ልብህ ነው
እግርማ ታዛዢ ነዉ..ከላከዉ ሚደርስዉ
እግርህን ላሰርዉ.....ልብህን ጠይቀዉ
እንዳደርስ ላርገህ...... ተራራውን መስሎ
ሳትይዝ ያሳጣህ........ በፍራት ጠቅልሎ
le comment @Amen122119 @gitmv
እግርማ ታዛዢ ነዉ..ከላከዉ ሚደርስዉ
እግርህን ላሰርዉ.....ልብህን ጠይቀዉ
እንዳደርስ ላርገህ...... ተራራውን መስሎ
ሳትይዝ ያሳጣህ........ በፍራት ጠቅልሎ
le comment @Amen122119 @gitmv
የጥቅምት መስክ ነኝ !!
(በእውቀቱ ስዩም)
ሰው ለሰው ይፈርዳል
ልብን ዘልቆ ሳያይ
ላልቃሽ እያዘነ
በፈካ ገፅ ውስጥ ያደፈጠን ስቃይ
-ማነው የመዘነ?
የይስሙላም ይሁን: ከልብ ያለቀሰ
አያጣም አይዞህ ባይ
ካንጀት ይሁን ካንገት : እንባ ላፈሰሰ
አይጠፋም ከምንገድ : መሀረብ አቀባይ
ይብላኝ ላሳሳች ፊት: አፅናኝ ለማይጋብዝ
አንዳንድ ሀዘን አለ
ከላይ ተሰውሮ : ልብ የሚበዘብዝ
የጥቅምት ብሩህ መስክ: አደይ የለበሰ
ስንቱን ጉድ አዝሎታል: ስሩ ከተማሰ!!
የጥቅምት መስክ ነኝ : አደይ ያደመቀው
ፈገግታ ቢውጠው: ዘበት ቢደብቀው
የኔን ብቻ ህመም: እኔው ነኝ የማውቀው::
(ተከፍተው የተከፉ ለማይመስሉ)
(በእውቀቱ ስዩም)
ሰው ለሰው ይፈርዳል
ልብን ዘልቆ ሳያይ
ላልቃሽ እያዘነ
በፈካ ገፅ ውስጥ ያደፈጠን ስቃይ
-ማነው የመዘነ?
የይስሙላም ይሁን: ከልብ ያለቀሰ
አያጣም አይዞህ ባይ
ካንጀት ይሁን ካንገት : እንባ ላፈሰሰ
አይጠፋም ከምንገድ : መሀረብ አቀባይ
ይብላኝ ላሳሳች ፊት: አፅናኝ ለማይጋብዝ
አንዳንድ ሀዘን አለ
ከላይ ተሰውሮ : ልብ የሚበዘብዝ
የጥቅምት ብሩህ መስክ: አደይ የለበሰ
ስንቱን ጉድ አዝሎታል: ስሩ ከተማሰ!!
የጥቅምት መስክ ነኝ : አደይ ያደመቀው
ፈገግታ ቢውጠው: ዘበት ቢደብቀው
የኔን ብቻ ህመም: እኔው ነኝ የማውቀው::
(ተከፍተው የተከፉ ለማይመስሉ)
ሆያ ሆዬ
ድቅን አለ ፊቴ ሳስበው በድንገት፣
ሆያ ሆዬ ስንል ያኔ በልጅነት፡፡
የሙልሙሉ ዳቦ የኩበቱ ሽታ፣
መቼም አይረሳም የቡሄ ትዝታ፡፡
ሆያ ሆዬ ሆ ሆያ ሆዬ፣
ሙልሙሊቷን ስጡኝ እባኮ ጌታዬ፡፡
እዛ ማዶ ሆ አንድ ስንደዶ፣
እዚ ማዶ ሆ አንድ ስንደዶ፣
የዚ ቤት ጌታ ጥርሰ በረዶ፣
"እንለው ነበረ"
ጥርሱ ግን ወላልቆ ቢሆንም ባዶ፡፡
ድቅን አለ ፊቴ ሳስበው በድንገት፣
ጆሮዬን ተሠማው የጅራፉ ጩኸት፣
ተሠማኝ ሙቀቱ የችቦውም እሳት፡፡
ሆያ ሆዬ ሆ ሆያ ሆዬ፣
ሙልሙሊቷን ስጡኝ እባኮ ጌታዬ፡
እዛ ማዶ ሆ አንድ እረኛ፣
እዚ ማዶ ሆ አንድ እረኛ፣
የዚ ቤት ጌታ የኢትዮጵያ አርበኛ፣
" እንለው ነበረ"
ለራሱም ቢያስፈልግ ጠባቂ ዘበኛ፡፡
ዳቦውም ይበላል ችቦው ይለኮሳል፣
ሆያ ሆዬ ተብሎ ቡሄ ይከበራል፡፡
እጅጉን ደነቀኝ ገረመኝ ሳስበው፣
ሆያ ሆዬ ማለት ራሡ ጥበብ ነው፡፡
©Afe.Z.eth @gitmv
ድቅን አለ ፊቴ ሳስበው በድንገት፣
ሆያ ሆዬ ስንል ያኔ በልጅነት፡፡
የሙልሙሉ ዳቦ የኩበቱ ሽታ፣
መቼም አይረሳም የቡሄ ትዝታ፡፡
ሆያ ሆዬ ሆ ሆያ ሆዬ፣
ሙልሙሊቷን ስጡኝ እባኮ ጌታዬ፡፡
እዛ ማዶ ሆ አንድ ስንደዶ፣
እዚ ማዶ ሆ አንድ ስንደዶ፣
የዚ ቤት ጌታ ጥርሰ በረዶ፣
"እንለው ነበረ"
ጥርሱ ግን ወላልቆ ቢሆንም ባዶ፡፡
ድቅን አለ ፊቴ ሳስበው በድንገት፣
ጆሮዬን ተሠማው የጅራፉ ጩኸት፣
ተሠማኝ ሙቀቱ የችቦውም እሳት፡፡
ሆያ ሆዬ ሆ ሆያ ሆዬ፣
ሙልሙሊቷን ስጡኝ እባኮ ጌታዬ፡
እዛ ማዶ ሆ አንድ እረኛ፣
እዚ ማዶ ሆ አንድ እረኛ፣
የዚ ቤት ጌታ የኢትዮጵያ አርበኛ፣
" እንለው ነበረ"
ለራሱም ቢያስፈልግ ጠባቂ ዘበኛ፡፡
ዳቦውም ይበላል ችቦው ይለኮሳል፣
ሆያ ሆዬ ተብሎ ቡሄ ይከበራል፡፡
እጅጉን ደነቀኝ ገረመኝ ሳስበው፣
ሆያ ሆዬ ማለት ራሡ ጥበብ ነው፡፡
©Afe.Z.eth @gitmv