ፒያሳ መሃሙድ ጋ ጠብቂኝ
194K subscribers
280 photos
1 video
16 files
207 links
እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ወግ
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
🎯መነባንብ

#ማንኛውም አይነት ፅሁፎች📕 ከፈለጉ ይቀላቀሉን
የተለያዩ PDF መፅሐፍት ከፈለጉ @Eyosibooks
አስተያየት ካሎት👇👇
☎️• 0922788490

📩@Eyos18
Download Telegram
😎ጠላፊዎቹ

#ክፍል_አርባ_ስድስት

#በኬንፎሌት

#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


መጋዘኑ ውስጥ አምጥቶ ሲወረውራት ክርኗና ጉልበቷ በመጎዳቱ ቁስሉ ጠዘጠዛት፡፡ ‹‹አንተ አሳማ!›› ብላ ፒተርን በሌለበት ተሳደበች፡፡
ጫማዋን አጠለቀችና ቦርሳዋን አንስታ ዙሪያውን ቃኘች። ሌላ በር አገኘችና ለመክፈት ብትሞክርም በጥብቅ የተዘጋ በመሆኑ መክፈት አልቻለችም::

ቤቱ ከባህር ዳርቻው የራቀ ቢሆንም የአይሮፕላኑ ተሳፋሪዎች ወይም
ሌላ ሰው በዚያ በኩል ሊያልፍ ይችላል፡፡ ናንሲም ጉሮሮዋ እስኪሰነጠቅ
‹‹የሰው ያለህ!›› ስትል ጮኸች፡

ጉሮሮዋ ደርቆ ድምጿ እንዳይዘጋ በየአንድ ደቂቃ ልዩነት አንድ ጊዜ
መጣራቷን ቀጠለች፡
ሁለቱም በሮች በወፍራም እንጨት የተሰሩና ግጥም ያሉ በመሆናቸው
ዲጂኖ ወይም ሌላ ብታገኝ ሰብራ ወይም ፈልቅቃ ትከፍተው ነበር፡፡
ምናልባትም አንድ የሆነ የእጅ መሳሪያ አገኝ ብላ አካባቢውን ቃኘች፡፡ የቤቱ
ባለቤት ዕቃውን በስርዓት የሚይዝ ኖሮ የእጅ መሳሪያዎቹን መጋዘኑ ውስጥ አልተዋቸውም፡፡ መጋዘኑ ውስጥ አንድም የሚታይ የአትክልት መኮትኮቻም ሆነ አካፋና ዶማ የለም፡፡

እንደገና ‹‹የሰው ያለህ!›› መልስ የለም፡፡

ቁጭ ብላ መተከዝ ሆነ ያላት አማራጭ፡ ኮቷን ይዛ በመምጣቷ ብርዱ
ብዙም አላስቸገራትም፡፡ መጣራቱን ባታቆምም ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ተስፋዋ
እየተሟጠጠ ሄደ፡ ይሄን ጊዜ ተሳፋሪዎቹ አይሮፕላኑ ላይ እንደገና እየገቡ
ይሆናል፡፡ ጥቂት ቆይቶ እሷን ጥሎ ይበራል፡፡
በአሁኑ ሰዓት እያስጨነቃት ያለው ኩባንያውን ማጣቱ አይደለም፡፡አይበለውና ለሳምንት ያህል ሰው ወደ መጋዘኑ ዝር ባይል ምን ይውጣታል፡ እዚሁ ልትሞት አይደል፡፡ ይህም ጭንቀት ላይ ስለጣላት ያለማቋረጥ
ጩኸቷን አስነካችው፡፡

ጥረቷ ሁሉ አለመሳካቱን ስታውቅ ዝም ብላ ቁጭ አለች፡፡ ፒተር ክፉ
ሰው ቢሆንም ነፍሰ ገዳይ ስላልሆነ እዚህ እንድሞት አይተወኝም ብላ ገመተች፡፡ ሼዲያክ ፖሊስ መምሪያ ስልክ ደውሎ ከመጋዘኑ እንዲያወጧት ይነግራቸው ይሆናል፡፡ ነገር ግን ከቦርድ ስብሰባው በፊት
አይነግራቸውም፡፡ ያለችበት ቦታ የማያሰጋ ቢሆንም ስጋት መፍጠሩ አልቀረም፡ ፒተር ካሰበችው በላይ ጨካኝ ቢሆንስ! ቢረሳትስ? ቢያመውስ?
ወይም የሆነ አደጋ ቢገጥመውስ? ታዲያ ከዚህ ማጥ ውስጥ የሚያወጣት
መቼም ማነው?

የአይሮፕላኑ ሞተሮች ሲያስገመግሙ ስትሰማ የነበራት ተስፋ ሁሉ ጨለመ  የገዛ ወንድሟ ለክፉ እንደዳረጋት መርቪንም ሊደርስላት እንደማይችል አወቀች፡፡ መርቪን ይህን ጊዜ አይሮፕላኑ ውስጥ ቁጭ ብሎ የአይሮፕላኑን መነሳት እየጠበቀ ይሆናል፡፡ አይሮፕላኑ ውስጥ ሲያጣት ‹ምን ሆና ይሆን?› ማለቱ ባይቀርም በመጨረሻ የተለያዩት ‹‹አንተ ጅል!›› ብላ ሰድባው ስለሆነ ከእሷ ጋር አብቅቷል ብሎ ያስብ ይሆናል፡፡እንግሊዝ አገር ተከትለሽኝ  ነይ ማለቱ ብልግናውን ያሳያል፡ ሆኖም
ማንም ወንድ ይህን ስለሚል መናደድ አልነበረባትም፡፡ የተለያዩት በጥል ስለሆነ ካሁን በኋላ እንደማታገኘው ተገነዘበች፡፡ ‹‹ኩባንያዬንም ተነጠቅሁ፣
መርቪንንም ተነጠቅሁ፣ በረሃብም እሞታለሁ›› ስትል አላዘነች፡፡

ጉንጯ ላይ የፈሰሰውን እንባ በእጅጌዋ ጠረገች፡፡ ከእዚህ ችግር ለመውጣት ወገቧን ጠበቅ ማድረግ እንዳለባት ተገነዘበች፡፡ ከዚህ መውጪያ መንገድ መኖር አለበት፡፡ በዙሪያዋ በሩን ለመስበር የሚጠቅም አንዳች መሳሪያ ካለ ቃኘች፡ ግድግዳውን በጥፍሮቻቸው ፍቀው ከእስር ያመለጡ እስረኞች እንዳሉ  አስታወሰች፡፡ እሷ ደግሞ የዓመታት ጊዜ
የላትም፡፡ ከጥፍር የጠነከረ መሳሪያ ያስፈልጋታል፡፡ ቦርሳዋን ፈታተሸች፡፡
ከዝሆን ጥርስ የተሰራ ማበጠሪያ፣ ሊፒስቲክ፣ መሃረብ፣ የባንክ ቼክ ቡክ፣
ገንዘብ፣ ከወርቅ የተሰራ ብዕር አላት፡፡ ሁሉም በር ለመክፈት አይጠቅሙም
የለበሰችውን ልብስ ተመለከተች፡፡ ቀበቶ ታጥቃለች: የቀበቶ ማያያዣው
ምናልባት በሩን ለመቦርቦር ሊጠቅም ይችል ይሆናል፡ ቡርቦራው ረጅም ጊዜ
ሊወስድ ይችላል ነገር ግን ከዚህ ሌላ አማራጭ የለም፡፡

ወደ በሩ አመራች፡፡ በሩ ከወፍራም እንጨት የተሰራ ነው፡፡ በሩን በሙሉ መቦርቦር አይኖርባትም፡፡ የተወሰነ ጥልቀት ከቦረቦረች ሊሰበር ይችላል፡፡ እንደገና ለእርዳታ ተጣራች፡፡ የሚሰማ የለም፡፡ቀበቶዋን ስትፈታ ቀሚሷ ወለቀ፡  ከዚያም ቀሚሷን አጠፈችና
አስቀመጠችው፡ የሚያያት ሰው ባይኖርም የሚያምር ፓንት አድርጋለች፡፡

በአራት ማዕዘን ቅርጽ ቦረቦረች፡ የቀበቶው ማያያዣ ጠንካራ ባለመሆኑ
ተጣመመ: ቢሆንም ቡርቦራዋን ቀጠለች፡፡ በመሃል በመሃል የድረሱልኝ
ጥሪዋን ታሰማለች፡፡ በትዕግስት ስትፈቀፍቅ የእንጨት ፍግፋጊ መሬቱ ላይ መርገፍ ጀመረ፡፡ እንጨቱ ለስለስ ያለ ነው፡፡ አየሩ እርጥበት ስላለው
ቡርቦራዋን በተስፋ ቀጠለች፡፡ ስትቦረቡር የቀበቶው ማያያዣ እየወለቀ
ያስቸግራታል፡፡ እያነሳች ትቀጥላለች፡፡  አምስት  ስድስት ጊዜ እየወደቀ
እያነሳች ብትቦረቡርም ስራው ፈቀቅ አልል ሲላት ለቅሶዋን ለቀቀችው፡
በሲቃ በሩንም በጡጫ ደበደበች፡፡

ከውጨው ድምጽ ተሰማ፡፡ ‹‹ሰው አለ እዚህ›› አለ ድምጹ፡፡

ድምጹን ስትሰማ በሩን መደብደቧን አቆመች፡፡ በትክክል ድምጽ
ሰምታለች፡፡ ‹‹የሰው ያለህ! ከዚህ አውጡኝ›› አለች፡፡
‹‹ናንሲ አንቺ ነሽ?››
ናንሲ ልቧ በደስታ ዘለለ፡፡ የሰማችው ድምጽ የእንግሊዛውያን ቅላጼ
ያለው ነው፡፡ ድምጹንም አወቀችውና ‹‹መርቪን! ተመስገን አምላኬ!›› አለች፡፡
‹‹አንቺን ያልፈለግሁበት ቦታ የለም፡፡ እዚህ ምን ትሰሪያለሽ?››
‹‹ከዚህ ማጥ አውጣኝ መርቪኔ››

መርቪን በሩን ነቀነቀው፡፡ ‹‹ተዘግቷል!›› አላት
‹‹በጎን በኩል ና››
‹‹መጣሁ››
‹‹መርቪን?!››
‹‹በሩ ተቀርቅሯል፡፡ ትንሽ ጠብቂኝ›› አለ መርቪን፡፡
‹‹በፓንትና በስቶኪንግ ብቻ መሆኗ ትዝ አላትና ገላዋን በኮቷ ሸፈነች፡
ጥቂት ደቂቃ ቆይቶ በሩ ወለል ብሎ ተከፈተ፡፡ ሮጣ መርቪን ደረት ላይ
ተለጠፈች፡፡ ‹‹እዚህ ሞቼ እቀር ነበር›› አለችና ለቅሶዋን ለቀቀችው::
መርቪንም ደረቱ ላይ እንደተለጠፈች ጸጉሯን እያሻሽ ‹‹አይዞሽ
አይዞሽ!›› አላት፡፡
‹‹ፒተር ነው እዚህ የዘጋብኝ›› አለች ዓይኗ እምባ አቆርዝዞ::
‹‹ይሄ ወንድምሽ የሆነ በድብቅ የሚሰራው ነገር ሳይኖር አይቀርም፡፡
ወንድምሽ ርጉም ሰው ነው፡፡››
በአሁኗ ደቂቃ ናንሲ  ስለወንድሟ ሳይሆን ስለመርቪን ነው
የምታስበው፡፡ በእምባ በተንቆረዘዙ ዓይኖቿ መላ አካላቱን ቃኘችና ጊዜ
ሳታጠፋ ፊቱን አገላብጣ ሳመችው፡፡ ለጠቀችና ከንፈሮቹን በስሜት
ጨመጨመቻቸው፡ በዚህ ጊዜ የወሲብ ፍላጎቷ በእጅጉ ተነሳሳ፡፡ እሱም
አላሳፈራትም፡፡ እጆቹን ሰደደና ደረቱ ውስጥ ከቶ እቅፍ አደረጋት፡ እሷም
የእሱን ገላ ስለተራበች ከእቅፉ ውስጥ መውጣት አልፈለገችም፡: እጆቹን ወደ
ቂጧ ሲሰድ ፓንቷን ነካና ደንገጥ ብሎ አቆመ:

‹‹ቀሚስሽ የት ሄደ?›› ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹በሩን ለመፈግፈግ ብዬ ቀበቶዬን ፈትቼው ስለነበር ቀሚሴም ያለቀበቶ
ወገቤ ላይ መቆም ስላልቻለ አሽቀንጥሬ ጣልኩት›› አለች እየሳቀች፡፡
‹‹እንዴት ጥሩ አጋጣሚ ነው›› አለና እጁን ሰዶ ቂጧንና ጭኗን መደባበስ ያዘ፡፡ በዚህ ጊዜ ብልቱ ቆሞ ሆዷን ሲነካካት ታወቃት፡ እሷም ሱሪው ውስጥ እጇን ከታ ብልቱን ታሻሸው ጀመር፡
📕ታምራተ_ኬድሮን

#ክፍል_አርባ_ስድስት

#ተከታታይ ልቦለድ

#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

‹‹የአባትሽ ዘመዶች ነው ያልከው….?››

‹‹አዎ የአባትሽ ወገኖች … ይሄንን ተክል በምድር ላይ  እንዲበቅል አድርገው ሲበትኑት ለመድሀኒትነት እንዲሆን አስበው አይደለም…››

‹‹እና ለምድነው….?››

‹‹አንቺን ለማግኘት….››ብሎ ጭራሽ ግራ አጋባት

‹‹እንዴት አድርገው ነው እኔን የሚያገኑኝ…….?ደግሞ የት ናቸው….?››

‹‹የት እንዳሉማ ታውቂለሽ….››

‹‹እና እንዴት ነው የሚያገኙኝ ….?››

‹‹ልክ  ያቺን ተክል ስትቀነጥሺ ቀጥታ መልእክቱ እነሱ ጋር ይደርሳል››

‹‹እወነትህን ነው….?››ውስጧ ፈነጠዘች..አባቷ የማግኘት ምኞት ሳታስበው አዘለላት..የእናቷን እውነት የማረጋጋጥ ፍላጎት…

‹‹እና አሪፍ ነዋ..ያለሁበትን ካወቁ ይመጣሉ አይደለ..….?አባቴም ይመጣል አይደል….?››ጠየቀችው

‹‹አይ አባትሽ በጥብቅ እስር ላይ ስላላ መምጣት አይችልም.. ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ ሳይፈቀድለት  ከሰው ጋር በፍቅር በመቆራኘትና አንቺን ስለወለደ ይሄው ባንቺ እድሜ ሙሉ እንደታሰረ ነው››አንጀቷ ተላወሰ..በምድር ላይ ታስሮ ቢሆን ኖሮ  የፈጀውን ያህል   ይፍጅ  እንጂ   መንግስትንም ገልብጣ ቢሆን አባቷን ታስፈታው ነበር

‹‹እና ታዲያ ዘመዶቹም ቢሆን ይምጡ ምን  ችግር አለው….?››

‹‹ሚመጡት  አንቺን ለመውሰድ ነው››

ደስ አለት..ደነገጠችም ‹‹ወዴየት ነው የሚወስድኝ….?››

‹‹ወደራሳቸው አለም….››

‹‹እኔ መሄድ ካልፈለኩስ….?››
‹‹ፈለግሽም አልፈለግሽም ይወስዱሻል …ምንም አይነት ምደራዊ ኃይል አንቺን ከመውሰድ አያግዳቸውም….››

ለአምስት ደቂቃ በትካዜ  ውስጥ ገባች…ሌላ አለም የማየት ፍላጎት… አባቷን እና ዘመዶቹን የማወቅ ፍላጎት..ደግሞ ይህቺን ምድርስ….?

‹‹ቆይ ሄጄ ሁሉን ነገር ካየሁ በኃላ ተመልሼ ወደምድር መምጣት አልችልም….?››

‹‹አይመስለኝም… ብትመለሺም እንደዚህ ሆነሽ አይደለም…ሙሉ በሙሉ ተቀይረሽ.. ሙሉ በሙሉ እነሱን ሆነሽ..የእነሱን ተልዕኮ ለማስፈፀም ነው ሚሆነው.ያ በእነሱ ፍቃድ ላይ የተመሰረተ ነው.ከፈለጉ እስከወዲያኛው ዳግመኛ ምድርን ላትረግጪ ትችያለሽ፡፡››

‹‹በቃ ይሁን.. ለእኛም እዛ መኖር ይሻለናል..የተለየ ዓለም  እኮ አሪፍ ነው..ይቺን ዓለም እንደሆነ በተቻለ መጠን በርብረናታል…ምን ይቀርብናል….?››

‹‹እና ወሰንሽ››

‹‹አዎ ባክህ እንደውም አሪፍ እድል ነው››
እንግዲያው ተዘጋጂ… ከአምስት ደቂቃ በኃላ ሄደሽ መቀንጠስ ትችያለሽ..ከቀነጠስሽ በኃላ ግን አንድ ሳምንት ብቻ ነው በምድር የመቆየት እድል የሚኖርሽ… ልክ የዛሬ ሳምንት በዚህን ሰዓት ካለሽበት ቦታ መጥተው ይዘውሽ ይፈተለካሉ››

‹‹አንድ ሰምንት..አንድ ሳምንት ፈጠነ..ግን ቢሆንም ቀላል ቀን አይደለም….ብዙ ነገር እንሰራበታለን…እናቴን ሄደን እንሰናበታለን..የልጅነት ጎደኞቼን እሰናበታለሁ… አሪፍ ነው..አንድ ሳምንት ይበቃናል..››አለችና ወደተክሏ ተራመደች..
ደረሰችና ልክ ድፍን  6 ሰዓት ሲሆን  ከብሳናው ዛፍ ቅርንጫፎች መካከል  እጇን ዘረጋችውና ጨበጠችው… ቀነጥሰዋለሁ ስትል በእጇ ሟሞና እንደቅባት ተሙለጭልጮ ወደሰውነቷ ሲገባ ታወቀት… ደነገጠች የቀነጠስችው መስሏት ነበር… እጇ ላይ ግን ምንም ነገር የለም… እጇ  የተለየ ቀለም እያመጣ ነው ..ሀመራዊ እሳት መሰል ቀለም… በመላ ሰውነቷ እየተራወጣ ከተዳረሰ በኃላ አንዘርዝሮና አንቀጥቅጦት በአፏ የቴንስ መጫወቻ የምታክል ድብልብል እሳት ብልቅ ብሎ በመውጣት እንደሮኬት ተተኩሶ ወደሰማይ ተምዘገዘገ ..እያየችው  አየሩን ሰንጥቆ ተሰወረ..ግራ ጋባት …እንደምንም ለመረጋጋት እየሞከረች ወደንሰሯ አዕምሮ ተመለስችና ‹‹ምን እየሆነ ነው….?››ጠየቀችው
‹‹በቃ ጨርሰናል እንሄድ››
‹‹እንዴ መቀንጠስ አልቻልኩም እኮ ..እጄ ላይ ምንም የለም….?››
‹‹እጅሽ ላይ ምን ያደርግልሻል …ተክሉ እኮ በመላ ሰውነትሽ ገብቶ ተዋሀደሽ..አሁን መዳኒቱ ተክሉ ሳይሆን አንቺ ራስሽ ነሽ..በዚህ የሳምንት ጊዚ ውስጥ የፈለግሽውን ማዳንም የፈለከግሽውን መግደልም  ትችያለሽ..››

‹‹ደስ ሲል ››

‹‹ደስ አይልም…››አለና ከመጣ ጀምሮ ተዘፍዝፎበት ከነበረው ቋጥኝ ላይ ክንፉን አርገፍግፎ ተነሳን ማጅራቷን ይዞ ወደሰማይ ተምዘገዘገ  ….ወደጀርባዋ ዞረና ተጣበቀባት…  ወደ አዲስአባ ተመልሰው እቤታችን ሲደርሱ ከምሽቱ 8 ሰዓት አልፎ ነበር… …

‹‹ወይኔ ድክም ብሎኛል..ግን መድሀኒቱን ስላገኘን ከአባቴ ወገኖችም ጋር ልንገናኝ ስለሆነ ደስ ብሎኛል…አንተስ ደስ አላላህም….?››ለመተኛት ወደ አልጋዋ እያመራች ነበር ምትናገረው

‹‹በጣም ከፍቶኛል››አላት ንስሯ

ደነገጠች‹‹ለምን….?››

‹‹ከንቺ ጋር የምኖረው ..በህይወትም የምቆየው ለሳምንት ብቻ ስለሆነ››

በህይወቷ እንደዚህ አይነት ድንጋጤ ደንግጣ አታውቅም.‹‹.እንዴ የእኔ ንስር ሟች ፍጡር ነው እንዴ…….?›ብላ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰበችብት ጊዜ ነው

‹‹ጥዬህ የምሄድ መስሎህ ነው..አብረን እኮ ነው የምንሄደው››

‹‹ይዘሺኝ መሄድ አትቺይም››

‹‹ለምን….?››

‹‹እኔ መጀመሪያም ከዛ ነው የመጣሁት…ለአባትሽ ብዬ እና አሁን ተመልሼ ለመሄድ ፍፅም አይፈቀድልኝም፡፡››

‹‹በቃ ይቀራላ ..እስከዛሬ ካንተ  ጋር እንጂ ከእነሱ ጋር አልኖርኩ.. ምን  ያደርጉልናል እነሱ መቅረት ይችላሉ››

‹‹እሱማ ጊዜው አለፈ..ቅድም ከአፍሽ የወጣችው እሳት አነሱ ጋር መልዕክት ይዛ የምትሄድ ነች…ወደድሽም ጠላሽም አንቺን ይወስዱሻል..እኔ ደግሞ ካለአንቺ ህይወት የለኝም …ተነጥለሺኝ እንደሄድሽ ወዲያው በዛኑ ሰዓት እሞታለሁ..››

‹‹እንዴ  እሞታለሁ ማለት ምን ማለት ነው….?ይሄንን ታዲያ ተክሉን ከመቀንጠሴ በፊት ለምን አልነገርከኝም….?››

‹‹ውሳኔሽ በእኔ ላይ እንዲመሰረት ስላልፈለኩ ››

‹‹ያምሀል እንዴ . ….?.ካንተ ሚበልጥብኝ ነገር አለ…….?

ህይወቴ እኮ ነህ..››አበደች ጮህች ፕሮፌሰሩ ከእንቅልፋቸው ባነው በራፏን እስኪያንኮኩ ድረስ ግቢውን አተረማመችው …፡፡

     ይቀጥላል

#ክፍል 47,,እንዲለቀቀ (15) ሰው ከስር ያለውን ሊንክ #Subscribe🔔ካረገ ይለቀቃል
https://youtube.com/@Weygud18

#Subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ ስለምትሆኑ እናመሰግናለን #Subscriber
YouTube link👇
https://youtube.com/@Weygud18

መልካም ምሽት ተመኘሁ🙏
🎙ግሩፑን ለማግኘት
              👇👇👇

        @Mtshaf_bicha
        @Mtshaf_bicha
❤️ለወዳጅዎ #ሼር ያድርጉ
👉አሰተያየት ካላችሁ
📩 @Eyos18     አድርሱን
             📗📒📕📗📒📕
                Join&share
                  @EyosC1
       📚ማንበብ ባህላችን ይሁን📚
┄┉┉✽‌»‌🎶••✿••🎶»‌✽‌┉┉┄