ASD AJ LAH
753 subscribers
1.72K photos
194 videos
3 files
486 links
ካነበብኩት…
Download Telegram
ምን ሠርተህ ዋልክ?

ሰው አምላኩ ፊት ቆሞ “ምድር ላይ ለምን ዓላማ ኖርክ? ምንስ ሠራህ?” ሲባል “ይኸው አምላኬ ሆይ ለዚህ ዓላማ ነው የኖርኩት” ብሎ ነገ ለአምላኩ የሚያሳየው ነገር በእጁ ይዞ ወደ መቃብር መውረድ፣ ወደ አኺራ መሸጋገር አለበት የሚል ፅኑ እምነት አለኝ፡፡ ዕድሜ እንደሆነ አይቆምም ይሄዳል፡፡
እናም ምድር ላይ ስትኖር የሆነ አስተዋጽኦ ይኑርህ፤ አንድ ሰው ኪሳራ ዉስጥ ነው የሚባለው ትናንትና እና ዛሬው፤ ዛሬው እና ነገው አንድ ሲሆንበት ነው፡፡ በበጎ ሥራ ምንም ሳይጨምር የዋለበት ቀን፡፡ ዛሬ ሥራ እንጂ ምርመራ የለም፤ ነገ ደግሞ የምርመራ ቀን ነው የሥራ ዘመን አልፏል፡፡ ያኔ “ምድር ላይ ምን ሠራህ?” ብትባል ምን ይሆን ታዲያ መልስህ ወዳጄ!
አንብቤያለሁ፣ ሌሎቸንም አስተምሬያለሁ አንድ ነገር ነው፤ ቀርቻለሁ፣ ፅፊያለሁ፣ ደዕዋ አድርጌያለሁ፣ ለሰው ልጆች ጠቃሚ ነገር ሠርቻለሁም አንድ ነገር ነው፡፡ አግብቼ መልካም ልጆችን ወልጄ ዲኑን እንዲያገልግሉ አሰማርቻለሁም አንድ ነገር ነው፡፡
ግና ምንም ሳይሠሩ ዉሎ ማደር፣ አምሽቶ ማንጋት፣ ወጥቶ መግባት ትልቅ ኪሳራ ነው፡፡ ከላይ ዛሬ እና ነገ የተመሳሰሉበት ሰው ያልነው እሱ ነው፡፡


ጀሊሉ ብርታቱን ይስጠን!

©
ጉለሌ የሙስሊም መካነ መቃብር ምን እየተሰማ ነው🤔
ሁለት ክስተቶች!

📌 የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በነገው እለት ወሳኝ ነው ያለውን የአጀንዳ ልየታ ፕሮግራም በአዲስ አበባ እንደሚጀምር አሳውቋል::

📌 ጉለሌ ሙስሊም መቃብር በተነሳ ግጭት ኡስታዝ ሙሐመድ አባተ እንደተደበደበ ተገልፇል:: የመቃብሩንም ይዞታ ለማስጠበቅ ሙስሊሙ ወደ መቃብሩ በነገው እለት እንዲመጣ አንዳንድ አክቲቪስቶች ጥሪ እያቀረቡ ነው::

🔺 አገጣጥሙት እስቲ:: ትኩረታችን ለየትኛው ይሁን? በመቃብሩ ላይ የተሰራው የድፍረትና የንቀት ተግባር ይቅር የማይባል ነው:: የመቃብሩ ስፍራ ላይ ያሉትን stores ሲዘርፉ ሲቀጥልም ኡስታዝ ሲደበደቡ እያዩ ፀጥ ያሉ የፀጥታ አካላት የተሰራውን ጥፋት ያባዙታል:: ነገር ግን መጠርጠሩም አይከፋም:: ከነገ በመለስ ለምን ብሎ መጠየቁ ደግ ነው:: ከዚያ በመለስ ጉዳዩን በህግ አግባብ መያዙ ይበጃል::

🔺 ከዚያ በመለስ ትኩረታችንን ሀገራዊ ምክክሩ ላይ እናድርግ:: ነገ አጀንዳ ልየታ ሊጀመር ሆኖ ሳለ መጅሊስ ለምን ዝም አለ? የመጡ ለውጦች ካሉ ቢያሳውቅ:: ለውጥ ከሌለም ባወጣቸው መግለጫዎች መሰረት ሙስሊሙ ምን ማሰብና ማድረግ እንዳለበት አቋሙን ቢገልፅ::

ወላሁ አዕለም!

Mohammadammin
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልዓርቢዓዐ 2️⃣1️⃣ #ዙልቀዓዳ 1️⃣4️⃣4️⃣5️⃣
ከትዳር በፊት ፍቅር የለም ብዬ የኸዲጃን ፍቅር ገደል አልከተውም… ምክንያቱ ምንም ይሁን አፍቅራ እንዳገባቻቸው አልጠራጠርም… በሪራ በሚሏት ሰሓቢት ፍቅር ተለክፎ በመዲና መንገዶች ላይ ከኋላዋ እየተከተለ…  የእንባ ቋንጣውን በመዲና አድማስ  ሲወረውር የነበረውን ሰሓባው ሙጊስ … አፍቃሪ አልነበርክም ልለው አልችልም… ቀድመው ቢለያዩና ከዚያ በኋላ ባያገባትም “ሙጊስ ለበሪራ ባለው ፍቅር፣ በሪራ ደግሞ ለሙግስ ባላት ጥላቻ አልተገረምክም ወይ” የተባለለት አፍቃሪ ነው… ያውም በረሱል አንደበት።

አንድ ነገር ግን አምናለሁ… ፍቅር በስሙ የሚደረጉ ኃጥያቶችን እንደማያውቃቸውና  የአፍቃሪ መድሀኒቱም ትዳር እንደሆነ…  ማንነትህን ፣ እምነትህንና ጉዞህን የሚያመክንብህ ከሆነ በሽታ እንደሆነ… አምናለሁ። ነብይህ “ለተዋደዱ ሰዎች ከኒካህ ውጪ (አማራጭ) አላየሁም” ሲሉም… ከትዳር በፊት መዋደድ እንዳለና ኒካህ ካልታከለበት ግን የኪሳራ መንገድ ሊሆን እንደሚችል ነው… አፍቅርሃል? በበር በኩል ና በቃ … በፍቅር ስም ሙድ አትያዝ!!

©
💌اللهم أشغلني بما ينفعني
و سخرني و سخر لي الخير
و قوّيني على هوى نفسي و هوى شياطين الإنس و الجن
و لا تُعدني إلى ذنب تُبت عنه يومًا

أستغفر الله العلي العظيم و أتوب إليه من جميع الذنوب ما علمت منها و ما لم أعلم، أستغفر الله حتى يغفر الله ذنبي و يبرأني من جميع الخطايا


💌💌💌💌💌💌💌💌💌💌💌💌
ድንቅ ክስተት - ሶሉ አለ ነቢ!

ሚካኤል ሀርት ነው:: 100 ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች የሚለውን መፅሐፍ ለመፃፍ 28 አመታት ፈጅተውበታል::  ከ100ዎቹ ሁሉ አስቀድሞ በአንደኛ ደረጃ ላይ የእኛን ነቢ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አስቀመጠ::

ለንደን ላይ ትምህርት እየሰጠ ባለበት ሰዓት ሰዎች "ለምንድን ነው ሙሐመድን አንደኛ ደረጃ ላይ ያስቀመጥከው?" በማለት ንግግሩን በማቋረጥ ረበሹት::

እሱም "ሙሐመድ ከ1400 አመታት በፊት ለሰዎች 'እኔ የአምላክ መልዕክተኛ ነኝ!' ብሎ ሲናገር ያመኑበት ሰዎች 4 ሲሆኑ ጓደኛው ሚስቱና ሁለት ህፃናት ብቻ ነበሩ::" አለ:: በመቀጠልም "ከ1400 አመታት ቡሃላ ዛሬ ላይ ከ1 ቢልዬን በላይ ተከታዮችን አፍርቷል:: ስለዚህ ውሸታም ሊሆን አይችልም:: አንድ ሰው አንድ ቢልዬን ሰውን መዋሸትም ሆነ መሸወድ አይችልም:: ውሸትም ለ1400 አመታት ሊቆይ አይችልም::" ሲል አከለ::

ከዚህም በመጨመር ለአድማጮቹ "ከዚህ ሁሉ አመታት ቡሃላ እንኳ በሚልዬን የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ነፍሳቸውን እርሱን ለማንቋሸሽ ለምትወረወር አንድ ቃል ሲባል መስዋዕት ለማድረግ ዝግጁ ናቸው::" ሲል ነገራቸው:: በማስከተልም "ከእናንተ መካከል አንድ ክርስቲያን እንኳ ይህንን መስዋዕትነት ለእየሱስ ለመክፈል ዝግጁ አለ?" ሲል ጠየቃቸው::: መልስ አልነበረም:: አዳራሹ በፀጥታ ተሞላ::

ፊዳከ ኡሚ ወአቢ ያኸይረልወራ!

Mohammadammin
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልኽሚስ 2⃣2⃣ #ዙልቀዓዳ 1⃣4⃣4⃣5⃣
ይሄንን የሰርግ ጥሪ ተመልከቱት¡ አጀብ ነው !
Forwarded from Mohammedamin Kassaw
ሀገራዊ ምክክር ምንድን ነው? ለምን ተቋቋመ? ለሙስሊሙስ ምን ይፈይዳል?

   ሀገራዊ ምክክር በዋናነት እንደ ሀገር በታሪክ ውስጥም ሆነ አሁን ባለው አውድ የተፈጠሩ ሀገራዊ ችግሮችንንና አለመግባባቶችን በምክክር ለመፍታት ታስቦ የተቋቋመ ኮሚሽን ነው:: በትላንት ውስጥ ያለፉ ታሪኮችና ትርክቶች እንዴት መፃፍ እንዳለባቸው አቅጣጫ ያስቀምጣል:: የሀገሪቱን ጀግኖች በዝርዝር ያስቀምጣል:: ሀገሪቱ ዛሬ ላይ ምን አይነት ምልክቶችና መገለጫዎች (ባንዲራ : ብሔራዊ መዝሙር: የአደባባይና መንገድ ስያሜዎች ወዘተ) ሊኖራት እንደሚገባ ይወስናል:: ዜጎች በሀገሪቱ ላይ ምን አይነት መብት ሊኖራቸው ይገባል የመብታቸው ድንበርስ እስከየት ነው የሚለውን ያስቀምጣል:: ህገ-መንግስቱ የሚሻሻልበትን አጠቃላይ መስመር ይዘረጋል::

📌 እንደ ሙስሊም ከላይ የተጠቀሱትም ሆነ ሌሎች ያልተጠቀሱ አጀንዳዎች ይነኩናል:: ውጤቱ አሉታዊም ሆነ አዎንታዊ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ቦታ መብትና ግዴታ ያስቀምጣል:: ታሪካችን ይፃፋል:: መብታችን ይቀመጣል:: ውክልናችን ይገለፃል:: እንደ አጠቃላይ ሙስሊሙ ጥያቄ ብሎ በሚያነሳቸው ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ያልፋል::

📌 በምክክሩ ውስጥ የሚመካከሩት ከማህበረሰቡ ውስጥ የተመረጡ ተሳታፊዎች ሲሆኑ እስከ አሁን አዲስ አበባ ላይ ከሚሳተፉ 2ሺህ ገደማ ተሳታፊዎች የሚሳተፉ ሙስሊሞች ከ5 ፐርሰንት በታች ማለትም 100 ሰው አካባቢ ነው:: ሙሉ ለሙሉ ሙስሊም በሆኑባቸው እንደ አፋርና ሱማሌ ክልል ያሉ ተሳታፊዎች ከአጠቃላዩ ከ50 ፐርሰንት በታች ነው:: በሌሎች ክልሎች ደግሞ 1.8 ፐርሰንት ገደማ ነው::

📌 በዚህ ውስጥ የሚወሰኑ ውሳኔዎች አሉታዊ ከሆኑ ችግሮች እንደ በፊቱ ይቀጥላሉ:: በቀላሉ አሁንም ልጆቻችን የግራኝ አህመድ ወረራ እያሉ የሀገራቸውን ጀግና እንደ ወራሪ ተደርጎ ይማራሉ:: በትምህርት ቤት ውስጥ ያለው የሂጃብ አጀንዳ አጀንዳ ሆኖ ይቀጥላል:: ወታደር ቤት ለመግባት ሶላትን መተው መስፈርት ሆኖ ይቀጥላል:: ሌላም ሌላም...

🔺 እውነታውና አደጋው የዚህን ያክል ቢሆንም አሁንም ድረስ የግንዛቤ እጥረት አለ:: የሙስሊሙ ችግር የዚህን ያክል ጥልቅ ቢሆንም የምክክር ኮሚሽኑ ለማሳተፍ ፈቃደኛ አልሆነም::

🔺 መሪ ተቋሙ ተቃውሞ ካሰማ ሰነባብቷል:: እኛም ከተቋማችን ጎን እንደሆንና ይህንን ዝም ብለን እንደማናየው የማሳየት ግዴታ አለብን:: በFacebook, telegram, X, Youtubeና መሰል የማህበራዊ ትስስር ገፆች ስለ ምክክሩና ኮሚሽኑ መልዕክት እናስተላልፍ:: ተቃውሟችንን በኮሚሽኑ ፔጅ Comment box ላይ እናስቀምጥ:: የቤትም ሆነ የስራ ቦታ ወሬያችንን ስለዚህ ብቻ እናድርግ:: የዚያኔ በአላህ ፈቃድ መሪዎቻችን ወኔያቸው ይበረታል:: በንቄት ዝም ያሉን ጆሮዎች በፍርሃት ያደምጥናሉ:: መብታችንንም አዝነውልን ሳይሆን አክብረውን ይስጡናል:: መብታችንን ለምነን ሳይሆን ታግለን እንወስዳለን:: አራት ነጥብ💪💪

የሁላችን ኢትዮጵያ ትምከር!
አላህ ምክክሩን ለሀገራችን የሚበጅ ያድርገው!!

@MohammadamminKassaw
~በዙሪያህ ያለውን ሁሉንም ነገር ለመረዳት አትሞክር። አንዳንድ ጉዳዮችን አለመረዳት ነው የሚሻለው። አንዳንዴ ነገሩን በመረዳትህ የሚመጣብህ የልቦና ቀውስና አንደበትህ ላይ የሰዎች ስም መመላለስ ብቻ ነው።በቃ ምናገባኝ ማለት አስፈላጊ ነው። በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ!

©AbuSufiyan_Albenan
የአላህ ጊዜ ሁሌም ትክክል ነው። የእርሱ ቃልኪዳን ሁልጊዜም እውን ነው። ባሮቹ ሲበደሉ ዝም ብሎ የሚመለከት አምላክ የለንም። አማኞች አቅም ሲያጡ፤ ለአዕምሮ የሚከብዱ ተጨባጮች ውስጥ ሲገቡ የሚዘነጋቸው ጌታ አይደለም።

አላህ አይረሳም! ❤️‍🩹

ጌታችን የባሮቹን ህመም ረሺ አይደለም። ረቢ በዳዬችን የሚበቀል አምላክ ነው። የአሳማሚ ቅጣት ባለቤት ነው!

ጀሀነም ሐቅ ነው!
ጌታችን ፊት መቅረብ ሐቅ ነው!
ሁሉም የስራውን የሚያገኝበት የሒሳብ ቀን'ም ሐቅ ነው!

የዛኔ ግን ቅጣቱም ሆነ ሽልማቱ ጊዜያዊ አይደለም። የዛኔ የትኛውም አምባገነን መሪ ጭፍ*ጨፋውን በሚዲያ ሽፋን ለመደበቅ አይሞክርም። ዳኛው አላህ ነዋ! የዛኔ ማምለጫ አይኖርም! ቆዳን በጣም አክሳይ በሆነው ሰቀር ውስጥ የመማቀቂያ ዘላለማዊ ህይወት ይጀምራል! ወላሂ የዛኔ ማምለጫ በፍፁም አይኖርም!

እነዚህ አረመኔዎች ምድር ላይ የበሉት ነፍስ፤ ያፈሰሱት የጨቅላ ደም የዛኔ ይከፍላቸዋል! እስከዛ ደግሞ በዚህች ትንሽ የዱንያ ቆይታቸው እረፍት ያለ ኑሮን አይሰጣቸውም። በቅዠት የተሞሉ ለሊቶች፤ በፍርሃት፤ በጭንቀት የተረበሹ ልቦችን ይለግሳቸዋል! ምክንያቱም አላህ በባሮቹ ድርድርን አያውቅም! እንዴት'ስ ዝም ይላል?! በእውነቱ ጌታችን ረሺ አምላክ አይደለም። 🙌🏽

እኛም እስከዛ "ሐስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል!" እንላለን! ... የትኛውም ቃል፤ የትኛውም መፈክር፤ የትኛውም የተስፋ ቃል ከዚህ በላይ ሊያጠነክረን አይችልም! ቁስላችንን በቅርቡ ያሽርልን ዘንድ ምላሳችን ላይ እናዘውትረው ኢንሻአላህ! ❤️‍🩹
#Nadia
« ሙትቻ ላሉህ ሰዎች እራስህን ለማስረዳት አትሞክር። ለሞትክባቸው ሰዎች የምታባክነው ጊዜ አይኑርህ። ውበትህ ግለፅ ሲወጣ የመጣ ሁሉ ውበትህን አይቶ ላይሆን ይችላልና በአመዳምነት ዘመንህ ላይ ውበትህ የታያቸውን ጠበቅ አድርገህ ያዝ።
ቆንጆ መሆንሽን ከሚያደንቁት የበለጠ የሚያስጠላብሽን ሊያስውቡልሽ የሚጣጣሩትን አትዘንጊ። ቁስልሽን በሰው አትከልዪ። የሚመክሩሽ ሁሉም ከጥቃት አይጠብቁሽም። ጥንቃቄ የብልሆች መንገድ ነው። በጣም ነፃነት በሚሰማሽ ሰው በኩል ስስ ነሽና አትራቆቺ።
ዋጋ የምትከፍዪላቸው ከጌታሽ መንገድ እንዳያስቱሽ አስተውዩ! የምወድሽዋ ልብሽን በቀደር አረጋጊ! የምወድህዋ እራስህ ካልወደቅክ አይጥሉህምና በጌታህ ታግዘህ ፅና። መንገዱ ምን እንዳለው አይታወቅምና ሰላም ለልባችሁ!
©
[አብዱልሀኪም ሰፋ]

❤️❤️❤️اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وآله وصحبه أجمعين ❤️❤️❤️

ልባችን ሰላም የሚያገኝበት፣  በሩቋ ሀገር ያሉትም ከአላህ የሆነ እርዳታ እና ድል የሚያገኙበት፣ ተረጋግተው የድል ሰላት የሚሰግዱበት፣  ለተጨነቁት ወንድሞቻችን ድልን ለታመመ መዳንን፣ ለሞቱት ሸሂድነትን  የሚወፈቁበት፣ በሰለዋት፣ በካህፍ እና በዱዓ የደመቀ እና የተዋበ ጁምዓ ይሁንልን💚💚💚

https://t.me/asdajlahh
"የሙስሊም ተሳታፊዎች ቁጥር አናሳ በመሆኑ የምናነሳው አጀንዳዎች ተቀባይነት እያጡ ነው"በአዲስአበባ የሀገራዊ ምክክር ሂደት ተሳታፊዎች
...
(ሀሩን ሚዲያ፦ግንቦት 22/2016)
...
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ትናንት ግንቦት 21/2016 ዓ.ል በአዲስ አበባ የምክክር መርሀግብር በአድዋ "ሙዚየም" አዳራሽ የጀመረ ሲሆን በዛሬው ዕለት በግዮን ሆቴል እየተካሄደ በነበረው አጀንዳ የመለየት መርሀግብር የሙስሊሙ ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ አጀንዳዎችን ለማስያዝ እና በቀጣይ በሚኖሩ ውይይቶች ለማለፍ በድምፅ ብልጫ በመሆኑ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በዚህ ረገድ የተሳታፊዎቹ ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ በድምሩ ብልጫ አጀንዳዎች ውድቅ እየሆኑ መሆኑን "ሀሩን ሚድያ "ያነጋገራቸው ተሳታፊዎች ገልፀዋል።

ውይይቱ በቡድን በቡድን ስምንት ስምንት ተሳታፊዎችን ያካተተ መሆኑን በማንሳት የሙስሊሙ ቁጥር ግን በየቡድኑ ከአንድ ወይም ከሁለት እንደማይበልጥ በዚህም ምክንያት ቀጣይ ለሚደረገው ውይይት ሙስሊሙ ተሳታፊ እንደማይሆን ጨምረው ተናግረዋል።

ተወካዮች በአጀንዳ ሃሳቦቻቸው ላይ ከተወያዩ በኋላ በቀጣይ የምክክር መድረኮች ሀሳቦቻቸውን በውክልና የሚያቀርቡላቸውን 121 ተወካዮችን የሚመርጡ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ የሙስሊሙ ተወካዮች እጅግ በጣም ጥቂት ሊሆኑ እንደሚችሉ ከታዘቡት በመነሳት አስተያየታቸውን የሰጡ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

ለሀሩን ሚድያ አስተያየታቸውን የሰጡ ተሳታፊዎች በመጨረሻም ሀገራዊ ምክክሩ አሁንም ከስተቱ በመማር ሙስሊሙ በቁጥሩ ልክ ተሳትፎ እንዲያደርግ ማመቻቸት እንዳለበት ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

©ሀሩን ሚድያ