ለስድስተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የምስጋና፣የእውቅናና ሽልማት ፕሮግራም ተካሄደ
07-10 -2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለስድስተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ከስልጠና ጀምሮ እስከ ምርቀት ፕሮግራም መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሳሬም ሆቴል የምስጋና እና እውቅና ፕሮግራም ተካሄደ ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የስድስተኛ ዙር ስልጠና እንዲከናወን ሌት ተቀን በመስራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የባለስልጣኑ እና አጋር ተቋማት ሰራተኞች በተቋሙ ስም ምስጋና አቅርበዋል።
አክለውም በስራውም ላይ በመተባበር ከተማዋን ከደንብ መተላለፍ የጸዳች ለነዋሪዎቿ እና ለእንግዶች ምቹ ማድረግ ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል ።
የእለቱ የክብር እንግዳ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊድያ ግርማ ስልጠናው በታሰበለት ግብ ውውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከታችሁ አካላት በሰላምና ጸጥታ ስም ምስጋናቸውን አቅርበው የተሰጣችሁ እውቅናና ምስጋና ለቀጣይ ተጨማሪ ኃላፊነትም ጭምር እንዲሆን ለማስታወስ እወዳለሁ ብለዋል።
ከተማችን ከመዘመኗ ጋር አብሮ የዘመነ የጸጥታ ሀይልና ደንብ አስከባሪ ሰራዊት ያስፈልጋታልበዚህ አግባብ የደንብ ስራንም በማጠናከር ፈረቃውን ወደ ሶስት በማድረግ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች ላይ በቁርጠኝነት መከላከል እንደሚገባ ክብርት ወ/ሮ ሊድያ ግርማ አሳስበዋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
07-10 -2017 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለስድስተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ከስልጠና ጀምሮ እስከ ምርቀት ፕሮግራም መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሳሬም ሆቴል የምስጋና እና እውቅና ፕሮግራም ተካሄደ ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የስድስተኛ ዙር ስልጠና እንዲከናወን ሌት ተቀን በመስራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የባለስልጣኑ እና አጋር ተቋማት ሰራተኞች በተቋሙ ስም ምስጋና አቅርበዋል።
አክለውም በስራውም ላይ በመተባበር ከተማዋን ከደንብ መተላለፍ የጸዳች ለነዋሪዎቿ እና ለእንግዶች ምቹ ማድረግ ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል ።
የእለቱ የክብር እንግዳ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊድያ ግርማ ስልጠናው በታሰበለት ግብ ውውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከታችሁ አካላት በሰላምና ጸጥታ ስም ምስጋናቸውን አቅርበው የተሰጣችሁ እውቅናና ምስጋና ለቀጣይ ተጨማሪ ኃላፊነትም ጭምር እንዲሆን ለማስታወስ እወዳለሁ ብለዋል።
ከተማችን ከመዘመኗ ጋር አብሮ የዘመነ የጸጥታ ሀይልና ደንብ አስከባሪ ሰራዊት ያስፈልጋታልበዚህ አግባብ የደንብ ስራንም በማጠናከር ፈረቃውን ወደ ሶስት በማድረግ በከተማዋ የሚስተዋሉ የደንብ መተላለፎች ላይ በቁርጠኝነት መከላከል እንደሚገባ ክብርት ወ/ሮ ሊድያ ግርማ አሳስበዋል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
ባለሥልጣኑ የቀጣይ 90 ቀናት እቅድ በተመለከተ ከማዕከል ሰራተኞች ጋር ውይይት አደረገ
ሰኔ 9/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የቀጣይ 90 ቀናት እቅድ በተመለከተ አና በኢትዮ ኮደር የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙት ከማዕከል ሰራተኞች ጋር በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ የውይይት አካሂዷል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በቀጣይ 90 ቀናት በይበልጥ ሰው ተኮር ስራዎች የሚሰሩበት እንደመሆኑ ሁሉም የበኩሉን መወጣት እንደሚገባ እና የኢትዮ ኮደር ስልጠናንም ሁሉም ሰራተኛ ሊተገብር እንደሚገባ ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተሰጥቷል።
የባለስልጣኑ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ በሆኑት በአቶ ሚሊዮን ካሳሁን አማካኝነት ስለ ኢትዮ ኮደር ምንነት፣5ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ምንድን ነው፣የፕሮግራሙ አለማ፣ ያሉ ፕሮግራም እና አጠቃቀም አስመለክቶ በዝርዝር አቀርቧል ።
የባለስልጣኑ የ90 ቀናት እቅድ በተመለከተ ባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ በአቶ ንጋቱ ዳኛቸው አማካኝነት አቀርቧል ።
በዕቅዱ ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴን መከላከል መቆጣጠር ፣ የአረንጓዴ አሻራና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ በችግኝ ተከላ ፣ቤት እድሳት ፣ማዕድ ማጋራት እንዲሁም የኮሪደር ልማት እና የመሰረት ልማት ጥበቃ ስራዎችን በተሳካ ሁኔታ ሊከናወኑ እንደሚገባ ዕቅዱ በዝርዝር አቀርቧል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
ሰኔ 9/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የቀጣይ 90 ቀናት እቅድ በተመለከተ አና በኢትዮ ኮደር የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙት ከማዕከል ሰራተኞች ጋር በባለስልጣኑ መሰብሰቢያ አዳራሽ የውይይት አካሂዷል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በቀጣይ 90 ቀናት በይበልጥ ሰው ተኮር ስራዎች የሚሰሩበት እንደመሆኑ ሁሉም የበኩሉን መወጣት እንደሚገባ እና የኢትዮ ኮደር ስልጠናንም ሁሉም ሰራተኛ ሊተገብር እንደሚገባ ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተሰጥቷል።
የባለስልጣኑ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቡድን መሪ በሆኑት በአቶ ሚሊዮን ካሳሁን አማካኝነት ስለ ኢትዮ ኮደር ምንነት፣5ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ምንድን ነው፣የፕሮግራሙ አለማ፣ ያሉ ፕሮግራም እና አጠቃቀም አስመለክቶ በዝርዝር አቀርቧል ።
የባለስልጣኑ የ90 ቀናት እቅድ በተመለከተ ባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ በአቶ ንጋቱ ዳኛቸው አማካኝነት አቀርቧል ።
በዕቅዱ ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴን መከላከል መቆጣጠር ፣ የአረንጓዴ አሻራና የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ በችግኝ ተከላ ፣ቤት እድሳት ፣ማዕድ ማጋራት እንዲሁም የኮሪደር ልማት እና የመሰረት ልማት ጥበቃ ስራዎችን በተሳካ ሁኔታ ሊከናወኑ እንደሚገባ ዕቅዱ በዝርዝር አቀርቧል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
ባለስልጣኑ በኮሪደር መሠረተ-ልማት ላይ በእግረኞች መንገድ በተሽከርካሪ በመሄድ ደንብ ተላልፈው የተሰወሩ አሽከርካሪዎች 300 ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
10/10/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በትላንትናው እለት በቂርቆስ ክፋለ ከተማ ወረዳ 03 ወሎ ሰፈር አካባቢ በተሠራው የኮሪደር ልማት መሰረተ ልማት የእግረኞች መንገድ ላይ በተሽከርካሪ በመሄድ ደንብ ተላልፈው የተሰወሩ አሽከርካሪዎች ከአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ፖሊሶች ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር በማዋል መቅጣቱን አስታወቀ ።
ግለሰቦቹ በህብረተሰቡ ጥቆማ መሠረት ክትትል በማድረግ 3 አሽከርካሪዎች ከነ ተሽከርካሪአቸው በቁጥጥር ስር በማዋል እያንዳንዳቸው 100.000 (አንድ መቶ ሺህ ብር )በድምሩ 300,000/ሦስት መቶ ሺህ/ ብር መቀጣቱን ገልጸዋል ።
ባለስልጣኑ የህብረተሰቡ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮርደር ልማትና በሌሎች አካባቢ የማገኙ መሠረተ ልማቶችን፣ለህዝብ የተሰሩ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን ደህንነት በመጠበቅ በሀላፊነት እንዲገለገል መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማዋ ደንብ የሚተላለፉ የግልና የመንግስት ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል ።
ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
10/10/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በትላንትናው እለት በቂርቆስ ክፋለ ከተማ ወረዳ 03 ወሎ ሰፈር አካባቢ በተሠራው የኮሪደር ልማት መሰረተ ልማት የእግረኞች መንገድ ላይ በተሽከርካሪ በመሄድ ደንብ ተላልፈው የተሰወሩ አሽከርካሪዎች ከአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ፖሊሶች ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር በማዋል መቅጣቱን አስታወቀ ።
ግለሰቦቹ በህብረተሰቡ ጥቆማ መሠረት ክትትል በማድረግ 3 አሽከርካሪዎች ከነ ተሽከርካሪአቸው በቁጥጥር ስር በማዋል እያንዳንዳቸው 100.000 (አንድ መቶ ሺህ ብር )በድምሩ 300,000/ሦስት መቶ ሺህ/ ብር መቀጣቱን ገልጸዋል ።
ባለስልጣኑ የህብረተሰቡ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮርደር ልማትና በሌሎች አካባቢ የማገኙ መሠረተ ልማቶችን፣ለህዝብ የተሰሩ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን ደህንነት በመጠበቅ በሀላፊነት እንዲገለገል መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማዋ ደንብ የሚተላለፉ የግልና የመንግስት ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል ።
ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለስድስተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና መሳካት የማዕከሉ ሰራተኞች ላደረጉት አስተዋጽኦ የምስጋና ፕሮግራም ተካሄደ ።
12-10 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለስድስተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ከስልጠና ጀምሮ እስከ ምርቀት ፕሮግራም መሳካት የማዕከሉ ሰራተኞች ላበረከቱት አስተዋጽኦ የምስጋና ፕሮግራም ተካሄደ ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የስድስተኛ ዙር ስልጠና እንዲከናወን ሌት ተቀን በመስራት ስልጠናው በታሰበለት ግብ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከታችሁ አካላት የባለስልጣኑ ዳይሬክተሮችና ሰራተኞች በተቋሙ ስም ምስጋና አቅርበዋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
12-10 -2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለስድስተኛ ዙር ፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰር ከስልጠና ጀምሮ እስከ ምርቀት ፕሮግራም መሳካት የማዕከሉ ሰራተኞች ላበረከቱት አስተዋጽኦ የምስጋና ፕሮግራም ተካሄደ ።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የስድስተኛ ዙር ስልጠና እንዲከናወን ሌት ተቀን በመስራት ስልጠናው በታሰበለት ግብ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከታችሁ አካላት የባለስልጣኑ ዳይሬክተሮችና ሰራተኞች በተቋሙ ስም ምስጋና አቅርበዋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡