የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
992 subscribers
1.5K photos
4 videos
1 file
51 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
ሙስናና ብልሹ አሰራር ለመግታት ባለሙያን በእውቀትና በስነ-ምግባር ማነፅ እንደሚያስፈልግ ተገለፀ

09/02/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2ኛ ዙር ሙያዊ ተላብሰው አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል ከ2100 በላይ ለፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በአስራ አንዱም ክፍለ ከተሞች የስነ-ምግባር መመሪያ ቁጥር 3/2015 እና በፀረ ሙስና ላይ የአቅም የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ።

ባለስልጣኑ ለመሚያስተዳድራቸው ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በስነ-ምግባር መመሪያ እና ብልሹ አሰራር በሀገር ላይ የሚያደርሱ ጉዳቶች በተመለከተ ስልጠና በመስጠትና ግንዛቤ በመፍጠር በቀጣይ በብልሹ አሰራር ተግባር ውስጥ ገብተው የተገኙ ኦፊሰሮች ላይ ጠንከር ያለ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።

የባለስልጣኑ የስነ ምግባር እና የፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ ሙስናና ብልሹ አሰራር ለመግታት ባለሙያን በእውቀትና በስነ-ምግባር ማነፅ እንደሚያስፈልግ ገልፀው ሰልጣኞች በሰለጠኑት መሰረት ህብረተሰቡን በመመሪያው መሰረት በሙያዊ ስነምግባር ማገልገል እንደሚጠበቅባቸው ገልፀዋል።

ስልጠናው በሦስት ዙር የሚሰጥ ሲሆን መጀመሪያው በተሰጠው የስነ-ምግባር መመሪያ ስልጠና 2000በላይ ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠናው የወሰዱ ሲሆን በቀጣይ 3ኛ ዙር ለ2100 ፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና እንደሚሰጥ ተጠቁሟል።

ዘገባው ፦ የአዲስ አባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
የባለስልጣኑ እየሰጠ ያለው የፖራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና ህግና መመርያን ተከትለው እንዲሰሩ የሚያስችል መሆኑ ተገለፀ

10 - 02 - 2017 ዓ.ም
*አዲስ አበባ*

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች በተለያዮ ርዕሰ ጉዳዬች ዙሪያ የሚሰጠውን የሁለተኛ ዙር ስልጠና ሁለተኛ ቀን የአቅም ግንባታ ስልጠና በሁሉም ክፍለ ከተሞች በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ ውሏል ።

ሰልጠናው በዛሬው እለት በዲስፕሊን መመሪያ ቁጥር 3/2015 ዓ.ም ዙርያ እና በተሻሽው በደንብ ቁጥር 167/2016 ዓ.ም ላይ በተሻሻሉ የቅጣት እርከኖቹን ላይ የዲስፕሊን ጥፋቶች እና በቅሬታ አቀራረብ ሂደቶች ላይ የተሰጠ ሲሆን በነገው ዕለትም ስልጠናው የሚቀጥል ይሆናል ።

የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ ኮ/ር አህመድ መሐመድ እና የስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ላቀች ሀይሌ ስልጠናው የሚሰጥ በትሂደት ጉብኝት በማድረግ ሰልጣኞችና አሰልጣኞች አበረታተዋል ።

በስልጠናው የደንብ ጥሰቶችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች የስነ ምግባር ግድፈት እንዳይፈፅሙ ፣ በስነ ምግባር የታነፁ እንዲሆኑና ህግና መመርያን ተከትለው እንዲሰሩ የሚያስችል መሆኑ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ ኮ/ር አህመድ መሐመድ ገልፀዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች ስልጠናው በእውቀትና መብትና ግዴታቸው ለመስራትናለስራቸው እጅግ አስፈላጊ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ከመድረክ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

ዘገባው :- የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።