የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን Addis Ababa Code Enforcement Authority
1.36K subscribers
2.65K photos
5 videos
1 file
63 links
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
Download Telegram
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር የግንዛቤ ማስጨበጫ የህዝብ ውይይት መድረክ አካሄደ

22/03/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በህገ-ወጥ እንሰሳት እርድና ዝውውር ላይ የሀይማኖት አባቶች፣አባ ገዳዎች ፣ሀደ ሲንቄዎች፣ሲቪክ ማህበራት፣ታዋቂ ግለሰቦች፣ የእድር መሪዎች፣የብሎክ አስተባባሪዎች፣ሴቶች፣ወጣቶች፣ ሰላም ሰራዊት፣የልኳንዳ ቤት ባለቤቶች በተገኙበት በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄና የህዝብ ውይይት መድረክ አካሄደ።

መድረኩ በሀይማኖት አባቶች፣በሀገር ሽማግሌዎች እና አባ ገዳዎች ምርቃት የተጀመረ ሲሆን በመድረኩ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ ተክሉ እንደተናገሩት ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ለህብረተሰቡ በደንብ መተላለፎች ላይ ሰፊ ግንዛቤ እየፈጠረ መሆኑን ገልፀው በዛሬው ዕለትም በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር ላይ ለህብረተሰቡን ግንዛቤ በመስጠት በጋራ በመስራትእንደሚገባ ገልፀዋል።

አክለውም እራሳችንን ከተለያዩ በሽታዎች እና ጤንነቱ ያልተረጋገጠ ስጋዎችን በየወንዝ ዳርቻዎች ፣በየአካባቢያችሁ ጨለማን ተገን አድርጎ ባልተፈቀደ ቦታ ፣በግለስብ ቤቶች ከሚታረዱ ህገወጥ እርዶች ከመመገብ እንቆጠብ ሲሉ አሳስበዋል።

በእለቱ ህገወጥ እርድ ሲከናወን ከህብረተሰቡ የተደበቀ አይደለም ከዚህ ጋር ተያይዞ ደንብ ተላልፈው ሲገኙ ጥቆማ በመስጠት እና ከተቋሙ ጎን በመቆም ደንብ መተላለፍን መቀነስ እና ማጥፋት እንደሚቻል ገልፀው ደንብ ተላልፎ የሚገኝ ማንኛውም ግለሰብ ይሁን ድርጅት ደንብና መመሪያው ባስቀመጠው መሰረት እርምጃ እንደሚወሰድበት ተገልጿል ፡፡

በመድረኩም የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የስልጠና ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ጌታሁን ኃብተ ማሪያም በህገወጥ እርድና እንሰሳት ዝውውር ሰነዶችን አዘጋጅቶ በማቅረብ ሰፊ የህዝብ ውይይት ተካሂዷል፡፡

በመጨረሻም ህብረተሰቡ ከደንብ ማስከበር ጎን ለመስራት ተነሳሽነት መኖሩን ገልፀው ከመድረኩ የተነሱትን ሀሳብና አስተያየት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ ተክሉ፣የደንብ መተላለፍ መከላከል እና ስልጠና ስራዎች አስተባባሪ ወ/ሮ ንፁህ ታጠቅ፣የስልጠና ቡድን መሪ አቶ ጌታሁን ኃ/ማሪያም በጋራ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ተጠናቋል፡፡

በአዲስአለም ከፈለኝ
👍76
የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰራተኞች የስራ ልምድና ተሞክሮ ልውውጥ አደረጉ

23/03/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰራተኞች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጋር በህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራዎችላይ የልምድና ተሞክሮ ልውውጥ አደረጉ።

በልምድ ልውውጡ ላይ የትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበበ ቸርነት ስለ ተቋማቸው ተግባር እንዲሁም የስራ ክፍሉን መዋቅርና ዝርዝር ስራዎችን ሰፊ ገለፃ አድርገዋል።

በልምድ ልውውጡ ወቅቱን የሚጠይቀው የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ስራዎችን በማዘመን የተሻለ የመረጃ ምንጭ መሆንእንደሚገባ ተገልጿል።

በተቋሙ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት እየተተገበሩ ያሉ የህዝብ ግንኙነት፣የህትመት ውጤቶች ፣የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምና የመረጃ አደረጃጀትና ተደራሽነት ስራዎች ዙሪያ ማብራሪያና በመስጠት የስራዎች ምልከታ ተደርጓል ።

የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን ማሳደግ ስራዎችን ወደ ህብረተሰቡ ለማድረስ ከፍተኛ ጠቀሜታ መኖሩንና ስራዎች በሚሰሩበት ወቅት እና ለህብረተሰቡ ተደረሻ ሲደረግ ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ሊሆን እንደሚገባ አቶ አበበ ገልጸዋል ።

የባለስልጣኑ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ ለተደረገላቸው የልምድና ተሞክሮ ማጋራት አመስግነው ከትምህርት ቢሮ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም፣የመረጃ አደረጃጀት አና የሚዲያ ሞኒተሪንግ ተግባራትን የወሰዱትንም ልምድ ወደ ተቋማቸው በማምጣት የኮሙኒኬሽን እና የህዝብ ግንኙነት ስራዎች አጠናክረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

መረጃው ፡-የአዲስ አበባ የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍41
የፈጠራ ባህል መፍጠር (creating a culture of creativity) እና ከማህበረሰብ ጋር ያለ ተግባቦት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

ህዳር 23/2018

ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለማዕከል ዳይሬክተሮች ፣ ቡድን መሪዎች ፣ ለክፍለ ከተማ ቡድን አስተባባሪዎች እና የስልጠና ባለሙያዎች የፈጠራ ባህል መፍጠር (creating a culture of creativity) እና ከማህበረሰብ ጋር ያለ ተግባቦት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ባለስልጣኑ የግንዛቤ ፈጠራ ላይ ትኩረት በመስጠት በርካታ ስራዎች እየሰራ መሆኑንና በዚህም የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሩን በተለያዩ ዙሮች ማሰልጠኛ በማስገባት ስልጠና እየሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል ።

የዛሬው ስልጠናም የፈጠራ ባህልን እንዴት ማሳደግ እንደሚቻልና ተቋማዊ ተግባቦት እንዴት መፍጠር እንደሚቻል የሚያሳይ ስለሆነ የሚሰጡትን ስልጠናዎች በትኩረት በመከታተል እንደሚገባ አሳስብዋል ።

የፈጠራ ባህል መፍጠር (creating a culture of creativity) እና በተግባቦት ክህሎት ስልጠና በአዲስ አበባ ከተማ አመራር አካዳሚ ከፍተኛ አሰልጣኝ አቶ ወልደመድህን መኮንን ተሰጥቷል።

ከማህበረሰብ ጋር ያለ ተግባቦት ዙርያ ስልጠና የሰጡት የአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ የከተማ አመራር ልማት ዳይሬክተር እና ከፍተኛ አሰልጣኝ የሆኑት ወ/ሮ ነፃነት የምሩ ሲሆኑ ተግባቦት ለአንድ ተቋም ስኬትና ውጤት አንዱ መለኪያ እነደሆነ፣ የመሪና የተመሪ ተግባቦት ለስራ ቅልጥፍና እንደሚጠቅም ፣ ለአገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት ጉልህ ሚና እንዳለው እና በተቋም ውስጥ ያሉ ሰራተኞች ጤናማ ተግባቦት እንደሚኖራቸው በስልጠናው ተመላክቷል ።
4
የጨረታ ማስታወቂያ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከዚህ በታች የተዘረዘሩት እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።