ተወግዶ በጌታ መያዝ ተስማምተዋል።

#የመልካም_መዓዛ_ቀንም_ይባላል፡-
ጌታችን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በሰምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት/ባለሽቶዋ ማርያም/ ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ማቴ ፳፮፥፮-፯ የመዓዛ ቀን ይባላል።

#የእንባ_ቀን_ይባላል፡-
ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ እፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አርሳለችና ማር ፲፬፥፱ የእንባ ቀን ይባላል።

#ሐሙስ
#ጸሎተ_ሐሙስ_ይባላል
ጌታችን ለአይሁድ ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ ሲጸልይ በማደሩ ማቴ ፳፮፥፴፮ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል።

#የምስጢር_ቀን_ይባላል፡-
ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምስጢር ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምስጢር ቀን ይባላል።

#የሐዲስ_ኪዳን_ሐሙስ_ይባላል፡-
መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድኅነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ ሉቃ ፳፪፥፳ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።

#የነጻነት_ሐሙስ_ይባላል፡-
ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነም ዮሐ ፲፭፥ ፲፭ የነጻነት ሐሙስ ይባላል።

#ዓርብ
#የስቅለት_ዓርብ_ይባላል
ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና ማቴ ፳፯፥፴፭ የስቅለት ዓርብ ይባላል።

#መልካሙ_ዓርብ_ይባላል፡-
ከጌታ ስቅለት በፊት በተለይም በሮማውያን ህግ የወንጀለኛ መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል ጌታችን በደሙ ቀድሶ የምህረት፣ የሕይወት አርማ፣ የዲያቢሎስ ድል መንሻ ስላደረገው፤ በሞቱ መልካሙን ሕይወት ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ይባላል።

#ቅዳሜ
#ቀዳም_ስዑር_ትባላለች
ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረች ቅዳሜ ይባላል።

#ለምለም_ቅዳሜ_ይባላል፡-
ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጤማ እስከ ትንሣኤ ለሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል።

#ቅዱስ_ቅዳሜ_ይባላል፡-
ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ያረፈበት ቀን ሲሆን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ስራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዶ ሲኦልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ የነበሩትን ነፍሳት የዘላለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል።

(ስምዐ ጽድቅ  መጋቢት ፳፻፪ ዓ.ም)

@beteafework       @beteafework
@beteafework       @beteafework
@beteafework       @beteafework
ከመላእክትም አንዱ ከሀዲ ጉዝፋር ከዚህ ለምን ቆምክ አለው። እርሱም ወዳጁ መርቀፀ ለክብር ባለቤት #ለጌታ_ኢየሱስ_ክርስቶስ እንጂ ለሌላ እንዳይሰጥ ብሎ እንዳማለው ነገረው። መልአኩም የክብር ባለቤት የሕያው #እግዚአብሔር_ልጅ_ጌታ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ይህ ነውና ና ስገድ አለው።

ጉዝፋርም ሰገደ ደብዳቤውንም ሰጠው።እየተንቀጠቀጠም የክብር ባለቤት #ጌታዬ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ሆይ አመንኩብህ አለ። ጌታም ያንን ወርቅ ይመዝኑ ት ዘንድ አዘዘ። አርባ ልጥርም ሆነ ጉዝፋርንም ከቀሲስ ታዴዎስ ዘንድ እንዲጠመቅ አዘዘው። ከቤተሰቡ ሁሉ ጋር ተጠመቀ የተጠመቁትም ሰባ አምስት ነፍስ ሆኑ።

ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡

#የዕለተ_ሐሙስ_ፍጥረታት

#ሐሙስ፡- የሚለው የዕለቱ ስም ሀምሰ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ነው #አምስተኛ ማለት ነው፡፡ አምስተኛነቱም እግዚአብሔር ፍጥረታትን መፍጠር ከጀመረበት ከዕለተ እሑድ ጀምሮ ያለው ቀን ማለት ነው፡፡

  #የሐሙስ_ፍጥረታት
እግዚአብሔር ሐሙስ በቀዳማይ ሰዓት ለሊት “#ውሃ_ሕያው_ነፍስ_ያላቸው_ተንቀሳቃሾች_ታስገኝ” ብሎ በማዘዝ ሦስት አይነት ፍጥረታትን ፈጠረ፡፡ ዘፍ 1፡20 በዕለተ ሐሙስ የተፈጠሩት ሦስት ፍጥረታት ዘመደ እንስሳት የሚባሉት አሣዎች፣ ዘመደ አራዊት የተባሉት ኣዞ፣ጉማሬ፣ አሳነባሪ፣ ዘመደ አዕዋፍ የሚባሉት ደግሞ ዳክዬዎች ናቸው፡፡ 
#በዕለተ_ሐሙስ_የተፈጠሩት_ፍጥረታት_ተፈጥሮአቸው_ከአራቱ_ባሕሪያተ_ስጋ /መሬት፣ ውሃ ፣ነፋስና፣ እሳት/ ነው፡፡ አካላቸው ሥጋና ደም፣ አፅምና ጅማት ሲሆን በደም ነፍስ ይንቀሳቀሳሉ የደመ ነፍስ እውቀት አላቸው ደመነፍስ ማለትም በደም ነፍስነት፣ ኃይልነት የሚንቀሳቀሱ፣ የደም ነፍስ ያላቸው፣ ደማቸው ሲቆም እንቅስቃሴያቸውም የሚቆም ማለት ነው፡፡
   #የሐሙስ_ፍጥረታት_በአካሄዳቸው_በአኗኗራቸው_አንፃር_በሦስት_ይከፈላሉ በአካሄዳቸው በልብ የሚሳቡ፣ በእግር የሚሽከረከሩ፣ /የሚሄዱ/፣ በክንፍ የሚበሩ ይባላሉ፡፡

#በአኗኗራቸውም አንጻር በባህር ውስጥ ተፈጥረው በረው ወደ የብስ፣ ወደ ደረቁ መሬት የወጡ፣ በዚያው በተፈጠሩበት በባህር ውስጥ የቀሩ፣ ወጣ ገባ እያሉ ማለት ከባህር ወደ የብስ፣ ከየብስ ወደ ባሕር ወጣ ገባ እያሉ የሚኖሩ ይባላሉ፡፡ ከእነዚህም ፍጥረታት የሚበሉና የማይበሉ ለሰው የሚገዙና፣ የማይገዙም አሉ፡፡
    
#የሐሙስ_ፍጥረታት_ምሳሌነት

#በባሕር_ውስጥ_የሚኖሩት_ምሌሳነታቸው፡-

በእግዚአብሔር አምነው በስሙ ተጠምቀው በዚያው ፀንተው የሚኖሩ ሰዎች፤
በሕገ እግዚአብሔር ፀንተው በትዳር ተወስነው በሀብት በንብረታቸው መልካም ስራ እየሠሩ ዓሥራት አውጥተው፣ በዓላትን አክብረው የሚኖሩ የሕጋውያ ሰዎች፤
ግብራችንን አንተውም ብለው ሲሰርቁ ሲቀሙ፤ ሲምሉና ሲገዘቱ የሚኖሩ የኃጥአን ምሳሌ ናቸው፡፡

#ወጣ_ገባ_እያሉ_የሚኖሩት_ምሳሌነታቸው
  አንድ ጊዜ ወደ ዓለም አንድ ጊዜ ወደ ገዳም ሲመላለሱ የሚኖሩ መነኮሳት፣
አንድ ጊዜ ወደ ሀይማኖት አንድ ጊዜ ወደ ክህደት የሚወላውሉ ሰዎች፤
#በባሕር_ተፈጥረው_በረው_ወደ_የብስ_የሄዱት
ከዘመድ አዝማድ ተለይተው ርቀው ከበረሃ ወድቀው ደምፀ አራዊቱን ፀብአ አጋንንቱን ግርማ ለሊቱን ታግሰው የሚኖሩ የመናንያን ምሳሌ ናቸው፡፡
አንድም በባህር ተፈጥረው በረው ወደ የብስ የሚኖሩት የከሀዲዎች ምሳሌ ነው በሀይማኖት ኖረው በኋላ ይክዳሉና
           
#አካሄዳቸውም 
#በልብ_የሚሳቡ፡- የመንግስት ምሳሌ ናቸው እነዚህ በልብ (በደረት) ተስበው ስራቸውን ፈቃዳቸውን እንዲፈፅሙ መንግስትም በልቡ ያሰበውን ይሠራል ይፈፅማል፡፡
#በእግር_የሚሽከረከሩ
“ያላችሁን ትታችሁ ተከተሉኝ” ባለው አምላካዊ ቃል መሠረት ሁሉን ትተው ከሴት ከወንድ እርቀው ድንግልናቸውን ጠብቀው ከትሩፋት ወደ ትሩፋት እየተሸጋገሩ የሚኖሩ የመናንያን ምሳሌ፡፡

#በክንፋቸው_የሚበሩት፡- ሥጋችሁን እንጂ ነፍሳችሁን ለመግደል የማይችሉትን አትፍሩ ባለው አምላካዊ ቃል ተመርተው ሳይፈሩ ዓላውያን ነገስታት ካሉበት ገብተው ሃይማኖታቸውን በመመስከር ሰማዕታትነታቸውን የሚፈፅሙ ሰማዕታት ምሳሌ ናቸው፡፡
  #ሰው_የሚባላቸውና_ለሰው_የሚገዙት፡- ለእግዚአብሔርና ለሰው በፍቅር በትሕትና የሚገዙ፣ የእግዚአብሔርን ፍቃድ የሚፈፅሙ የፃድቃን ምሳሌ ናቸው፡፡
#ሰው_የማይበላቸው_ለሰው_የማይገዙት ለእግዚአብሔርም ለሰውም የማይገዙ፣ አንገዛም አንታዘዝም ብለው በትዕቢት በዓመፅ የሚኖሩ የሃጣን ምሳሌ ናቸው፡፡
እግዚአብሔር ከአንድ ባሕር ሦስት ወገን የሆኑ ፍጥረታትን ፈጠረ፡፡ ከአንድ ማየገቦ ሦስት ትውልድ፡- ትውለደ ሴም፣ ትውልደ ያፌት፣ ትውልደ ካም ይጠመቁ ዘንድ መሰጠቱን  ያሳያል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ልጅነት በአብ‹ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቀው ለመሰጠቷም ምሳሌ ነው፡፡
  በዕለተ ሐሙስና በዕለተ ዓርብ የተፈጠሩት ፍጥረታት “እንስሳት” በመባል አንድ ቢሆኑም በአኗኗራቸውና በግብራቸው ይለያያሉ፡፡ የሐሙስ ፍጥረታት ከባሕር ተለይው በየብስ /በምድር/ መኖር አይችሉም የፀሐይ ሙቀት ሲነካቸው ይሞታሉ፡፡
  የግብር ፍጥረታትም ከምድር ተለይተው በባህር ውስጥ መኖር አይችሉም የባህር ውርጭ ቅዝቃዜ ይገድላቸዋልና፡፡

#ሚያዝያ_1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፣
፩, ቅዱስ መርቄ ጻድቅ (ክርስቲያናዊ ነጋዴ)
፪, ቅዱስ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም
፫, አባ ሚካኤል ዘእስክንድርያ
፬, #እግዚአብሔር በእግር የሚራመዱ በክንፍ የሚበሩና በልብ የሚሳቡ በየብስ የሚኖሩ ፍጥረታትን ፈጠረ

#ወርኃዊ_በዓላት
፩, በዓታ ለእግዝእትነ #ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
፪, ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
፫, ቅዱሳን ሊቀ ካህናት አበው (ዘካርያስና ስምዖን)
፬, አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
፭, አቡነ ዜና ማርቆስ
፮, አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል

እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም። መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል። መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።(ማቴ. ፭÷፲፬-፲፮)

        ✝️ወስብሐት ለ#እግዚአብሔር✝️