ፈለገ ጥበብ ሚዲያ felegetbeb media
980 subscribers
8.39K photos
102 videos
99 files
1.2K links
ይህ ቻናል የደብረ ዘይት ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ወ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ፈለገ ጥበብ ሰንበት ት/ቤት የመረጃ ሚዲያ እና ህዝብ ግንኙነት ክፍል ሲሆን ይህ ቻናል ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የሆኑ አስተምህሮቶች በየእለቱ የሚለቀቅበት ቻናል ነው ቻናላችን ስለተቀላቀሉ በእግዚአብሔር ፅኑ ፍቅር እናመሰግናለን ።

#የፈለገ_ጥበብ_ሰንበት_ትምህርት_ቤት_የመረጃ_ሚዲያ_እና_ህዝብ_ግንኙነት_ክፍል
#FTM
Download Telegram
+<< #ወይን_ለማይጠጣ_ሕይወቱ_ምንድን_ነው? >>+

"ምንትኑ ሕይወቱ ለዘኢይሰቲ ወይነ" (ሲራክ. 34:26)

=>#ቅድስት_ቤተ_ክርስቲያን ወይንን (ጠላ: ቢራ . . .)
¤"አትጠጡ" ብላ አትከለክልም::
¤ግን ደግሞ "ጠጡ" ብላም አታበረታታም::

¤አልኮል መጠጦችን መጠቀም "ኃጢአት ነው" አትልም::
¤ግን ደግሞ " . . . ካያያዝ ይቀደዳል" እንዲሉ አጠቃቀማችን ወደ ኃጢአት ሊወስደን ስለሚችል "ጥንቃቄን አድርጉ" ትለናለች::

+በዘመናችን ከመጠጥ ጋር በተያያዘ (በተለይ ለክርስቲያኖች) 2 ፈተናዎች ይታያሉ::

1.አብዛኛው የቤተ ክርስቲያናችን ምዕመን (በተለይ ወጣቱና ጐልማሳው) አነሰም በዛም ጠጪ እየሆነ ነው:: (ልብ በሉልን "ይሰክራል" አላልኩም)

2.እጅግ በሚያስቀይም መንገድ ለመጠጣት ጥቅሶች ከቅዱስ መጽሐፍ ሲጠቀሱ እየሰማን ነው::

+በተለይ "#ወይን_ያስተፌስሕ_ልበ_ሰብእ" (መዝ. 103:15) ከእኛው አልፎ በዘፈንና በመገናኛ ብዙኃን ማስታወቂያዎች ላይ ሲጠቀስ ስንሰማ አንጀታችን ካላረረ የቁም ሙት ሆነናል ማለት ነው::

+አሕዛብ ከመጽሐፋቸው አንዲት ዘለላ ብትነካ ሃገሪቱን በተቃውሞ እንደሚንጧት እናውቃለን::

¤እኛ ግን #የሊቀ_ሰማዕታት ስም የቢራ ማሻሻጫ ሲሆን: #ቅዱስ_ቃሉ ለአልኮል መጠጥ ሲጠቀስ: #በአባቶቻችን_ካህናትና_ጻድቃን ላይ በፌዘኞች (ኮሜዲያን ነን ባዮች) ሲቀለድ: ማንም ባለጌ በተቀደሰች ሃይማኖታችን ላይ አፉን ሲከፍት ምንም አይመስለንም:: (አንቀላፍተናላ!!!)

=>ወደ ጉዳዬ ልመለስና የወይንን ነገር እንጨዋወት:: "የትውልዱ ክፋቱ ኃጢአት መሥራቱ አይደለም:: ይልቁኑ ኃጢአቱን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስመሰሉ እንጂ" ብለውኛል የኔታ ክንፈ ገብርኤል:: (በቀኝ ያቁማቸውና!!!)

+ዛሬ በሃገሪቱ የሚገኘውን ጠጪ (ካልጠጣ የሚሞት የሚመስለው) በመቶኛ/በ% ቢሰላ አብዛኛው (ምናልባት እስከ 90 % ) ኦርቶዶክሳዊ ነኝ ባይ ነው::

+ታዲያ ይህ ጥራዝ ነጣቂ ትውልድ ለምን ስትሉት "ዳዊት እንዲህ አለ: ሐዋርያው ቅ/ዻውሎስ እንዲህ አከለ . . ." ይላል::

<< ለመሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጠቀሱ ስለ ወይን መጠጣት የሚናገሩ ቃላት ትርጉም እንደሚባለው ነው??
#ለመሆኑ_ቅዱስ_መጽሐፍ_ጠጪነትን_ያበረታታል??
አምላካችን እግዚአብሔርስ ወደዚህች ምድር ያመጣን ለዚሁ ግብር ነው?? (ሎቱ ስብሐት!!!) >>

+ቅዱስ ቃሉን ለገዛ ፈቃድ መተርጐም ፍጹም ኃጢአት ነው:: (2ዼጥ. 1:20) ስለዚህም "ወይን" የሚሉ ቃላት ምንድን ናቸው? ወደሚለው እንመለስ::

+በመጀመሪያ ግን #ብርሃነ_ዓለም: #ዓዘቅተ_ጥበብ (የጥበብ ምንጭ) #ቅዱስ_ዻውሎስ ለደቀ መዝሙሩ #ቅ/ጢሞቴዎስ ስለ ምን "ውሃ ብቻ አትጠጣ:: ጥቂት ወይን ጨምር" አለው ቢሉ:-

1.ወይን በዘመኑ ለሆድ በሽተኞች ፍቱን መድኃኒት ስለ ነበር ነው:: (ቃሉም የሚለው ስለ ሆድህ ህመም ነው(1ጢሞ. 5:23)) ቅዱሱ ከገድል የተነሳ ሆዱ ፍጹም ሕመምተኛ ነበርና::

2.ወይን መጠጣት በልኩ (ጥቂት) የሆነ እንደሆን አካልን ያለመልማል:: ልቡናን ያረጋጋል:: ግን በጊዜው: በቦታውና በመጠኑ ሲሆን ነው::

+#ቅዱስ_መጽሐፍ ላይ ግን "ወይን" ተደጋግሞ የተጠቀሰባቸው በርካታ መንፈሳዊ ምስጢራት አሉ:: እነዚህን መነሻ ርዕስ ባደረግነው: በቃለ ሲራክ ተመርኩዘን እንመልከታቸው::

=>ነቢዩ "#ወይን_ለማይጠጣ_ምን_ሕይወት_አለው?" ይላል::

1.ወይን=(#ምስጢረ_ሥላሴ)

¤"ምስጢረ ሥላሴን ላላመነ ሰው ምን ሕይወት አለው?" ይለናል:: የእግዚአብሔርን አንድነት: ሦስትነት ሳያምኑ ዘለዓለማዊ ሕይወት የለምና:: (ዮሐ. 1:12, 3:17, ማቴ. 28:19)

+ምስጢረ ሥላሴ በወይን መመሰሉን #አባ_ሕርያቆስ በቅዳሴው "አብ ጉንደ ወይን: ወልድ ጉንደ ወይን ወመንፈስ ቅዱስ ጉንደ ወይን . . ." ሲል ነግሮናል::

2.ወይን=#ክርስቶስ (#ምሥጢረ ሥጋዌ)

¤በወልድ (ክርስቶስ) ያላመነ የዘለዓለም ሕይወት የለውም:: (ዮሐ. 3:36) ስለዚህ ነገር ጌታችን ራሱን የወይን ግንድ: አባቱን ተካይ አድርጐ ሲጠራ እንሰማዋለን:: "#አነ_ውእቱ_ጉንደ_ወይን=እኔ የወይን ግንድ ነኝ" እንዲል:: (ዮሐ. 15:1)

+መዳን የሚቻለውም መድኅን ክርስቶስን "#አምላክ_ወልደ_አምላክ: #ወልደ_አብ_ወልደ_ማርያም: #ሥግው_ቃል" ብሎ ማመን ሲቻል ነው::

3.ወይን=#ድንግል_ማርያም (#ነገረ_ማርያም)

¤ጌታን ወይን ካልን ድንግል ማርያምን #ሐረገ_ወይን: #አጸደ_ወይን ልንላት ግድ ይለናል:: (እሴብሕ ጸጋኪ ዘዘመነ ጽጌ)

+መዳንን የሚሻ ሁሉ እመቤታችን ማርያምን #ወላዲተ_አምላክ መሆኗን: #ዘለዓለማዊ_ድንግልናዋን: ፍጹም ሞገስ ያላት #አማላጅ መሆኗን: #ቅድስናዋንና #ክብሯን ሊያምን ግድ ይለዋል:: (መዝ. 44:9, 86:5, ኢሳ. 1:9, 7:14, ሕዝ. 44:1)

4.ወይን=#ቅዱሳን (#ነገረ_ቅዱሳን)

¤መድኃኒታችን ክርስቶስ ራሱን የወይን ግንድ ብሎ አልቀረም:: ወዳጆቹን #ወአንትሙሂ_አዕጹቂሁ=እናንተ የወይኑ ቅርንጫፎች ናችሁ" ይላቸዋል:: (ዮሐ. 15:5)

+ስለዚህም በቅዱሳን #ክብር: #አማላጅነት: #ፈራጅነትና #የጸጋ_አማልክትነት ልናምን ግድ ይለናል:: (ዘጸ. 7:1, መዝ. 81:1, ማቴ19:28)

5.ወይን=#ሥጋ_ወደሙ (#ምስጢረ_ቁርባን)

¤#እመቤታችን በቃና ዘገሊላ ቸር ልጇን የጠየቀችው ስለጊዜአዊው መጠጥ ቢመስልም ምስጢሩ ግን ለዘለዓለማዊው መጠጥ (ክቡር ደሙ) ነው:: (ዮሐ. 2:1)

+ለዚያም "#ወይንኬ_አልቦሙ=ወይንኮ የላቸውም" ስትለው: "ዓዲ ኢበጽሐ ጊዜየ=እናቴ ሆይ! በቀራንዮ አንባ ሥጋና ደሜን የምሰጥበት ጊዜየ ገና ነው" ሲል የመለሰላት::

+ወንጌል ደግሞ እንዲህ ይላል::
"የክርስቶስን ሥጋውን ካልበላችሁ: ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም::" (ዮሐ. 6:53)

¤የወይን ትርጉም ይቀጥላል . . . ለእኛ ግን እዚህ ላይ ይብቃን::

+ቅዱሱ #ነቢይ_ሲራክ "ወይን ለማይጠጣ ሰው ምን ሕይወት አለው?" ሲል በአንክሮ የጠየቀው ስለዚህ ነው::
¤በወይን በተመሰሉ #በሥላሴ: #በምስጢረ_ሥጋዌ: #በነገረ_ማርያምና #ነገረ_ቅዱሳን ሳያምኑ: ከወይኑ ግንድ ክርስቶስ ጐን በፈሰሰ #ማየ_ገቦ ሳይጠመቁና #ከቁርባኑ ሳይሳተፉ ሕይወት የለምና::

=>ቸር አምላከ ቅዱሳን የምናስተውልበትን አዕምሮ አይንሳን::

<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>