TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.5K photos
1.41K videos
203 files
3.84K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የአዲስ_አበባ_ሞተረኞች...

የሞተር ብስክሌት #እገዳው በኑሯቸው ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን–የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች ተናግረዋል።

ተጨማሪ የንብቡ👇
https://telegra.ph/Mot-07-09-2
#እገዳው_ተነስቷል !

ለትንሳኤ በዓል ወደ እስራኤል በሚሄዱ ኢትዮጵያዊያን ላይ ተጥሎ የነበረው የቡድን ጉዞ እገዳ መነሳቱ ተገልጿል።

የእስራኤል የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ለሚመጡ ጎብኚዎች የቡድን ቪዛ እገዳ ጥሎ ነበር።

ሚኒስቴሩ ውሳኔውን አሳልፎ የነበረው በኢትዮጵያ ያለው የእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት ተጓዦች ወደ እስራኤል ከመጡ አይመለሱም በሚል ስጋት ነበር።

በተላለፈው ውሳኔው ላይ ቅሬታ የተሰማቸው የተለያዩ አካላት በተለይ በእየሩሳሌም የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ገዳም አባቶች ባቀረቡት አቤቱታ መሠረት፣ በእስራኤል የኢፌዴሪ ኤምባሲ ከእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ከእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፣ ከሕዝብና ኢሚግሬሽን ጉዳይ የሥራ ኃላፊዎች እና ከሌሎችም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ከተለያዩ አካላት ጋር በተደረገው ተደጋጋሚ ምክክር ውሳኔው የሁለቱን አገራት ወዳጅነት አንጻር ተገቢ አለመሆኑን አሳውቋል።

በመቀጠልም ፤ የእስራኤል የፓርላማ አባል የሆኑት ጋዲ ይባርከን ጋር በመሆን ከእስራኤል ከሕዝብና ኢሚግሬሽን ባለስልጣን ኃላፊዎች ጋር በተደረገው ውይይት ተጥሎ የነበረው የጉዞ ገደብ የተነሳ መሆኑን በእስራኤል ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#እገዳው_ተነስቷል !

ሳዑዲ አረቢያ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሳቢያ ወደ ኢትዮጵያ፣ ቱርክ፣ ቬትናም እና ህንድ በሚደረጉ ጉዞዎች ላይ ጥላ የነበረውን ጊዜያዊ እገዳ ዛሬ ማንሳቷን ከሃገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘን መረጃ ዋቢ አድርጎ Saudi Gazette ዘግቧል።

ሀገሪቱ በዓለም አቀፉ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሳቢያ ዜጎቿ ወደተለያዩ የውጭ ሀገራት እንዳይጓዙ እገዳ ጥላ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia