TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Somalia

አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ በዓለ ሲመታቸው ይከናወናል።

ለዚህም በዓለ ሲመት የተለያዩ ሀገራት መሪዎች ወደ ሶማሊያ ሞቃዲሾ በመግባት ላይ ይገኛሉ።

ዛሬ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከልዑካቸው ጋር ሞቃዲሾ ገብተዋል።

በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ በተመራው የልዑካን ቡድን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ፣ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ ይገኙበታል።

ዶ/ር ዐቢይ ዛሬ ሞቃዲሾ ከገቡ በኃላ ከፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ጋር መገናኘታቸውን የሶማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሶማሊያ በሚኖራቸው ቆይታ በፕሬዝደንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ በዓለ ሲመት ላይ ንግግር እንደሚያርጉ ፤ በተጨማሪም በበዓለ ሲመቱ ከሚታደሙ ከሌሎች የሀገራት መሪዎች ጋር የሁለትሽ ምክክር እንደሚያደርጉ ተሰምቷል።

ፎቶ ፡ Ahmed K Kosar / Somali Guardian

@tikvahethiopia
#Somalia

የግብፁ " Banque Misr " እና የቱርኪዬ " Ziraat Katilim " ባንኮች ሶማሊያ ውስጥ እንዲሰሩ ፍቃድ ፀደቀላቸው።


ጎረቤት ሶማሊያ ለግብፅ እና ቱርኪዬ ባንኮች የስራ ፍቃድ አፅድቃለች።

የሶማሊያ ማዕከላዊ ባንክ ቦርድ ትላንት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ መስፈርት አሟልተው ለተገኙት ሁለት ዓለም አቀፍ ባንኮች በሀገሪቱ ውስጥ ቅርጫፎቻቸውን እንዲመሰርቱ እና እንዲንቀሳቀሱ ፍቃድ አፅድቋል።

ፍቃዱ ረጅም ወራት ከወሰደ ሂደት በኃላ ነው የፀደቀው።

ፍቃድ የፀደቀላቸው ባንኮች የግብፁ " Banque Misr " እና የቱርኩ " Ziraat Katilim " ሲሆኑ በሶማሊያ የፋይናንስ ሴክተር እና በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ፍቃዱን ያፀደቀው CBS ገልጿል።

ሁለቱ ባንኮች ሶማሊያ ውስጥ እንዲሰሩ ፍቃድ ያገኙ #የመጀመሪያዎቹ ዓለም አቀፍ ባንኮች ሆነው ተመዝገበዋል።

@tikvahethiopia
#Somalia

አልሸባብ ዛሬ #ሶማሊያ ውስጥ ባደረሰው ጥቃት የሰዎች ህይወት ጠፋ።

በሽብር ቡድኑ በሶማሊያ ደቡባዊ አቅጣጫ በተለያዩ ቦታዎች በተፈፀሙ ሁለት የቦንብ ጥቃቶች በርካቶች ተገድለዋል።

በመጀመርያው ጥቃት ታችኛው ሸበሌ ክልል በአፍጎዬ ከተማ በእንስሳት የገበያ ቦታ በተወረወሩ 2 ቦምቦች በትንሹ 4 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን ተነግሯል።

ሁለተኛው ጥቃት ማርካ በተባለችው የወደብ ከተማ የተፈፀመ ሲሆን የወረዳው ኮሚሽነር አብዱላሂ አሊ ዋፎው በጥቃቱ መገደላቸው ተዘግቧል።

ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል።

የአካባቢው ፖሊስ እንዳስታወቀው ጥቃቱ የተፈፀመው የማርክ ወረዳ ኮሚሽነር በወረዳዉ ጽሕፈት ቤት ቅጥር ግቢ ዉስጥ ለተሰበሰቡ ነዋሪዎች ንግግር ሲያደርጉ ነው።

ንግግር ሲያደርጉ የነበሩት ኮሚሽነሩ አብዱላሒ ዓሊ አሕመድ ዋፎው እና ሌሎች ስምንት ተሰብሳቢዎች ወዲያዉ ሞተዋል።

ምንጭ፦ ሮይተርስ እና ዶቼ ቨለ

@tikvahethiopia
#Somalia #SW

ሀሰን ኢብራሂም ሉግቡር ተገደሉ።

የሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ክልል ፍትህ ሚኒስትር ሀሰን ኢብራሂም ሉግቡር በባይዶዋ ከነ ልጃቸው በአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ጥቃት ተገደሉ።

ሚኒስትሩ የተገደሉት ዛሬ ዓርብ ዕለት ከመስጂድ ሲወጡ በተፈፀመ ጥቃት ነው።

በጥቃቱ ሌሎች 11 ሰዎችም ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።

የደቡብ ምዕራብ ክልል ፕሬዜዳንት አብዲአዚዝ ሀሰን ሞሀመድ ግድያውንና ጥቃቱን አውግዘው ከጥቃቱ ጀርባ የአልሸባብ የሽብር ቡድን መኖሩን አመልክተዋል።

ይህ ጥቃት በያዝነው ወር እኤአ በቀን 27 በታችኛው ሸበል ክልል የማርካ ወረዳ አስተዳዳሪ አብዱላሂ አሊ ዋፎውን ጨምሮ ከ10 በላይ ሰዎችን ከገደለው የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት እንዲሁም በአፍጎዬ ከተማ ፍንዳታ ተከስቶ ቢያንስ አራት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች ከቆሰሉበት ጥቃት ከቀናት በኃላ የተፈፀመ ነው።

በሌላ በኩል፤ የአልሸባብ የሽብር ቡድን ዛሬ #ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰነው የሶማሊያዋ የድንበር ከተማ " አቶ " ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት ከፍቶ እንደነበር ቢቢሲ ሶማልኛ ዘግቧል።

አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልወደዱ የሶማሌ ክልል ባለሥልጣን በሰጡት ቃል ፤ የሽብር ቡድኑ አቶ ላይ በ2 ሳምንት ውስጥ ለ2ኛ ጊዜ ጥቃት መሰንዘሩን ይህን ተከትሎ ውጊያ መካሄዱን አመልክተዋል።

ዛሬ ወደ አቶ ዘልቆ ጥቃት የመፈጸም ዓላማ የነበረው የአልሻባብ ታጣቂ ኃይል፤ ያሰበው ሳይሳካ #ሽንፈት እንዳጋጠመው ተናግረዋል።

በፀጥታ ኃይሎችም በኩል ጉዳት መድረሱን ያመለከቱት ባለስልጣኑ ለጊዜው ዝርዝር መናገር አልችልም ብለዋል።

አልሸባብ ከጥቂት ቀናት በፊት ኢትዮጵያን ለመዳፈር ሞክሮ በሶማሌ ልዩ ኃይል ክፉኛ መመታቱ አይዘነጋም። አሁንም በድንበር የተጠናከረ ጥበቃ መኖሩን ለማወቅ ችለናል።

@tikvahethiopia
#Somalia

የአልሸባብ ታጣቂዎች ተገደሉ።

ዛሬ ቅዳሜ በሶማሊያ ቤይ ክልል ባርዳሌ ወረዳ ስር በሚገኘው " ቶስዌይን መንደር " አቅራቢያ የአልሸባብ ታጣቂዎች ተገድለዋል።

የሶማሌ ብሄራዊ ጦርና የሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ግዛት የክልል ጦር በአልሸባብ አሸባሪዎች ላይ ባካሄደው የማጥቃት እርምጃ ሶስት የቡድኑ ታጣቂዎች መገደላቸውን የሶማሊያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USAirstrike የአሜሪካ አየር ጥቃት - በጎረቤት ሶማሊያ ! በጎረቤታችን ሶማሊያ ሂራን ክልል የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር ኃይል የፀረ ሽብር ዘመቻ እያካሄደ ሲሆን ጦሩን ለመደገፍ #አሜሪካ የአየር ጥቃት መሰንዘር መጀመሯ ተገልጿል። አሜሪካ የአየር ላይ ጥቃቱን እንድትሰነዝር የተጠየቀችው በሶማሊያ መንግስት መሆኑን የሀገሪቱ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል። በክስተቱ ንፁሀን ዜጎች ላይ ምንም አይነት…
#US #SOMALIA

አሜሪካ ትላንትና ማክሰኞ ፤ ከሶማሊያ መንግስት ጋር በመተባበር በፈፀመችው የአየር ድብደባ 4 የአልሸባብ የሽብር ቡድን አባላትን መግደሏን አሳውቃለች።

የአልሸባብ ታጣቂዎች የሶማሊያ ጦር ላይ በቤልድዌይኔ ጥቃት የከፈቱ ሲሆን ይህን ተከትሎ የአሜሪካ ጦር በአየር በፈፀመው ድብደባ 4 የቡድኑን አባላት መግደሉ ተገልጿል።

አሜሪካ እርምጃው በሶማሊያ መንግስት በኩል ፍቃድ ኖሮት መፈፀሙን አሳውቃለች።

በጥቃቱ በሲቪል ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ / ሲቪሎች እንዳልተገደሉ ተመላክቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#US #SOMALIA አሜሪካ ትላንትና ማክሰኞ ፤ ከሶማሊያ መንግስት ጋር በመተባበር በፈፀመችው የአየር ድብደባ 4 የአልሸባብ የሽብር ቡድን አባላትን መግደሏን አሳውቃለች። የአልሸባብ ታጣቂዎች የሶማሊያ ጦር ላይ በቤልድዌይኔ ጥቃት የከፈቱ ሲሆን ይህን ተከትሎ የአሜሪካ ጦር በአየር በፈፀመው ድብደባ 4 የቡድኑን አባላት መግደሉ ተገልጿል። አሜሪካ እርምጃው በሶማሊያ መንግስት በኩል ፍቃድ ኖሮት መፈፀሙን…
#Somalia

የጎረቤት ሶማሊያ ብሄራዊ ጦር በሂራን ክልል እያካሄደ ባለው የፀረ ሽብር ዘመቻ ትላንት በማሃስ አውራጃ መሀመድ ወህሊዬ ዋሱጌን የተባለ የአልሸባብ ቡድን ቀደኛ ሰው ጨምሮ 14 ታጣቂዎችን መግደሉን የሶማሊያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

በተጨማሪ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በጦሩ ተይዘዋል።

አሜሪካ ደግሞ የአየር ላይ ጥቃት በመፈፀም የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎችን መደበቂያ ማውደሟ ተገልጿል።

አሜሪካ የአየር ድብደባ የፈፀመችው የፀረሽብር ኦፕሬሽን እያካሄደ የሚገኘውን የሶማሊያ ብሄራዊ ጦርን ለመደገፍ ነው።

ከቀናት በፊት አሜሪካ በሶማሊያ መንግስት ጥያቄ የአየር ጥቃት መፈፀም መጀመሯን መነገሩ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Somalia

" ... የሶማሊያ ህዝብ ማብቂያ በሌለው የሀዘን መግለጫ እና ሀዘን መሰላቸቱን አውቃለሁ " - ሀሰን ሼክ ሞሐመድ

የጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ " አልሸባብ " ን ለማጥፋት ሁሉን አቀፍ ጦርነት ለመክፈት ቃል ገቡ።

ፕሬዝዳንቱ ስልጣን ከያዙ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ባወጡት መግለጫ የሶማሊያ ህዝብ የሰላም ጠላት በሆኑት ጨካኞች ላይ ለሚካሄድ አጠቃላይ ጦርነት ይዘጋጅ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

" የሶማሊያ ህዝብ ማብቂያ በሌለው የሀዘን መግለጫና ሀዘን መሰላቸቱን አውቃለሁ " ያሉት ፕሬዝዳንቱ አሸባሪው ቡድን በሚፈጽመው በእያንዳንዱ ግድያ እጅግ የተከበሩ ሰዎች እየሞቱ ነው ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ ስልጣን ከያዙ ወዲህ ከባድ ነው የተባለው የአልሸባብ ጥቃት ባለፈው አርብ ሞቃዲሾ በሚገኘው በ " ሃያት ሆቴል " ውስጥ ተፈፅሟል። በዚሁ ጥቃትም 21 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 117 ቆስለዋል።

የሶማሊያ ጠ/ሚ ፣ የሀገር ውስጥ ጉዳይ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተገኙበትን የብሔራዊ የፀጥታ ኮሚቴ ስብሰባ ያካሄዱት ፕሬዝዳንት ሞሐመድ " ህዝባችንን የሚያጠፉት አሸባሪዎች የሚቆጣጠሯቸው አካባቢዎች ነጻ እስኪወጡ ድረስ ቡድኑን ለማዳከም ቆርጠን ተነስተናል " ብለዋል።

ይህንንም ፤ መንግሥታት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገልፀው የእቅዱ ዝግጅትና አተገባበሩ እየተካሄደ መሆኑን ማስታወቃቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia #Somalia

" የፕሮግራሙ ይዘት የኢትዮጵያን መንግስት ፖሊሲ #የማይወክል ነው " - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

ትላንት በኢትዮጵያ ብሄራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ (Etv World) በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተሰራጨ ፕሮግራም ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል።

ፕሮግራሙን ተመልክተው ቅሬታቸውን የገለፁ በርካቶች ሲሆኑ ፤ ፕሮግራሙን በተመለከተ የሶማሊያ ሚዲያዎች ሲቀባበሉት ውለዋል።

በEtv የእንግሊዝኛው የተረጋገጠ የፌስቡክ ገፅ ላይ አሁን ድረስ ያለው ይኸው ፕሮግራም ስለ ሱማሊያ የተለያዩ የሚያነሳ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አንዱ አዲሱን ፕሬዜዳንት እና መንግስታቸውን የሚመለከት ነው።

ይህንን ፕሮግራም በተመለከተ ኢትዮጵያ ዛሬ ምሽት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል አጭር መግለጫን አውጥታለች።

የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትላንት በ “Etv WORLD” ፕሮግራም ስለ ሶማሊያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ በሚመለከት በቀረበው ፕሮግራም ላይ ትክክለኛ ያልሆነ ዘገባ መመልከቱን ገልጿል።

ሚኒስቴሩ ፤ የፕሮግራሙ ይዘት የኢትዮጵያን መንግስት ፖሊሲ የማይወክል እና ከሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ጋር የማይጣጣም ነው ብሎታል።

@tikvahethiopia
#Somalia

የጎረቤት ሶማሊያ መንግስት በ " አልሸባብ " ላይ መጠነ ሰፊ ዘመቻ እያካሄደ ሲሆን በዚህ ዘመቻ በርካታ የቡድኑን ታጣቂዎች መግደል ጨምሮ ተይዘው የነበሩ ቦታዎችን ነፃ አድርጓል።

የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር ከጉሪኤል ከተማ በስተምስራቅ 55 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውን የ " ጃው " መንደር በአካባቢው ማህበረሰብ ድጋፍ ከአልሸባብ ነፃ ማድረጉ ተሰምቷል።

ጃው በጉሪኤል እና ኤልቡር መካከል ያለ ስልታዊ ቦታ መሆኑን የሀገሪቱ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ገልጿል። ከዚህ አካባቢ በፊት ባለፈው አርብ በተሰራ ኦፕሬሽን ሳጋልጌድ፣ ያሶማን እና አቦሬይ የሚባሉ አካባቢዎች ከአልሸባብ ነፃ ማድረግ ተችሏል።

በሌላ በኩል ፤ የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር በአካባቢው ማህበረስብ እገዛ በሂራን ክልል በያሶማን መንደር አቅራቢያ በትናንትናው እለት ባካሄደው ዘመቻ 75 የአልሸባብ ታጣቂዎች መገደላቸው ተመላክቷል።

በአጠቃላይ በዚሁ ክልል እስካሁን በተካሄደ የፀረ ሽብር ዘመቻ ኦፕሬሽን 200 የቡድኑ ታጣቂዎች መገደላቸውና 30 መንደሮች ከአልሸባብ ነፃ መደረጋቸውን የሀገሪቱ ጦር አሳውቋል።

Photo Credit : SNTV

@tikvahethiopia
#Somalia #Ethiopia

የሶማሊያ ኘሬዝደንት ሃሰን ሼክ መሃሙድ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ኘሬዝደንት ሃሰን ሼክ መሃሙድ ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ሃሰን ሼክ መሃሙድ በሚኖራቸው ቆይታ የሁለቱ ሃገራት እና ቀጠናዊ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ይደረጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

ፕሬዜዳንቱ ምርጫ አሸንፈው ወደ ስልጣን ከመጡ በኃላ በተለያዩ ሀገራት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን አሁን ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል።

Photo Credit : የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሶማሊያ በጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ለ13 ዓመታት አልሸባብ ሲቆጣጠረው የነበረው ዋና መንገድ ነፃ መደረጉ ተገለፀ። ለ13 አመታት በአልሸባብ ቁጥጥር ስር የነበረው በሂራን ክልል ቡልቡርዴ እና በለድዌይን ወረዳዎች መካከል ያለው ዋና መንገድ የሶማሌ ብሄራዊ ጦር በአካባቢው ነዋሪዎች እገዛ ነፃ ማድረጉን አሳውቋል። የፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ አስተዳደር በአልሸባብ ይዞታዎች ላይ እያካሄደ ያለውን እጅግ…
#Somalia

ሶማሊያ የአልሸባብ ከፍተኛ መሪ መገደሉን ገለፀች።

የሶማሊያ መንግስት ለረጅም ጊዜ ሲያፈላልገው የነበረው የአልሸባብ ከፍተኛ መሪ አብዱላሂ ናዲር በሶማሊያ ብሄራዊ ጦር እና በዓለም አቀፍ የፀጥታና ደህንነት አጋሮች በተካሄደ ኦፕሬሽን መገደሉን የሀገሪቱ መንግስት አሳውቋል።

የአልሸባቡ ከፍተኛ መሪ የተገደለው በመካከለኛው ጁባ ክልል ሃራምካ መንደር መሆኑ ተገልጿል።

አብዱላሂ ናዲር ከአልሸባብ መስራቾች መካከል እና ከፍተኛ አመራሮች አንዱ ሲሆን ሞቱን ተከትሎ የሶማሊያ መንግስት " እሾሁ ከሶማሊያ ህዝብ ላይ ተወግዷል " ሲል ገልጿል።

ከዚህ ቀደም ይህንን ግለሰብ ላገኘው / ለጠቆመ 3 ሚሊዮን ዶላር እንደሚሰጥ ተገልጾ ነበር።

በሌላ በኩል ፤ የፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ መንግስት በአልሸባብ ላይ እያካሄደ ያለውን መጠነ ሰፊ ዘመቻ የቀጠለ ሰሆን ባለፉት ሁለት ሳምንታት በሞቃዲሾ የአልሸባብ መረብ በፀጥታ ኃይሎች በተሳካ ሁኔታ መበጣጠሱን እና የቡድኑን አተባባሪዎች፣ ተላላኪዎች እንዲሁም 5 የሚደርሱ ተከራተውበት የነበሩ ቤቶችን በቁጥጥር ስር ማዋላቸው ተገልጿል።

ምንም እንኳን በአልሸባብ ላይ የተከፈታው ዘመቻ ተጠናክሮ ቢቀጥልም ከሰሞኑን የየሞቃዲሾ ፖሊስ ኮሚሽነር ፋርሃን ሞሐሙድ አዳን በአልሻባብ መንገድ ዳር በተጠመደ የቦንብ ፍንዳታ ተገድለዋል።

በአልሸባብ ላይ እየተካሄደ ካለው ዘመቻ ጋር በተያያዘ ትላንት የሱማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃሙድ እያንዳንዱ ሱማሊያዊ አልሸባብ ለመዋጋት መሰለፍ አለበት ያሉ ሲሆን ከአልሸባብ ጋር በሚደረገው ፍልሚያ ገለልተኛ የሚባል አቋም ፈጽሞ ሊኖር አይችልም ብለዋል።

ፕሬዜዳንቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በርካታ ዜጎች ከአልሸባብ ጋር የሚደረገውን ውጊያ እየተቀላቀሉ መሆኑን አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሶማሊያ #ኤርትራ የ5 ሺህ የሶማሊያ ወታደሮች ጉዳይ ከምን ደረሰ ? የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ፤ የሶማሊያ ወታደሮች ከኤርትራ ያልተመለሱበት ምክንያት ፤ ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሀገሪቱ ውስጥ (በሶማሊያ) ባለው የፖለቲካ ልዩነት ምክንያት ሊመልሷቸው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው መሆኑን ገልፀዋል። ኤርትራ የሶማሊያን ኃይል በማሰልጠን ረገድ ጥሩ ሀሳብ እንዳላትም ፕሬዜዳንቱ ተናግረዋል። …
#Somalia #Eritrea

የሶማሊያው ፕሬዜዳንት በ3 ወር ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ  ወደ ኤርትራ አቅንተዋል።

የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ለ4 ቀን የስራ ጉብኝት ዛሬ ኤርትራ፣  አስመራ መግባታቸው ታውቋል።

የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አስመራ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው የሶማሊያ አቻቸውን ተቀብለዋቸዋል።

ፕሬዝዳንት ሙሀሙድ ወደ ፕሬዜዳንትነት የስልጣን መንበር ከመጡ በኃላ ወደ ኤርትራ በስራ ጉብኝት ሲያቀኑ ይህ ሁለተኛቸው ነው።

ከሶስት ወር በፊት ነበር ለስራ ጉብኝት ወደ ኤርትራ ሄደው የነበር።

በወቅቱ በዛው በኤርትራ ያሉ የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር አባላትን (ከፕሬዜዳንት ኢሳያስ ጋር) እንደጎበኙ ፣ ከጉብኝቱ በኃላ ወታደሮቹን ወደ ሀገራቸው ሶማሊያ ለመመለስ በሚቻልበት መንገድ ላይ እየሰሩ መሆኑን ፤ በኤርትራ ከነበራቸው ቆይታ በኃላ ወደ አሜሪካ በሄዱበት ወቅትም በኤርትራ ያሉትን 5,000 የሶማሊያ ጦር አባላትን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የአሜሪካን ድጋፍ እንደጠየቁ አይዘነጋም።

ፕ/ት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ፤ የሶማሊያ ወታደሮች ከኤርትራ ያልተመለሱበት ምክንያት ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሀገሪቱ ውስጥ (በሶማሊያ) ባለው የፖለቲካ ልዩነት ምክንያት ሊመልሷቸው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው መሆኑን መግለፃቸው እና ኤርትራ የሶማሊያ ወታደሮችን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን እያስታጠቀችም እንደሆነ መግለፃቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን መጥራቷን ተከትሎ አምባሳደር አብዱላሂ ዋርፋ ወደ #ሞቃዲሾ ማቅናታቸው ተሰምቷል። በሌላ በኩል ደግሞ ፤ የሶማሊያ ሁለቱ የፌደራል ፓርላማ ምክር ቤቶች በአሁን ሰዓት አስቸኳይ የጋራ ስብሰባ የተቀመጡ ሲሆን በዚህ ስብሰባ ላይ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል። ከ100 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ የወደብ እና…
#Somalia #Somaliland

" የሶማሊያ ደካማ መንግስት ይሄን ታሪካዊ ስምምነት ለማስቆም ምንም አይነት ሕጋዊነት የለውም " - አብዱላሂ አርሼ (የሶማሊላንድ ባለስልጣን)

የቀድሞ የሶማሊላንድ " የሀገር ውስጥ " ሚኒስትር አማካሪ እና በአሁን ሰዓት በሶማሌላንድ " የሀገር ውስጥ " ሚኒስቴር የሚዲያ እና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር የሆኑት አብዱላሂ አርሼ የሶማሊያን መንግሥት " ደካማ መንግሥት " ሲሉ ጠርተው በኢትዮጵያ እና በሶማሊላንድ ሪፐብሊክ መካከል የተፈረመውን #ታሪካዊ_ስምምነት ለማስቆም ምንም አይነት ሕጋዊነት የለውም ብለዋል።

" የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እውቅና የሰጠው የሶማሊያ ስርዓት እንደ ወቀደ መንግስት ነው፣ ሞቃዲሾ ውስጥ የአስተዳደር ስርዓት የለም። " ሲሉ ጠንካራ ትችት ሰንዝረዋል።

ኢስማኤል ሺርዋክ የተባሉ የሶማሊላንድ ዲፕሎማት ደግሞ ፤ " ሀገራችን አንድ እርምጃ ወደፊት ስትሄድ ሶማሊያ በታሪክ ግልፅ የሆነ ጥላቻ  አሳይታለች። " ያሉ ሲሆን " ሶማሌላንድ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (#UAE) ስምምነት ላይ ሲደርሱ ተመሳሳይ እርምጃ ወስደዋል፣ ነገር ግን ምንም አይነት ውጤት አላመጣም። " ብለዋል።

" እንደ አንድ ሉዓላዊ ሀገር የዜጎቻችንን ጥቅም መሰረት አድርገን የሚያስፈልገውን እንወስናል " ሲሉ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ዛሬ ለሁለቱ የፌዴራል ም/ቤት አባላት ንግግር ማድረጋቸው የተሰማ ሲሆን የሶማሊላንድ እና የኢትዮጵያን የትብብር ስምምነት ሰነድ ተቃውመዋል።

" አንድም ኢንች የሶማሊያ ግዛት በማንም ሊፈረም አይችልም ፤ሉዓላዊነታችንንና የግዛት አንድነታችንን እንጠብቃለን ፤ በዓለም አቀፍ ህጎች መሰረት እናስከብራለን፤ እያንዳንዱን ኢንች መሬት እንጠብቃለን፤ ሶማሊያ የሶማሊያውያን ነች ፤ ይሄ የመጨረሻው ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" አቶ መለስ ዜናዊ በሶማሊያ ውስጥ የገቡት ጣልቃ ገብነት የአልሸባብን መነሳት አስከትሏል " ሲሉ የተደመጡት ፕሬዜዳንቱ " የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እርምጃም ያሸነፍነውን አልሸባብ ዳግም እንዲነሳሳ ሌላ ዕድል የሚሰጥ ነው " ብለዋል።

" የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጥር 1 ከያዙት መንገድ እንዲመለሱ " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ ያላቸው አማራጭ አንድ ብቻ ነው እሱም በሰላም መኖር ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

የሶማሊንላንድ ባለልስጣናት ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን በሶማሊያ ባለስልጣናት ላይም ጠንክራ ትችት እየሰነዘሩ ይገኛሉ። ስምምነቱን የማስቆም ምንም አይነት አቅም የላቸውም ሲሉ እየተደመጡ ናቸው።

@tikvahethiopia
#Somaliland #Somalia

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ለቢቢሲ አማርኛ በሰጡት ቃል ፤  ዛሬ ወደ ሶማሊላንድ መዲና ሃርጌሳ ሲበር የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን የሶማሊያ አየር ክልል ውስጥ ከመግባቱ በፊት እንዲመለስ መደረጉን ተናግረዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚ፤ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ ሃርጌሳ ሲጓዝ የነበረው አውሮፕላን ከሶማሊያ በኩል " ፍቃድ የለውም " በመባሉ ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ ለማረፍ ተገዷል ብለዋል።

" ወደ ሃርጌሳ እየሄደ የነበረው አውሮፕላን ተመልሷል። ምክንያቱም በረራውን ከጀመረ በኋላ ከሶማሊያ በኩል ፍቃድ አልሰጠንም የሚል ጥያቄ ተነስቶ ነው። " ሲሉ አስረድተዋል።

የበረራ መከታተየ " ፍላይትራዳር24 " በተባለው ድረ ገጽ ላይ መመልከት እንደሚቻለው ዛሬ ጥር 8/2016 ዓ.ም. ሁለት በረራዎች ወደ ሶማሊያ ተደርገዋል።

መደበኛው የበረራ ቁጥር ኢቲ372 ረፋድ 5 ሰዓት ላይ ሃርጌሳ ማረፉን ፍላይትራዳር ያሳያል።

ይሁን እንጂ የበረራ ቁጥር ኢቲ8372 የሆነው ዲ ሃቪላንድ-400 አውሮፕላን ጠዋት 2፡30 ከአዲስ አበባ ተስቶ ወደ ሃርጌሳ አቅጣጫ እየበረረ ሳለ የጂግጂጋ ሰማይ ላይ በመዞር ረፋድ 4፡30 አካባቢ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተመልሶ አርፏል።

አቶ መስፍን ጣሰው ፤ የትኛው የአየር መንገዱ አውሮፕላን እንዲመለስ እንደተደረገ እና እንዲመለስ በተደረገው አውሮፕላን ተሳፍረው ስለነበሩት መንገደኞች ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ነገር ግን ወደ ተነሳበት መድረሻ እንዳይበር ተከልክሎ ጉዞው የተስተጓጎለውን አውሮፕላን በተመለከተ ንግግር ከተደረገ በኋላ በረራው ዳግም እንዲቀጥል መደረጉን ተናግረዋል።

የሶማሊያ የማስታወቂያ ሚኒስትር ዳውድ አዌይሳ የኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን የያዘ አውሮፕላን ፍቃድ ስላልነበረው ወደ ሃርጌሳ እንዳይገባ ተከልክሏል ሲሉ ለቢቢሲ አማርኛ ተናግረዋል።

የሶማሊያ ሲቪል አቪዬሽን ምን አለ ?

- የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ኢቲ8372 ፍቃድ ስላልነበረው ሃርጌሳ ላይ እንዳያርፍ ተከልክሏል።

- የኢቲ 8273 በረራ ከሶማሊያ ማግኘት የነበረበትን ፈቃድ ስላልነበረው የዓለም አቀፍ የበረራ ሕግን በመተላለፉ ወደ አገሪቱ የአየር ክልል እንዳይገባ ተደርጓል።

- ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ ከተደረገው አውሮፕላን ውጪ በሁለቱ አገራት መካከል የሚደረጉት መደበኛ በረራዎች ቀጥለዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ...

የተለያዩ የሶማሌላንድ አክቲቪስቶች እና ጋዜጠኞ ዛሬ ወደ ሶማሌላንድ በገባው አውሮፕላን የኢትዮጵያ መንግሥት ልዩ ልዑካን ስለመኖራቸው እየገለፁ ይገኛሉ።

እኚህ ልዑካን ከሶማሌላንድ መንግሥት ጋር ለመምከር የመጡ ናቸው ብለዋል።

ምንም እንኳን ጋዜጠኞቹና አክቲቪስቶቹ ይህን ቢሉም የሶማሌላንድ መንግሥት በይፋ ምንም ያለው ነገር የለም።

የኢትዮጵያ መንግሥት እየተባለ ስለሚገኘው ጉዳይ ሆነ ወደ ሶማሌላንድ ልዑክ ስለመላኩ ያለው ነገር የለም።

በሌላ በኩል የሶማሊያ ጋዜጠኞች እና አክቲቪስቶች የኢትዮጵያ ልዑካን የያዘ አውሮፕላን ወደ ሀርጌሳ እንዳይገባ መደረጉን ሲፅፉ ተስተውለዋል።

የኢትዮ-ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመ በኃላ የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ግንኙነት የሻከረ ሲሆን ሶማሊያ ኢትዮጵያ ላይ ዛቻ እንስከመሰንዘር ደርሳለች።

ኢትዮጵያ ከሶማሌለንድ ጋር የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት የትኛውንም ሀገር / አካል የማይጎዳ፣ ዓለም አቀፍ ህግንም ያልጣሰ መሆኑን በተደጋጋሚ ገልጻለች። የህዝቧን ጥቅም ለማስጠበቅ በሁሉም የሰላማዊ መንገዶች ፍላጎቷን እንደምታሳካም አሳውቃለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሶማሊያ እና ኤርትራ ምን መከሩ ? የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ወደ ኤርትራ አቅንተው የሁለት ቀን የስራ ጉብኝት አድርገው ወደ ሞቃዲሾ ተመልሰዋል። ፕሬዜዳንቱ ጉብኝታቸውን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር። በማብራሪያቸውም ፤ " ኤርትራን በተደጋጋሚ ጎብኝቻለሁ። ኤርትራ ለኛ እንደ ቤታችን ናት " ብለዋል። ወደ ኤርትራ የሄዱት ፦ - ኤርትራ ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገች ባለችበት በሶማሊያ…
#Somalia #Eritrea

የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼይክ ማሕሙድ ዳግም ወደ አስመራ ማቅናታቸው ተነግሯል።

ፕሬዝደንቱ ዛሬ አስመራ ሲደርሱ የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ተቀብለዋቸዋል።

ሐሰን ሼይክ ማሕሙድ በፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ #ግብዣ ለሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት ወደ አስመራ እንደተጓዙ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል ገልጸዋል።

የሶማሊያ ብሔራዊ የዜና ወኪል (SONNA) ሀሰን ሼይክ መሕሙድ ከፕሬዝደንት ኢሳያስ ጋር በሁለቱ ሀገሮች ትብብር ላይ እንደሚወያዩ አስታውቋል።

የሶማሊያው ፕሬዝደንት ባለፈው ጥር ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ “የአጋርነት እና የትብብር የመግባቢያ ሥምምነት” በተፈራረሙ በቀናት ልዩነት ወደ አስመራ አቅንተው ከፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ተገናኝተው ነበር።

መረጃውን የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር / SONNAን ዋቢ በማድረግ ያጋራው ዶቼቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

Photo Credit - Yemane G. Meskel

@tikvahethiopia
#Puntland #Somalia

ፑንትላንድ ለሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ዕውቅና መስጠት ማቆሟን ይፋ አድርጋለች።

ከፊል ራስ ገዝ የሆነችው #ፑንትላንድ በሞቃዲሾ ለሚገኘው ለሶማሊያ የፌደራል መንግሥት ከዚህ ቀደም ሰጥታው የነበረውም ዕውቅና አንስታለች።

የፑንትላንድ መንግሥት ካቢኔ አስቸኳይ ስብሰባ አካሂዶ ፑንትላንድ የሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ተቋማት ላይ የነበራትን መተማመን በማጣቷ ትሰጥ የነበረውን ዕውቅና እንዳነሳች አሳውቋል።

ምክንያቱ ምንድነው ?

የሶማሊያ መንግሥት ፓርላማ ብዙ ባወዛገበ ሂደት በአገሪቱ ሕገ መንግሥት ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ ውሳኔ አሳልፏል።

የሕገ መንግሥት ማሻሻያው ፕሬዝዳንቱ የአገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር የማሰናበትን ሙሉ ሥልጣን የሚሰጥ ሲሆን ‘ አንድ ሰው አንድ ድምጽ ’ የሚለውን ዓለም አቀፍ የምርጫ መርህ ተግባራዊ እንዲሆን የሚያደርግና ሌሎችም ማሻሻያዎች አሉበት።

NB. በሶማሊያ #ውስብስብ የሆነውን እና በጎሳ መሠረት የሚደረገውን ምርጫ ከ50 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት ቆይታለች፡፡ አሁን ' አንድ ሰው አንድ ድምፅ ' የሚለው ማሻሻያ በፑንትላንድ ባለልስጣናት ተቃውሞ ገጥሞታል።

በአጠቃላይ የፌዴራል መንግሥት ያካሄደው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ በፑንትላንድ አልተወደደም ውድቅም ተደርጓል።

ፑንትላንድ ፤ " በጋራ መግባባት ላይ የሚደረስበት ሕገ መንግስታዊ ሂደት እስከሚፈጠር ድረስ የፑንትላንድ አስተዳደር ለፌዴራል ተቋማት እውቅና አይሰጥም፣ ተቋማቱ ላይም እምነት የለውም " ብላለች።

ሕዝበ ውሳኔ (#ሪፈረንደም) የሚደረግበት ሕገ መንግስት እስከሚወጣ ድረስ፣ ፑንትላንድ የራሷ የሆነ መንግስታዊ ስልጣን እንደሚኖራት አስታውቃለች፡፡

ከአሁን በኋላ ፍላጎቷን ለማስጠቅ ከማዕከላዊ የሶማሊያ መንግሥት እውቅና ውጪ በራሷ አማካይነት #የውጭ_ግንኙነቶችን እንደምታደርግ ገልጻለች።

ይህ የፑንትላንድ ውሳኔ ከሶማሊያ ተነጥሎ ነጻ አገርነትን ከማወጅ ጋር ሊስተካከል እንደሚችል በመጥቀስ #ከሶማሊላንድ ቀጥሎ ለፌደራል መንግሥቱ ሌላ ራስ ምታት እንደሚሆን ተንታኞች እየገለጹ ነው።

ፑንትለንድ በተፈጥሮ ሃብቶችና #በቦሳሶ_ወደቧ በመተማመን እ.አ.አ 1998 ነው ከፊል ራስ ገዝ መሆኗን ያወጀችው። እራሷን እንደ ነጻና ሉኣላዊ ሀገር የምትቆጥረው የሶማሊላንድ ጎረቤትም ናት።

መረጃው ከቪኦኤ እና ቢቢሲ የተውጣጣ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Puntland #Somalia ፑንትላንድ ለሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ዕውቅና መስጠት ማቆሟን ይፋ አድርጋለች። ከፊል ራስ ገዝ የሆነችው #ፑንትላንድ በሞቃዲሾ ለሚገኘው ለሶማሊያ የፌደራል መንግሥት ከዚህ ቀደም ሰጥታው የነበረውም ዕውቅና አንስታለች። የፑንትላንድ መንግሥት ካቢኔ አስቸኳይ ስብሰባ አካሂዶ ፑንትላንድ የሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ተቋማት ላይ የነበራትን መተማመን በማጣቷ ትሰጥ የነበረውን ዕውቅና…
#Somalia

° " ስለዚህ ጉዳይ መረጃው የለኝም " - አቶ ነብዩ ተድላ

ሶማሊያ ፥ በሶማሊያ #የኢትዮጵያን_አምባሳደር የሆኑትን ሙክታር ሞሃመድ ዋሬን ወደ ሀገራቸው #እንዲመለሱ ማድረጓን ሁለት ከፍተኛ የሶማሊያ ባለስልጣናትን ዋቢ በማድረግ #ሮይተርስ ዘግቧል።

ሶማሊያ የኢትዮጵያን አምባሳደር ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ያደረገችበት ምክንያት ከሶማሊላንድ ጋር የገባቸው የወደብ መግባቢያ ስምምነት እንደሆነ ተነግሯል።

ከዚህ ባለፈ ሶማሊያ በፑንትላንድ እና ሶማሊላንድ ያሉ የኢትዮጵያን ቆንስላ ጽህፈት ቤቶችን ዘግቻለሁ ብላለች።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ በጉዳዩ ዙሪያ ምንም አይነት መረጃ እንደሌላቸው እንደነገሩት ሮይተርስ አስነብቧል።

የፑንትላንድ እና ሶማሊላንድ ነገር ?

ፑንትላንድ ከሕገ-መንግስት ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ለሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ዕውቅና መስጠት ማቆሟን ከቀናት በፊት ይፋ ማድረጓ ይታወሳል።

ከአሁን በኃላም ማንኛውም ፍላጎቷን ለማስጠበቅ ከማዕከላዊ የሶማሊያ መንግሥት እውቅና ውጪ በራሷ የውጭ ግንኙነትም እንደምታደርግ ገልጻለች።

ሶማሌላንድም ምንም እንኳን እስካሁን ሶማሊያ ' የራሴ ግዛት ነሽ ' ብትላትም ራሷን እንደ ነጻ ሀገር መቁጠር ከጀመረች አመታት አልፈዋል። የውጭ ግኝኑነቶችንም ታደርጋለች።

የሰሞኑን የፑንትላንድ ነገር ለሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት " በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ " ሆኖበታል።

ከፊል ራስ ገዟ ፑንትላንድ ሰሞኑን ፥ " ከሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት ጋር ተቆራጠናል ፤ እውቅናም አልሰጥም " ካለች በኃላ ከፍተኛ ባለስልጣናቷ ኢትዮጵያ / አዲስ አበባ ለውይይት መግባታቸው መነጋገሪያ ሆኗል።

እዚህ አዲስ አበባ የመጣው በገንዘብ ሚኒስትሯ ሞሃመድ ፋራህ ሞሀመድ የተመራ ልዑክ ነው።

ልዑኩ ከኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ ጋር መክሯል።

በዚህም ኢትዮጵያ ከፑንትላንድ ጋር ያላትን ዘርፍ ብዙ ትብብሮች ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗ ተገልጿል።

የፑንትላንድ ልዑክም ፥ ኢትዮጵያ በፑንትላንድ በጸጥታና በትምህርት ዘርፍ ድጋፍ እያደረገች መሆኑን ገልጾ የፑንትላንድ መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ግንኙነት የማሳደግ ፍላጎት እንዳለው አረጋግጧል።

በዚህ ወቅት የፑንትላንድ ባለስልጣናት ኢትዮጵያ መምጣታቸው ግጥምጥሞች ወይስ ከወቅታዊ ሁኔታው ጋር የተያያዘ ነው ?

" ጉብኝቱ የቆየ ቀጠሮ ነው " - አቶ ነብዩ ተድላ

ዛሬ በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብዩ ተድላ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህም ወቅት ፑንትላንድ በገንዘብ ሚንስትሯ መሀመድ ፋራህ የተመራ ልዑክ በኢትዮጵያ አ/አ ጉብኝት ማድረጉን ገልጸዋል።

ይህ ጉብኝት ከሰሞነኛው የፑንትላንድ ወቅታዊ ጉዳይ ጋር #የማይገናኝ እንደሆነ እና የጉብኝት ፕሮግራሙም የቆየ ቀጠሮ መሆኑን አስረድተዋል።

@tikvahethiopia
#Somalia

• " የትውልድ ሀገሬ እየሄደችበት ያለው አቅጣጫ በዚህ መጠን አስግቶኝ አያውቅም "- ሙርሳል ካሊፍ


ጎረቤት ሶማሊያ በሀገሪቱ የጸጥታ ክፍተት ሊፈጠር ይችላል ስትል አስጠንቅቃ ፤ የአፍሪካ ሰላም አሰከባሪ ኃይሎች ከሶማሊያ ለቀው የሚወጡበትን ፍጥነት እንዲቀንሱ መጠየቋ ተሰምቷል።

ሮይተርስ ተመለከትኳቸው ያላቸው ሰነዶች እንደሚያሳዩት ከሶማሊያ ጋር ድንበር የሚዋሰኑ አጎራባች ሀገሮች፣ ዳግም እያንሰራራ የሚገኘው የአል-ሻባብ ቡድን ስልጣን ሊቆጣጠር ይችላል የሚል ስጋት ገብቷቸዋል።

በሶማሊያ የሚገኘው የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ (አትሚስ) ሰላም አስከባሪ ኃይል እ.አ.አ በታህሳስ መጨረሻ ሙሉ ለሙሉ ሶማሊያን ለቆ ለመውጣት ዝግጅቱን የጨረሰ ሲሆን በቁጥር አነስተኛ የሆነ ኃይል በቦታው እንደሚተካ ይጠበቃል።

ሆኖም የሶማሊያ መንግስት ለአፍሪካ ህብረት ሰላም እና ጸጥታ ም/ቤት ጊዜያዊ ሊቀመንበር ባለፈው ወር በላከው ደብዳቤ፣ አሁን ካሉት 4 ሺህ ወታደሮች ግማሽ የሚሆኑትን እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ለማስወጣት የተያዘውን እቅድ ወደ መስከረም እንዲያሻግር ጠይቋል።

መንግስት ቀድም ሲል ለህብረቱ አስገብቶት በነበረው እና ሮይተርስ በተመልከተው ሰነድም፣ ሰላም አስከባሪው ኃይል ለቆ የሚወጣበት ጊዜ በሶማሊያ ኃይሎች " ዝግጁነት እና አቅም ላይ እንዲመሠረት " ጠይቆ ነበር።

በተመድ የፀጥታው ም/ቤት ተልዕኮ የተሰጠው ቡድን ባካሄደው የጋር ግምገማም " የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል በችኮላ መውጣታቸው የፀጥታ ክፍተት እንደሚፈጥር " አስጠንቅቋል።

የፓርላማው መከላከያ ኮሚቴ ገለልተኛ አባል የሆኑት ሙርሳል ካሊፍ ፤ " የትውልድ ሀገሬ እየሄደችበት ያለው አቅጣጫ በዚህ መጠን አስግቶኝ አያውቅም " ብለዋል።

ሶማሊያ ለሚገኘው የአፍሪካ ህብረት ጸጥታ ኃይል ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ደጋፊ የሆኑት አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት የሰላም አስከባሪውን ኃይል ለመቀነስ የወሰኑት ዘላቂነት ያለው የረጅም ጊዜ የገንዘብ ድጋፍ የማድረጉ ሁኔታ ስጋት ውስጥ ስለከተታቸው መሆኑን አራት የዲፕሎማቲክ ምንጮች እና አንድ የዩጋንዳ ከፍተኛ ባለስልጣን ለሮይተርስ ተናግረዋል።

የሶማሊያ ፕሬዝዳንትና የጠ/ሚ ፅ/ ቤት በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አልሰጡም።

#ሮይተርስ #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ይህ በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስም በተለይ በ X መተግበሪያ ላይ እየተራጨ ያለው መግለጫ ሀሰተኛ እና የተቀነባበረ ነው። የሚኒስቴሩን የቀድሞ ሎጎ በመጠቀም እየተሰራጨ ያለው ይህ መረጃ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶሌላንድ ጋር የተፈራረመችውን የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ፦ - በUN - በEU - BRICS (ኢትዮጵያ እራሷ አባል የሆነችበት) - በኢስላሚክ ሀገራት ከፍተኛ ጫና እንደሰረዘችው…
#Ethiopia #Somalia

" ልዑካኑ የቀጥታ የፊት ለፊት ንግግር / ውይይት አላደረጉም " - የሶማሊያው ፕሬዜዳንት

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አሸማጋይነት ትላንት አንካራ ውስጥ ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል።

በቱርክ ጋባዥነት በተደረገው ውይይት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታየ አጽቀስላሴ እና የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አህመድ ሞሊም የመሯቸው ልዑካን አንካራ ተገኝተው ነበር። 

ከውይይቱ በኃሏ የሶስቱ ሀገራት የጋራ መግለጫ ወጥቷል።

መግለጫው ፥ ሚኒስትሮቹ ያላቸውን ልዩነቶች ለሁለቱም ተቀባይነት ባለው ማዕቀፍ ውስጥ ለመፍታት ያሉ ሁኔታዎችን እንደዳሰሱ ገልጿል።

ሚኒስትሮቹ በተናጥል በግልጽነት ፣ ወዳጅነት ባለው እና የወደፊቱን ያለመ ውይይት እንደነበራቸው ነው የተመላከተው።

ሁለቱ አገራት ችግሮቻቸውን ለመፍታትና ቀጣናው እንዲረጋጋ የጀመሩትን ውይይት ለመቀጠል ተስማምተዋል የተባለ ሲሆን ለሁለተኛ ዙር ውይይት በአንካራ ነሐሴ 27/ 2016 ዓ.ም እንደሚገናኙ ተገልጿል።

ኢትዮጵያ ራሷን በነጻ አገርነት ካወጀችው ሶማሊላንድ ጋር ከ6 ወራት በፊት የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች ወዲህ በይፋ ተገናኝተው ሲመጋገሩ ይህ የመጀመሪያቸው ነው።

የጋራ መግለጫው ሁለቱ አገራት ልዩነታቸውን ለሁለቱም ተቀባይነት ባለው ማዕቀፍ ለመፍታት ያሉ ሁኔታዎችን እንደዳሰሰ ቢገልጽም እነዚህ ተቀባይነት አላቸው ስለተባሉ ጉዳዮች የተጠቀሰ ጉዳይ የለም።

በሌላ በኩል ፥ የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ ትላንት ውይይቱ ካበቃ በኃሏ ባሰሙት ንግግር ፦
- ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር ከተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ወደኋላ የምትመለስበትን ምንም ምልክት አላሳየችም፤
- ከያዘችው መንገድ እየተመለሳች ስለመሆኑ ምንም ምልክት የለም ፤
- አንካራ ውስጥ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ልዑካን ቀጥተኛ ንግግር አላደረጉም ይልቅም ቱርክ በመሃል እንደ አስታራቂ ሆና እየሰራች ነበር ብለዋል።

ከሰሞኑን የኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትና ከዛም የውጭ ጉዳይ መ/ቤትን ሎጎ በመጠቀም አንካራ ውስጥ በተደረገ ውይይት " ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር የገባችውን ስምምነት  ሰርዛለች " የሚሉ ሀሰተኛ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።

#Ethiopia #Somalia #Turkey

@tikvahethiopia