TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የጀርመን ፌዴራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር #ፍራንክ_ዋልተር_ሽቴይንሜይር በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ትላንት ጥር 19 ቀን 2011 ዓ.ም ከምሽቱ 3 ስዓት አዲስ አበባ ገብተዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 20/2011 ዓ.ም.

የጀርመን ፌዴራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር #ፍራንክ_ዋልተር_ሽቴይንሜይር በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።
.
.
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀድሞ አፈ ጉባኤ አቶ #ዳዊት_ዮሃንስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።
.
.
ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል #የደም_ስር_መጥበብ ችግር ላለባቸው ታካሚዎች ከዛሬ ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የፒሲአይ የነጻ ህክምና አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
.
.
ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ ኢትዮጵያን እየጎበኙ ካሉት ከጀርመን ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፍራንክ ዋልተር ስታይንማየር ልዑካቸውን ተቀብለው አነጋግረዋል።
.
.
ለኢፌድሪ ፕረዝዳንት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ታከለ ኡማ(ኢ/ር) የEuropean Tourism Academy Membership ሽልማት ሊሠጥ እንደሆነ ተሰምቷል።
.
.
የኢትዮጵያ ክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ በ2011 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት 4 ሚሊየን 234 ሺህ 856 መቶ ተሸከርካሪዎች በማስተናገድ በአጠቃላይ ብር 124 ሚሊየን 578 ሺህ 594 መቶ ብር መሰብሰብ መቻሉ ተሰምቷል።
.
.
#አለን_ኢትዮጵያ የበጎ-አድራጎት ድርጀት የሰው ልጆች የለውጥ ማዕከል ህጋዊ እውቅና በማግኘት ትላንት በ19/05/01 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በይፋ ሥራ ጀምሯል።
.
.
በአንድ ፒካፕ ተሽከርካሪ ላይ በተደረገ ፍተሻ ከባህርዳር ወደ አዲስ አበባ ሲጓጓዙ የነበረ ሦስት መትረየስ፣ 1924 የስታር እና 1856 የማካሮቭ ሽጉጥ ጥይቶች ከ37 የጥይት መያዥ ጋር #መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
.
.
የጀርመኑ ግዙፍ የመኪና አምራች ኩባንያ ቮልስዋገን ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
.
.
የሚድሮክ ግሩፕ የሼክ ሙሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲንን ከእስር #መፈታትን ምክንያት በማድረግ ሠራተኞቹን #አንበሻብሿል
.
.
ከፍተኛው ፍርድ ቤት ለሙስና ተጠርጣሪው የጄኔራል ክንፈ ዳኘው ወንድም #ኢሳያስ_ዳኘው ፈቅዶት የነበረውን የዋስትና መብት ዛሬ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንደሻረው ካፒታል ዘግቧል፡፡
.
.
ጠ/ሚር ዶክተር #ዐቢይ_አሕመድ ዛሬ ምሽት #በብሄራዊ_ቴአትር በየሶስት ወሩ የሚካሄደውን የኪነ ጥበብና የባህል ምሽት ተካፍለዋል።
.
.
ሚድሮክ ኢትዮጵያ የሼክ ሞሃመድ አላሙዲን መፈታት አስመልክቶ፦ የሚድሮክ ንብረት በሆነው #ዩኒቲ_ዩኒቨርስቲ የሚማሩ ተማሪዎች ላንድ ወሰነ ትምህርት(1 ሴሚስተር) #በነጻ እንዲማሩ ፈቅዶላቸዋል፡፡
.
.
ምንጭ፦ ዋልታ፣ ፋና፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ ዋዜማ ሬድዮ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
.
.
ሰላም እደሩ!!
የነገ ሰው ይበለን!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia