እንኳን ደስ አላችሁ!!! እንኳን ደስ አለን!!!
ድርብ ደስታ!!! ድንቅ ስኬት!!!
ሁለቱም ተቋሞቻችን በ2017 በጀት ዓመት በላቀ አፈፃፀም ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከተቋማት 1ኛ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ከከተማው ከቢሮዎች 2ኛ በመውጣት የመኪና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ድርብ ደስታ!!! ድንቅ ስኬት!!!
ሁለቱም ተቋሞቻችን በ2017 በጀት ዓመት በላቀ አፈፃፀም ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከተቋማት 1ኛ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ከከተማው ከቢሮዎች 2ኛ በመውጣት የመኪና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
👍22🏆8😁1
"እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን! ስኬቱ የሁሉም አመራርና፣ ሰራተኞችና ኦፊሰሮች የጥረት ውጤት ነው" ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ
ሐምሌ 14/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2017 በጀት ዓመት በተካሄደው ምዘና ከተቋማት ( ካቢኔ አባል ካልሆኑ ) በጣም ከፍተኛ ውጤት በማምጣት አንደኛ ደረጃ በመውጣት የመኪና ሽልማት ተበርክቶለታል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደገለፁት ይህ ዕውቅናና ሽልማት መምጣት የቻለው ከላይ እስከታች የሚገኝ ሁሉም አመራርና ሰራተኛ በትጋት፣ በጥረት፣ በመደማመጥ፣ በቅንጅትና በትብብር ተግባብቶ በጋራ መስራት በመቻሉ ስለሆነ መላው የደንብ ማስከበር አመራሮች ፣ሰራተኞችና የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ልፋታችን ውጤታማ ስለሆነ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እወዳለሁ።
በእለቱ የባለስልጣኑ አመራሮች በዘንድሮ አመት ለውጤት ያበቃንን ተግባብቶና ተናቦ የመስራት ባህል በቀጣዩ በጀት ዓመት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አስገንዝበዋል ።
አክለውም በ2018 በጀት አመትም ወርቃማ ድል ለማስመዝገብና የከተማችን የደንብ ጥሰት ለመቀነስ ከወዲሁ ዝግጁ መሆን ይገባናል ብለዋል።
በተጨማሪም የባለስልጣኑ አመራሮች ፣ ዳይሬክተሮች እና ሰራተኞች በተገኘው ውጤት ደስተኞች መሆናቸውንና በቀጣይም የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆናቸው ገልፀዋል ።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ሐምሌ 14/2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2017 በጀት ዓመት በተካሄደው ምዘና ከተቋማት ( ካቢኔ አባል ካልሆኑ ) በጣም ከፍተኛ ውጤት በማምጣት አንደኛ ደረጃ በመውጣት የመኪና ሽልማት ተበርክቶለታል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ እንደገለፁት ይህ ዕውቅናና ሽልማት መምጣት የቻለው ከላይ እስከታች የሚገኝ ሁሉም አመራርና ሰራተኛ በትጋት፣ በጥረት፣ በመደማመጥ፣ በቅንጅትና በትብብር ተግባብቶ በጋራ መስራት በመቻሉ ስለሆነ መላው የደንብ ማስከበር አመራሮች ፣ሰራተኞችና የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ልፋታችን ውጤታማ ስለሆነ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እወዳለሁ።
በእለቱ የባለስልጣኑ አመራሮች በዘንድሮ አመት ለውጤት ያበቃንን ተግባብቶና ተናቦ የመስራት ባህል በቀጣዩ በጀት ዓመት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አስገንዝበዋል ።
አክለውም በ2018 በጀት አመትም ወርቃማ ድል ለማስመዝገብና የከተማችን የደንብ ጥሰት ለመቀነስ ከወዲሁ ዝግጁ መሆን ይገባናል ብለዋል።
በተጨማሪም የባለስልጣኑ አመራሮች ፣ ዳይሬክተሮች እና ሰራተኞች በተገኘው ውጤት ደስተኞች መሆናቸውንና በቀጣይም የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል ዝግጁ መሆናቸው ገልፀዋል ።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
👍8