TIKVAH-ETHIOPIA
1.38M subscribers
54.6K photos
1.35K videos
197 files
3.61K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia በአሜሪካን ዋሽንግቶን ዲሲ የሚገኙት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከአሜሪካ - አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከተለያዩ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል። - ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ ከአሜሪካ የንግድ ተወካይ አምባሳደር ካትሪን ታይን ተገናኝተው ተውያይተዋል። የሁለቱን ሀገራት የንግድ ግንኙነት ማስፋፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ጥሩ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል። - ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ IMF…
#USA #AFRICA

ለ3 ቀናት የተካሄደው የአሜሪካ-አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ትናንት ሐሙስ ተጠናቋል።

የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን በጉባኤው ምን አሉ ?

- ከሰሃራ ግርጌ ወዳሉ የአፍሪካ አገሮች በቅርቡ ጉብኝት እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። ከሰሃራ ግርጌ ወዳሉ የአፍሪካ አገሮች የሚያደርግት ጉብኝት እንደ ፕሬዝደንት የመጀመሪያው ነው። ቀኑን እና የትኞቹ ሀገራትን እንደሚጎበኙ ግን አላሳውቁም።

- አፍሪካ እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልፀው አሜሪካ ትኩረቷን እንደምትጨምርም ጠቁመዋል።

- ከፍተኛ አማካሪዎቻቸውን ወደ አፍሪካ እንደሚልኩ ገልፀዋል። ወደ አፍሪካ ከሚላኩት ውስጥ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ አንተኒ ብሊንከን፣ የገንዘብ ሚኒስትሯ ጃነት የሊን እና የንግድ ሚኒስትሯ ጂና ሬይሞንዶ ይገኙበታል።

- በሚቀጥለው ዓመት ለሚደረጉ ምርጫዎች 165 ሚሊዮን ዶላር እንደሚመደብ ቃል ገብተዋል።

ፕሬዚደንት ባይደንና ባለቤታቸው ጂል ባይደን የአፍሪካ አገራት መሪዎችንና ቀዳማዊ እመቤቶቻቸውን በዋይት ሃውስ የእራት ግብዣ አድርገውላቸዋል።

በሌላ በኩል ፤ በአሜሪካ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ሊሳተፍ ወደ አሜሪካ አቅንቶ የነበረው የኢትዮጵያ ልዑክ ወደ ሀገር መመለሱን የጠ/ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ዛሬ አመሻሹን አሳውቀዋል።

#ቪኦኤ #አምባሳደር_ሬድዋን_ሁሴን

@tikvahethiopia
#USA #NorthKorea

አሜሪካ #ኑውክሌር_የመሸከም አቅም ያላቸውን " B-52 " ቦምብ ጣይ ጄቶቿን ዛሬ በደቡብ ኮሪያ አቅራቢያ ለልምምድ ማብረሯን ቪኦኤ ዘግቧል።

በረራው ከሰሜን ኮሪያ ሊመጣ የሚችልን ስጋት የመመከት አቅሟን ለማሳየት ነው ተብሏል። በተጨማሪም F-22 የተባሉትን ስቲልዝ ተዋጊ ጄትችንም ማብረሯ ተሰምቷል።

ደቡብ ኮሪያ በበኩሏ F-35A እና F-15K ይተሰኙ ተዋጊ ጄቶቿን በልምምዱ ማሳተፏን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሀገራቱን ልምምዱን ያደረጉት በዚህ ዓመት ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሚሳዬል ሙከራ ላደረገችውና በአሜሪካና ደቡብ ኮሪያ ላይ ዛቻዋ እየጨመረ ለመጣው ሰሜን ኮሪያ ጡንቻቸውን ለማሳየት እንደሆነ ነው የቪኦኤ ዘገባ የሚያስረዳው።

2ቱ አገሮች ወታደራዊ ልምምዳቸውን ለማጠናከርና በአሜሪካ በኩል የሚቀርቡትን የመሣሪያና ጄቶችን ቁጥር ለመጨመር፣ እንዲሁም አሜሪካ ደቡብ ኮሪያን ለመከላከል የገባቸውን ቃል በተግባር እንድታጠናክር ባለፈው ወር ተስማምተው ነበር።

የደቡብ ኮሪያው የመከላከያ ሚኒስቴር ፤ ያንን ስምምነት በመጥቀስ፣ ለሰሜን ኮሪያ የኑክሌርና የሚሳዬል ዛቻ መልስ ለመስጠት ሁለቱ አጋሮች የመከላከያ ብቃታቸውን ማሳየታቸውን ይቀጥላሉ ሲሉ ተናግረዋል።

ሰሜን ኮሪያ በዚህ ዓመት ብቻ እጅግ ተደጋጋሚ ሚሳኤል ስታስወነጭፍ የነበር ሲሆን ከቀናት በፊትም መካከለኛ ርቀት ያላቸውን ባሊስቲክ ሁለት ሚሳዬሎች አስወንጭፋለች።

ሀገሪቱ የመጀመሪያውን የስለላ ሳተላይት ለመላክ ወሳኝና የመጨረሻ ሙከራ ነው ማለቷን ዘግባው ያሳያል።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #USA

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊነከን ጋር በስልክ መወያየታቸውን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት አሳውቋል።

ውይይታቸው ትኩረቱን ያደረገው የሰላም ስምምነቱን አፈፃፀም በተመለከተ እንደነበር ተመላክቷል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት ይፋ ባደረገው መረጃ፤ የኤርትራ ወታደሮች ከሰሜን ኢትዮጵያ እየወጡ መሆኑን በማመልከት በዚህም ጉዳይ ብሊንከን ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ መነጋገራቸውን ገልጿል።

ብሊንከን ፤ የታየውን መሻሻል (የኤርትራ ሰራዊት መውጣት መጀመር) በደስታ መቀበላቸው፤ ይህም በሰሜን ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ቁልፍ መሆኑን የገለፁ ሲሆን የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቆጣጣሪዎች ወደየአካባቢዎቹ እንዲደርሱ አሳስበዋል።

ብሊንከን ፤ ሀገራቸው አሜሪካ በአፍሪካ ህብረት መሪነት እየተካሄደ ላለው የሰላም ሂደት ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል ለዶ/ር ዐቢይ አህመድ አረጋግጠዋል።

በተጨማሪ፤ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ እና ብሊንከን በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን አለመረጋጋት እንዲያበቃ በማድረግ አስፈላጊነት ላይም መመካከራቸው ተገልጿል።

ይህንን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መረጃ በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግሥት ኮሚኒኬሽን /ከጠ/ሚ ፅ/ቤት/ ከራሳቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ በኩል ምንም የተባለ ነገር የለም።

የኤርትራ ወታደሮችን ከሰሜን ኢትዮጵያ በተለይ ከትግራይ ክልል መውጣትን በተመለከተ ከሰሞኑን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ነዋሪዎችን ዋቢ አድርገው ዘገባ እያቀረቡ ይገኛሉ ነገር ግን  ወታደሮቹ እየወጡ ስለመሆኑ ከአፍሪካ ህብረት/ ከኢትዮጵያ መንግሥት/ከትግራይ ክልል አመራሮች በኩል እስካሁን ምንም ይፋዊ መግለጫ አልተሰጠም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " በኢትዮጵያ እና አሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ስምምነት ላይ ተደርሷል " - የጠ/ሚ ፅ/ቤት ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ቢንከንን በፅ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ይህን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ባወጣው መረጃ ውይይቱ በተለያዩ የሀገር ውስጥ፣ ቀጣናዊ…
#USA #ETHIOPIA

አሜሪካ ለኢትዮጵያ ከ331 ሚሊየን ዶላር በላይ የሰብአዊ ድጋፍ ይፋ አደረገች።

ለሥራ ጉብኝ አዲስ አበባ የሚገኙት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ለኢትዮጵያ ከ331 ሚሊየን ዶላር በላይ የሰብአዊ ድጋፍ ይፋ አድርገዋል።

አንቶኒ ብሊንከን እንዳስታወቁት ድጋፉ በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እና በአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት አማካኝነት የሚሸፈን ነው፡፡

ድጋፉም በተለያዩ ምክንያቶች በችግር ለተጋለጡ ወገኖች ለምግብ፣ ለመድሃኒት፣ ለንጹህ የመጠጥ ውሃ የሚውል እንደሆነ ተገልጿል።

ይህም በግጭት ለተጎዱ፣ ለተፈናቀሉ፣ በድርቅ ለተጠቁ እና ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ዜጎች ሕይወት አድን ድጋፍ ማድረግ እንደሚያስችል ብሊንከን ማሳወቃቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘገቧል።

@tikvahethiopia
#USA

አሜሪካ የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት ለማብቃት በተደረሰው ስምምነት መሠረት ውጤታማ ትጥቅ የማስፈታት እና ተያያዥ ተግባራትን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ ተቆጣጣሪዎች እንዲሰማሩ ጠየቀች።

ይህንን የጠየቀችው በኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል የተደረሰው ስምምነትን ስድስተኛ ወር ምክንያት በማድረግ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ ነው።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምን አለ ?

- የሰላማዊ ሰዎችን ጥበቃ እና ውጤታማ ትጥቅ የማስፈታት፣ ታጣቂዎችን የማሰናበት እና ከኅብረተሰቡ ጋር መልሰው የሚቀላቀሉበትን ሂደት የሚከታተሉ ተቆጣጣሪዎች በማሰማራት በስምምነቱ ላይ የተቀመጡ ሃሳቦች መቋጫ ሊያገኙ ይገባል።

- የኤርትራ ጦር እና ከፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት ውጪ ያሉ ኃይሎች ሙሉ ለሙሉ ከትግራይ እንዲወጡ መደረግ እንዲሁም የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን የፈጸሙ እና ተሳታፊዎችን ተጠያቂ ማድረግን ጨምሮ ተአማኒ የሽግግር ፍትሕ ሂደት በሰሜን ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው።

- ባለፉት ስድስት ወራት በስምምነቱ ትግበራ በርካታ አውንታዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።

• በትግራይ ተቋርጠው የቆዩ መሠረታዊ አገልግሎቶች መልሰው ሥራ መጀመራቸው፣

• የሰብአዊ እርዳታ ያለገደብ መቅረቡ፣

• ህወሓት ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ማስረከቡ፣

• እስረኞች መፈታታቸው፣

• ሁሉን አካታች የሽግግር ፍትህ ሂደት መጀመር እና በትግራይ ጊዜያዊ መስተዳደር መቋቋሙ የተወሰዱ አውንታዊ እምርጃዎች ናቸው።

በሌላ በኩል ፥ አሜሪካ በሰሜን ኢትዮጵያ የተከናወነው ስኬታማ የሰላም ሂደት በኦሮሚያ ክልል ሰላም ለማምጣት ዕድል መፍጠሩን አሳውቃለች።

ሀገሪቱ በመንግሥት እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል የተጀመረውን ንግግር አድንቃለች።

ሁለቱም ወገኖች ለሁሉም ተቀባይነት ያለው ስምምነት ላይ ለመድረስ በቅን ልቦና እንዲደራደሩ አበረታታለሁ ብላለች።

@tikvahethiopia
#USA #ETHIOPIA

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ዛሬ ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር በስልክ መምከራቸውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

ውይይቱ የነበረው በሰሜን ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ዙሪያ እንደነበር ተገልጿል።

አንቶኒ ብሊንከን ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል እና በጎራባቹ አፋር እና አማራ ክልሎች ያለውን ያልተገደበ የሰብአዊ ድጋፍ እና መሰረታዊ አገልግሎቶችን ወደ ነበረበት ለመመለስ እየሰራ ያለውን ጥረት እውቅና መስጠታቸው ተመላክቷል።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፤ የውጭ ኃይሎችን ከትግራይ ምድር ማስወጣትና አብሮም የትግራይ ኃይሎችን ትጥቅ ማስፈታት የሚለው ጨምሮ የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት በአስቸኳይ ተግባራዊ ማድረግን እንዳሰመሩበት ተሰምቷል።

ብሊንከን ፤ ሀገራቸው አሜሪካ የአፍሪካ ህብረት የስምምነት አፈፃፀም የክትትል እና ማረጋገጫ ዘዴን ጨምሮ በአጠቃላይ ህብረቱ የሚመራውን ሂደት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።

በደቡብ አፍሪካ ፤ ' ፕሪቶሪያ ' በዘላቂነት ግጭት እንዲቆም የተፈረመው ስምምነትን ለማስፈፀም በኬንያ ኖይሮቢ በተፈረመው ስነድ ፤ የትግራይ ኃይሎች የከባድ መሳሪያ ትጥቅ አፈታት የውጭ ኃይሎችና ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ ያሉ ኃይሎች ከክልሉ መውጣት ጋር በአንድ ግዜ እንደሚፈፀም ይገልጻል።

@tikvahethiopia
#BekeleGerba #USA🇺🇸

አቶ በቀለ ገርባ በአሜሪካ ሀገር #ጥገኝነት መጠየቃቸውን አሳወቁ።

ለረዥም ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በግል እና በፓርቲ ደረጃ ተሳታፊ የነበሩት የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ ፓርቲ ተቀዳመ ምክትል ፕሬዜዳንት አቶ በቀለ ገርባ በፓርቲያቸው የነበራቸውን ተሳትፎ አብቅተው በአሜሪካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን ለቢቢሲ አማርኛ ክፍል ተናገሩ።

አቶ በቀለ ፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ " በሰላማዊ መንገድ ለመታገልም ሆነ በግል በነጻነት መኖር " አሳሳቢ በመሆኑ በሄዱበት አሜሪካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን ገልጸዋል።

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ምክትል የሆኑት አቶ በቀለ፣ በውጭ አገር ሆነው ሥልጣኑን ይዘው መቀጠጣለቸው ጠቃሚ ስላልሆነ እራሳቸውን ከፓርቲው ለማግለል መወሰናቸውን ተናግረዋል።

አቶ በቀለ ገርባ ፤ ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ ተፈጥሮ የነበረውን ሁከት ተከትሎ በቁጥጥር ሥር ውለው ለ18 ወራት በእስር ላይ ቆይተው ከተለቀቁ በኋላ ወደ አሜሪካ ተጉዘዋል። አሜሪካ ከሄዱ 1 ዓመት ከሶስት ወር ሆኗቸዋል።

አቶ በቀለ ከእስር ከወጡ በኋላ ወደ አሜሪካ ሲጓዙ ዓላማቸው የእርሳቸውን ከእስር መለቀቅ ሲጠይቅ ለነበረው የዳያስፖራ ማኅብረሰብ ምስጋና ለማቅረብ ነበር።

ነገር ግን አሜሪካ በቆዩባቸው ያለፉት 15 ወራት በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ በመቀየሩ " ወደዚያ አገር መመለሱ አስፈላጊ መስሎ አልታየኝም "  በማለት እዛው ጥገኝነት መጠየቃቸውን እና ከፓርቲው ኃላፊነትም እራሳቸውን ማግለላቸውን ለቢቢ አማርኛ አገልግሎት በሰጡት ቃል ገልጸዋል።

More - https://telegra.ph/BBC-08-28-2

@tikvahethiopia
#USA

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር ከነሐሴ 22 እስከ ጳጉሜ 3 ድረስ በኬንያ  እና በኢትዮጵያ ቆይታ እንደሚያደርጉ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

በናይኖቢ እንዲሁም በአዲስ አበባ ቆይታቸው ከሀገራቱ ባለስልጣናት፣ ከአፍሪካ ህብረት፣ ከልማት ድርጅት ባለስልጣን እና ሌሎች ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር ይነጋገራሉ ተብሏል።

ሐመር በአዲስ አበባ በሚያደርጉት ቆይታ፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉትን ግጭቶች በድርድር እንዲቋጩ እና ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት እንዳይደርስ እና ከለላ እንዲያገኙ ግፊት ያደርጋሉ ተብሏል።

ሐመር፣ በሱዳን ቀውስ እና ጦርነቱን ለማስቆም እየተደረጉ በሚገኙ ቀጠናዊና ዓለማቀፋዊ ጥረቶች ላይም ከአካባቢዉ አገራት፤ ከአፍሪቃ ኅብረትና ከኢጋድ መሪዎች ጋር እንደሚመክሩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ገልጿል።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመድ ከዚህ ቀደም በተለይም በትግራይ ከነስቶ ወደ አፋር እና አማራ ክልል የተስፋፋውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲበጅለት በተደጋጋሚ ወደ ኢትዮጵያ እና ጎረቤት ሀገራት መምጣታቸው የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #USA

ዓለም አቀፍ ለጋሾች ያቆሙት የምግብ ርዳታ ይቀጥል ዘንድ በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና በአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን መካከል የስልክ ውይይት ተደረገ።

የሚኒስቴር መ/ቤቱ ቃል አቀባይ ማት ሚለር እንዳሳወቁት ብሊንከን ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር የስልክ ውይይት አድርገዋል።

በዚህ ውይይት ወቅትም ፤ ዓለም አቀፍ ለጋሾች ያቆሙት የምግብ ርዳታ ይቀጥል ዘንድ ፣ የሰብአዊ ሁኔታ ቁጥጥር ተሻሽሎ ስለሚቀጥልበት አሠራር ላይ ተወያይተዋል።

በተጨማሪ አንተኒ ብሊንከን፣ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል ያለው ሁኔታ " አሳስቦኛል "  ሲሉ ተናግረዋል።

በሁለቱ ክልሎቹ ያሉትን ችግሮች #በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት፣ የፖለቲካ ውይይትንና የሰብአዊ መብቶች መከበር አስፈላጊነትን አጽንዖት ሰጥተውበታል።

እውነተኛ ፣ ታማኝ እና ሁሉን አካታች የሽግግር ፍትሕ ሒደትን ለመፍጠር እየተከናወነ ያለውን ሥራ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በመልካም እንደተቀበሉት ተጠቁሟል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከንና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ፣ በአፍሪካ ቀንድ ስለሚታየው የጸጥታ ተግዳሮት፣ እንዲሁም አንዲት፣ ሰላማዊት እና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት ያላቸውን የጋራ ግብ አስመልክቶም እንደተወያዩ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤትን ዋቢ በማድረግ ቪኦኤ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA #Israel

የአሜሪካው ፕሬዜዳንት #ጆ_ባይደን እስራኤል ገብተዋል።

ባይደን በእስራኤል ቆያታቸው ጦርነቱ ከዚህም በላይ ከፍቶ እንዳይስፋፋ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ያደርጋሉ ተብሏል።

የአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት ቃል አቀባይ ፕሬዝዳንት ባይደን የቀጠለውን ጦርነት #ዓላማን በተመለከተ ለኔታንያሁ ከበድ ያሉ ጥያቄዎችን እንደሚጠይቋቸው ገልጸዋል።

ባይደን በቅድሚያ ይሄዳሉ ተብሎ የነበረው ወደ ዮርዳኖስ ነበር።

በዛም ከአረብ ሀገራት መሪዎች ጋር ይመክራሉ ተብሎ ነበር። ነገር ግን ከአሜሪካ ከተነሱ በኃላ የአረብ ሀገራት መሪዎች ከባይደን ጋር እንደማይገናኙ እና የነበረውም ስብሰባ መሰረዙ ተሰምቷል።

አሜሪካም ፕሬዜዳንቷ ወደ ዮርዳኖስ እንደማይሄዱና ይህም " የጋራ ውሳኔ " መሆኑን ገልጻለች።

" በእናተ አልተፈፀመም " - ባይደን

ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን እስራኤል በሆስፒታሉ ላይ ጥቃት አልፈፀመችም ብለዋል።

እስራኤል የሚገኙት ጆ ባይደን በጋዛ በሚገኘው " አል አህሊ ባፕቲስት ሆስፒታል " ላይ ፍንዳታ የተፈፀመው በእስራኤል ሳይሆን " በሌላኛው ቡድን " ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ባይደን ለእስራኤሉ ጠ/ሚ ኔታንያሁ ፤ " ትናንትና በጋዛ ሆስፒታል በደረሰው ፍንዳታ በጣም አዝኛለሁ " ያሉ ሲሆን " ባየሁት መሰረት፣ የተደረገው በሌላው ቡድን ይመስላል ፤ እንጂ በአንተ (እስራኤል) አይደለም " ሲሉ ተናግረዋል።

እስራኤል ፤ በሆስፒታሉ ላይ ለደረሰው ጥቃት ያልተሳካ " የኢስላሚክ ጂሃድ " ቡድን ሮኬት ነው ያለች ሲሆን " ሃማስ " እንዲሁም " የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " ድርጅት ጥቃቱ የተፈፀመው በእስራኤል ነው ብለዋል።

" የፍልስጤም ኢስላሚክ ጂሃድ " የእስራኤል ክስ ሀሰተኛ እና ምንም መሰረት የሌለው እንዲሁም ከጭፍጨፋው ተጠያቂነት ለማምለጥ ጣቷን በእስላሚክ ጂሃድ እና ፍልስጤማውያን ላይ የጠቆመችበት የተለመደ የሀሰት እና ቅጥፈት ፈጠራዋ ነው ብሏ

More + @BirlikEthiopia
#USA

" ፕሬዜዳንት በሆንን በአንድ ሳምንት ውስጥ ቲክቶክን እናግዳለን " ያለቱ የሪፐብሊካን እጩዎች !

የአሜሪካ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ በ2024 ይካሄዳል።

የሪፐብሊካን የፕሬዜዳንታዊ እጩዎች ቢሮ በገቡ በመጀመሪያው ሳምንት " #ቲክቶክ " የተሰኘውን መተግበሪያ እንደሚያግዱ ገልጸዋል።

እጩዎቹ ሰሞኑን በነበረ ክርክር መድረክ ላይ ነው ይህን የገለፁት።

እጩዎች የቻይናን መረጃ መሰብሰብን ለመዋጋት አንዴ ፕሬዜዳንት ሆነው ወደ ነጩ ቤተመንግስት ይግቡ እንጂ " ቲክቶክ" ን እስከወዲያኛው እንደሚያግዱት ገልጸዋል።

ክሪስ ክርስቲ የተባሉ የሪፐብሊካን እጩ ምን አሉ ?

እኚህ እጩ " ቲክቶክ " መረጃዎችን ከመሰብሰብ ባለፈ በመላው ሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የወጣት አሜሪካውያንን አእምሮ እየበከለ ነው ብለዋል። " ይህንን የሚያደርጉት ደግሞ ሆን ብለው ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

" ቲክቶክ " በአልጎሪዝሙ አሰቃቂ፣ ያልተገቡ፣ ከፋፋይ፣ አፍራሽ ፣ የወጣቶችን አእምሮ የሚበክሉ ጉዳዮችን ከፍተኛ ደረጃ ወደ ተጠቃሚው እንዲገፋ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ይህም ቻይና አሜሪካንን ለመከፋፈል ይበልጥ እየተጠቀመችበት ያለ ተግባር ነው ሲሉ ከሰዋል።

የሪፐብሊካኑ ሰው የቀድሞው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስልጣን ዘመናቸው " ቲክቶክን ማገድ " በተመለከት ብዙ ሲናገሩ እንደነበር ነገር ግን መተግበሪያውን ማገድ ሲገባቸው ያን አለማድረጋቸው የሚያስወቅስ እንደሆነ ገልጸዋል።

እሳቸው ፕሬዜዳንት ሆነው በመጡ በመጀመሪያው ሳምንት ቲክቶክን እንደሚያግዱ አሳውቀዋል።

ሮን ዴሳንቲስ የተባሉ እጩ ደግሞ " የአሜሪካን ህዝብ ለመጠበቅ ስንል ቲክቶክን የማገድ እርምጃ እናሳያችኃለን " ብለዋል። ፕሬዜዳንት ሆነው ሲመጡም ይህንን እንደሚያደርጉትን ገልጸዋል።

ቲም ስኮት የተባሉት እጩ ፤ " እኛ ማድረግ ያለብን ቲክቶክን ማገድ ነው ፤ አለቀ !! " ብለዋል።

በቀድሞው ፕሬዝደንት ትራምፕ ቲክቶክን ለማገድ ሁለት ጊዜ ሲሞከር አይተናል ያለቱ ስኮት ፤ ነገርግን በፌደራል ፍርድ ቤቶቻችን እንዳይፈፀም ተደርጓል ሲል አስታውሰዋል።

ቲክቶክን ማገድ ካልተቻለ በመተግበሪያው ላይ ያለውን የቻይናን ተፅእኖ መኖር እንደወዲያኛው #ማስወገድ ነው ብለዋል።

ባይትዳንስ የተሰኘው ኩባንያ ንብረት የሆነው " ቲክቶክ " ከዚህ ቀደም በተለይም ግላዊ መረጃን በመበዝበዝ እና ከቻይና መንግሥት ጋር የተቆራኘ ነው በሚል ከፍተኛ ወቀሳ ሲደርስበት ነበር ፤ ኩባንያው የቻይና መንግሥት መረጃውን እንደማያገኝበትና ቻይና ያለው ቲክቶክ ከሌላው ዓለም ፈፅሞ የተለየ መሆኑን ደጋግሞ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቲክቶክ ለምንድነው ሀገራት " ቲክቶክ " ን ለማገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉት ? ከቅርብ ወራት ወዲህ አሜሪካ፣ አውሮፓ፣ ካናዳ ያሉ የህግ አውጪዎች ከፀጥታ እና ደህንነት ስጋት ጋር በማያያዝ ግዙፉን የአጫጭር ቪድዮዎች ማጋሪያ " ቲክቶክ " ን ለማገድ / ለመገደብ የሚያደርጉትን ጥረት ማጠናከራቸውን ኒውዮርክ ታይምስ አስነብቧል። ዋይትሃውስ እኤአ በፌብሩዋሪ 27 የፌዴራል  ኤጀንሲዎች አፕሊኬሽኑን ከመንግሥት…
#USA #TikTok

" ወጣቶችን ቲክቶክ እንዳይጠቀሙ የሚገድብ ረቂቅ ህግ እንደሚወጣ አሳውቃለሁ ... አለቀ !! " - ግሌን ያንግኪን

በአሜሪካ የቨርጂኒያ ግዛት ገዥ ግሌን ያንግኪን ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ሰዎች " ቲክቶክ "ን እንዳይጠቀሙ የሚገድብ ረቂቅ ህግ እንደሚወጣ አሳወቁ።

ያንግኪን ፤ " ቲክቶክ " የማህበራዊ ሚዲያ መድረክ ለህጻናት ልጆቻችን አእምሮአዊ ጤንነት እጅግ ጎጂ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የሪፐብሊካኑ ሰው ወደዚህ እርምጃ እንደሚመጡ ያሳወቁት ባለፈው አመት ቲክቶክን ከማንኛውም የመንግስት ኤሌክትሪክ መሳሪያዎች እና ዋይፋይ #ካገዱ በኋላ ነው።

ያንግኪን ፤ በአጠቃላይ ማህበራዊ ሚዲያ በልጆቻችን ላይ ከባድ እና ቀጣይነት ያለው አሉታዊ ተጽእኖዎች እያሳደረ ነው ብለዋል።

ከነዚህም ውስጥ ፦
- የማህበራዊ ክህሎታቸው እንዲያጡ ፣
- በሳይበር አማካኝነት የማዋረድ፣ ስድብና ሌላም ጎጂ ድርጊት እንዲደርስ፤
- የአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር እንዲስፋፋ አሉታዊ ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑ አመላክተዋል።

በመሆኑም " ወጣቶችን ቲክቶክ እንዳጠቀሙ የሚገድብ ረቂቅ ህግ እንደሚወጣ አሳውቃለሁ ... አለቀ !! " ሲሉ ገልጸዋል።

" ቲክቶክ " ን ልጆች እንዳይጠቀሙ ከሚያግደው ረቂቅ በተጨማሪ ልጆች ከማህበራዊ ሚዲያ ግብይት እና መረጃዎቻቸውን ከመጠቀም እና ከመሸጥ የሚከላከሉ ህጎች እንደሚያወጡ ገልጸዋል።

የቨርጂንያው ገዥ " ሱስ አስያዥ " ብለው ከጠሯቸው የማህበራዊ ሚዲያ የማርኬቲንግ ስልቶች ልጆችን እና ታዳጊዎችን ለመጠበቅ የሚረዱ ረቂቆችን ይፋ እንደሚያደርጉ የተናገሩ ቢሆንም " መቼ ? " የሚለውን አልገለፁም።

በአሜሪካ እንደ አጠቃላይ እስካሁን " ቲክቶክ " ባይታግደም፤ እንቅስቃሴዎች ስለመኖራቸው ግን ተደጋጋሞ ተነግሯል።

በተለይም በርካታ የሪፐብሊካን ዕጩዎች በቀጣይ ምርጫ አሸንፈው ፕሬዜዳንት መሆን ከቻሉ በአጭር ጊዜ መተግበሪያውን ለማገድ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

በተለያዩ ግዛቶች ደግሞ ከደህንነት እንዲሁም ወጣቶችን ከመጠበቅ ጋር በተያያዘ " ቲክቶክ " ከመንግሥት የኤሌክትሪክስ መሳሪያዎች ፣ ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ኮሌጅ ካምፓሶች ዋይፋይ እንዲታገድ ተደርጓል።

" ቲክቶክ " ባለቤት የሆነው የቻይናው ባይትዳንስ ኩባንያ በተለያየ ጊዜ የሚነሳበትን ወቀሳ ውድቅ ሲያደርግ መቆየቱ እየሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia
#USA #Election

" ስደተኞች የሀገራችንን ደም እየበከሉ ነው " - ዶናልድ ትራምፕ

ሪፐብሊካንን በመወከል ለፕሬዝዳንትነት የሚወዳደሩት ዶናልድ ትራምፕ ስደተኞች " የሀገራችንን ደም እየበከሉ ነው " በማለት ተናገሩ።

ትራምፕ ይህ ያሉት #ከሜክሲኮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች በሚገቡበት " ኒው ሃምሻየር " ግዛት ባደረጉት የምርጫ ቅስቀሳ ላይ ነው።

ትራምፕ ለ4 አመት የስልጣን ዘመን በድጋሚ የሚመረጡ ከሆነ ህገወጥ ስደትን እንደሚያስቆሙ እና በህጋዊ ሰደተኞች ላይ ደግሞ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚያደርጉ ተናገረዋል።

ትራምፕ ለደጋፊዎቻቸው ስደተኞች ከደቡብ አሜሪካ በተጨማሪ #ከአፍሪካ፣ ከእስያ እየመጡ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

" ከሁሉም የዓለም ክፍል ወደ ሀገራችን የፈሰሱ ነው " ሲሉ አክለዋል።

ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው መስከረም ወር " ናሽናል ፐልስ " ከተባለው የቀኝ ዘመም ዌብሳይት ባደረጉት ቃለ ምልልስ ስደተኞች " ደማችንን እየበከሉት ነው " የሚል ተመሳሳይ ንግግር አሰምተው ነበር።

በወቅቱ ይህ የትራምፕ ንግግር " ዘረኝነት እና ጥላቻ " የሚያንጸባርቅ ነው የሚል ትችት አስነስቶ ነበር።

የያሌ ፕሮፌሰር እና በዘረኝነት ጉዳይ መጸሀፍ ያሳተሙት ጆናታን ስታንሊ ትራምፕ ቋንቋውን አሁንም ደግመው መጠቀማቸው አደገኛ ነው ብለዋል።

ፕሮሬሰሩ እንደተናገሩት ትራምፕ " የጀርመኖች ደም በጅዊሾች እየተበከለ ነው " የሚለውን የሂትለር ንግግር ያስተጋባ ነው ሲሉ ተችተውታል።

ስታሊ" ትራሞፕ ይህ ቃል በሁሉም የድጋፍ ሰልፎች ላይ እየደገሙት ነው። አደገኛ  የሆኑ ንግግሮችን መደጋገም እንዲለመዱ ያደረጋል " ብለዋል።

ፕሮፌሰሩ እንደተናገሩት ይህ በአሜሪካ የሚኖሩ ስደተኞችን ስጋት ላይ እንዲወድቁ ያደርጋል።

ባለፈው ጥቅምት ወር የትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ ቃል አቀባይ ስቴቨን ቹንግ እንዲህ አይነት ቃላት በመጽሀፍ፣ በዜና እና በቴሌቪዥን የተለመድ ናቸው በማለት በትራምፕ የቀረበውን ትችት " ትርጉም የለሽ " ሲሉ አጣጥለውት ነበር።

Credit - AL AIN News

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#IGAD ዛሬ በኡጋንዳ፣ ኢንቴቤ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግስታት (ኢጋድ) መሪዎች ስብሰባ ይደረጋል። ስብሰባው ትኩረት ከሚያደርግባቸው ጉዳዮች አንዱ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል የተፈጠረው ውጥረት ነው። ሌላው የሱዳን ጦርነት ነው። ለኢጋድ የመሪዎች ስብሰባ እስካሁን ድረስ በታወቀው ፦ የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር የጅቡቲው ፕሬዜደንት ኢሳሜል ኦማር ጌሌህ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት…
#USA #IGAD

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ካምፓላ እና አዲስ አበባን ይጎበኛሉ ተብሏል።

ማይክ ሐመር መጀመሪያ ካምፓላ ገብተው በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ እንዲሁም በሱዳን ጦርነት ላይ በሚመክረው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) መሪዎች ስብሰባ ላይ ይሳተፋሉ።

ከዛም ወደ ኢትዮጵያ፣ አዲስ አባባ ይመጣሉ።

ልዩ መልዕክተኛው በአዲስ አበባ ቆይታቸው፦

" - ከኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በተለይ በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ስላለው ግጭት ውይይት ያደርጋሉ።

- በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያሉትን ግጭቶች አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ይወያያሉ።

- ሰላማዊ ሰዎች እንዲጠበቁ እንዲሁም ሰብዓዊ መብት እንዲከበር ጥሪ ያቀርባሉ።

- ከአንድ ዓመት በፊት በስምምነት የተቋጨውን የትግራይ ጦርነት ተከትሎ የሚከናወነውን ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት፣ ተሃድሶ እና ማሰናበትን በተመለከተ እንዲሁም ተጎጂዎችን መሠረት ስላደረገው የሽግግር ፍትህ ሂደት ይወያያወሉ። " ሲል የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ቢቢሲ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤትን ዋቢ አደርጎ ካሰራጨው ዘገባ ነው የወሰደው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EHRC የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) በአማራ ከልል ምዕራብ ጎጃም ዞን መርዓዊ ከተማ በ20/05/2016 ዓ.ም በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በታጣቂ ቡድኖች መካከል በነበረ ግጭት ከፍተኛ የሆኑ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ መረጃዎች እንደደረሱት ባወጣው መግለጫ አሳውቋል። በእዚህ ግጭት ምክንያት በመርዓዊ ከተማ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ እንደነበር…
#USA #ETHIOPIA #MERAWI

በአማራ ክልል መርዓዊ ከተማ ሰላማዊ ሰዎችን ኢላማ በማድረግ ግድያ የፈጸሙ ላይ ምርመራ ተደርጎ ለፍርድ እንዲቀርቡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጠየቁ።

አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ በኤምባሲው የX ገጽ ላይ ባወጡት መልዕክት በመርዓዊ ከተማ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በሚመለከት የወጡ ሪፖርቶች የአሜሪካ መንግሥትን እንደሚያሳስበው ገልጸዋል።

አምባሳደር ማሲንጋ፣ የክስተቱን አሳሳቢነት ከመግለጻቸው ባሻገር " የግድያውን ፈጻሚዎች ለሕግ ለማቅረብ " ገለልተኛ የሰብዓዊ መብት ተቆጣጣሪዎች ምንም ገደብ ሳይደረግባቸው ወደ ሥፍራው እንዲንቀሳቀሱ እንዲፈቀድላቸው እንዲሁም በግድያው ዙሪያ ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቀዋል።

በአገሪቱ ባሉት የአማራ እና የኦሮሚያ ክልሎችን ጨምሮ በሌሎችም ቦታዎች ላይ " በመንግሥት እና ከመንግሥት ውጪ በሆኑ ኃይሎች በተመሳሳይ የመብት ጥሰቶች እና ጥቃቶችን መፈጸማቸውን የሚያመልክቱ በርካታ የሚረብሹ ሪፖርቶች " እየወጡ መሆናቸውንም አምባሳደሩ ጠቅሰዋል።

" ኃይል ሳይሆን ውይይት ብቸኛው አማራጭ ነው"ም ሲሉ አሳውቀዋል። #USEmbassy #BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#PretoriaAggrement አሜሪካ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች። የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሃመር እና በኢትዮጵያ ከአሜሪካ አምባሳደር ኤቪን ማሲንጋ ጋር ሆነው ወደ ትግራይ መቐለ ተጉዘው ከክልሉ ባለልስጣናት ጋር ውይይት አድርገዋል። አምባሳደር ሀመር ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም ከሌሎች…
#USA

አምባሳደር ሃመር እና አምባሳደር ማሲንጋ በመቐለ ቆይታቸው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (TPLF) ሊቀመንበር የሆኑትን ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤልን አገኝተው ተወያይተዋል።

ውይይታቸው የፕሪቶሪያ ስምምነትን አተገባበርን የተመለከተ ነበር።

በዚህም ወቅት ፤ የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በትግራይ በኩል በፕሪቶሪያ ስምምነት ውል አተገባበር ዙሪያ ብዙ ጉዳዮች ቢፈፀሙም ፦
- ከጦርነት በፊት የነበረው የትግራይ አስተዳደር ግዛት መመለስ
- ህዝብ ነፃ የማውጣት ፣
- ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ ፣
- ለረሃብ ለተጋለጠ ህዝብ ሰብአዊ እርዳታ የማቀረብ ጉዳዮች ሳይፈፀሙ ረጅም ጊዜ መውሰዳቸው ለልኡካኑ ገልፀዋል።

ተመላሽ የሰራዊት አባላት የማቋቋም ጉዳይ ትኩረት የሚሻ ቢሆንም  ቀዳሚው ጉዳይ ከጦርነት በፊት የነበረው የትግራይ አስተዳደር ማረጋገጥና ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ መሆኑ ዶ/ር ደብረፅዮን መግለፃቸውና ውይይቱ በቀጣይ ለሚኖሩ ለውጦች የሃሳብ ልውውጥ እንዲደረገ መግባባት መደረሱ ለማወቅ ተችሏል። 

#TikvahFamilyMekelle
                    
@tikvahethiopia            
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#USA #Ethiopia

አሜሪካ በአማራ ክልል ይንቀሳቀሳሉ ያለቻቸው የፋኖ ኃይሎች " ውይይትን አልቀበልም " ማለታቸውን በመግለጽ ይህ " ለራሳቸውም አይጠቅማቸውም " አለች።

ሀገሪቱ ይህን ያለችው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር በሆኑት ኢርቪን ማሲንጋ አማካኝነት ነው።

አምባሳደሩ ፤ " በአማራ ክልል ውስጥ ውጊያ እያደረጉ የሚገኙት እራሳቸውን ' ፋኖ ' ብለው የሚጠሩ ኃይሎች ' ውይይትን አንቀበልም ' ማለታቸው ለራሳቸውም አይጠቅማቸውም " ብለዋል።

ከመንግስት ጋር በታንዛንያ የሰላም ንግግር ሲያደርጉ የቆዩት የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) ተዋጊዎችን " በድርድር ተስፋ ሳትቆርጡ ፤ መተማመንን ለመገንባት ጥረት አድርጉ " ብለዋቸዋል።

አሜሪካ ይህን ያለችው ዛሬ ግንቦት 7 ቀን 2016 ዓ/ም ኢትዮጵያን በተመለከተ የምትከተለውን ፖሊሲ አስመልክቶ በአምባሳደሯ በኩል ባስተላለፈችው መልዕክት ነው።

በአዲስ አበባ ፤ መርካቶ አካባቢ በሚገኘው የቀድሞ የአሜሪካን ግቢ በነበረ መርሀ ግብር የአሜሪካ አፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመርን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተው ነበር።

Video Credit : US Embassy Addis Ababa / Ethiopia Insider

@tikvahethiopia
#Kenya #USA

የጎረቤት ኬንያ ፕሬዜዳንት በአሜሪካ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።

እ.ኤ.አ ከ2008 ወዲህ ወይም ከ16 ዓመት በኃላ ነው ዋይት ሃውስ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ መሪ በዚህ ደረጃ ተቀብሎ እያስተናገደ የሚገኘው።

አሜሪካን እየጎበኙ የሚገኙት ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ከፍ ያለ አቀባበል እና ከፍተኛ የቀድሞና የአሁን ባለስልጣናት በተገኙበት ልዩ እራት ግብዣ እንደተደረገላቸው ታውቋል።

ከፕሬዜዳንት ጆ ባይደንና ከሌሎች ባለልሰጣናት ጋር ተገናኝተው የሁለትዮሽ ውይይት ያደረጉም ሲሆን ሁነኛ ስምምነቶችም ከአሜሪካ መንግሥት ጋር መፈራረማቸው ተሰምቷል።

ሩቶ ከቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ባራክ ኦባማ ጋርም ተገናኝነትው መክረዋል።

በሌላ በኩል ፥ ኬንያ የሀገሪቱን የጸጥታ ስራዎች እና የሰላም ማስከበር ተልእኮዎቿን ለማሳደግ 16 በአሜሪካ የተሰሩ እጅግ ዘመናዊ ሄሊኮፕተሮች ልትቀበል እንደሆነ " ሲትዝን ቲቪ " ዘግቧል።

ይህ የፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በዋሽንግተን ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ ለኬንያ ካበረከቱት መልካም ነገሮች አንዱ ነው ተብሏል።

ሂሊኮፕተሮቹ እ.ኤ.አ ከ2024 እስከ 2025 መጨረሻ ናይሮቢ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዋይት ሀውስ አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ ኬንያ በመስከረም ወር 150 " M1117 " የታጠቁ እጅግ ዘመናዊ የደህንነት ተሽከርካሪዎችን ትቀበላለች።

More ➡️ @thiqahEth

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA #kenya

የጎረቤታችን ሀገር ኬንያን ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶን ተቀብለው እያስተናገዱ ያሉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ኬንያን ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል የመጀመሪያዋ #የNATO_አባል_ያልሆነች (non-NATO) ዋና አጋር ሀገር እንደምታደርጋት ቃል መግባታቸው ተነግሯል።

@tikvahethiopia
#USA

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በሜክሲኮ በኩል ወደ አሜሪካ የሚገቡ ስደተኞችን ለመቆጣጠር ያለመ አዲስ እና መጠነ ሰፊ ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ዛሬ ይፋ እንደሚያደርጉ ተነግሯል።

ውሳኔው የአሜሪካ ኢሚግሬሽን ባለሥልጣናት በየዕለቱ ከሚመለከቱት በሕገ ወጥ መንገድ የገቡ ተጥገኝነት ጠያቂዎች ቁጥር በላይ አመልካቾች የሚቀርቡ ከሆነ ጥያቄያቸውን ሳይመለከቱ በቀጥታ ከአገር እንዲባረሩ ማድረግ የሚያስችል ሥልጣን ይሰጣል።

ይህም ድንበር ላይ ያሉ ባለሥልጣናት አሜሪካ የሚገቡ #ስደተኞች ቁጥርን እንዲገድቡ እንደሚያስችላቸው ተነግሯል።

ፕሬዝዳንት ባይደን ሥልጣን ላይ በቆዩባቸው ባለፉት 4 ዓመታት ውስጥ ከ6.4 ሚሊዮን በላይ ስደተኞች በሕገ ወጥ መንገድ ወደ አሜሪካ ለመግባት እንደሞከሩ ተነግሯል።

ይህም እስካሁን ከታየው ከፍተኛው ነው።

የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ፤ ባይደን አሁን ላይ በ1952 የወጣውን በአሜሪካ ጥገኝነት የማግኘት ሥርዓትን ለመገደብ የሚያስችለውን ሕግ ለመጠቀም እያሰቡ እንደሆነ ዘግበዋል።

212 (ኤፍ) በመባል የሚታወቀው ሕግ ወደ አሜሪካ የሚገቡ የውጭ ዜጎች " ለአገሪቱ ብሔራዊ ጥቅም አስጊ የሚሆኑ ከሆነ " ፕሬዝዳንቱ " እንዳይገቡ ማገድ "  የሚያስችለው ነው።

#BBC
#USA #Immigration

@tikvahethiopia