TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
55K photos
1.37K videos
199 files
3.67K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Sidama

" #አፊኒ " የተሰኘውና በሲዳማ ባህላዊ የእርቅ ስነስርአትና የግጭት አፈታት ላይ ትኩረቱን አድርጎ የተሰራው ፊልም ትላንት በሀዋሳ ከተማ ተመርቋል።

ፊልሙ የሲዳማ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞን ጨምሮ በርካታ ባለስልጣናት የሀገር ሽማግሌዎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች በተገኙበት ነው የተመረቀው።

የፊልሙ ባለቤትና ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ኃላፊነቱን ወስዶ ሲሰራዉ የነበረው የሲዳማ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ነው ተብሏል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ጃጎ አገኘሁ ፤ " አፊኒ ፊልም የሲዳማን ባህል ወግና ትውፊት የሚያንጸባርቅ ተንቀሳቃሽ ሙዚየም ነው " ብለውታል።

" አፊኒ " ፊልም የሲዳማን ባህል የማስተዋወቅ ዓላማ ያለዉና በኢንተርናሽናል ስታንዳርድ የተሰራ መሆኑ ከዚህ ቀደም መገለፁ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቀናት በፊት " አፊኒ " ፊልም ከ7.5 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ መሰራቱን መግለጹን ተከትሎ ከፊልሙ አሰሪ ኮሚቴ " ትክክል አይደለም !! " የሚል ቅሬታ ቀርቦ ነበር።

ይሁንና ትክክለኛ የፊልሙ ወጭ ስንት እንደሆነና ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በተጨማሪ ፊልሙን በገንዘብ ስላገዙ አካላት መረጃ ለማግኘት በተደጋጋሚ ያደረግነው ሙከራ ሊሳካ አልቻለም።

ሌላው ከምርቃት ስርዓቱ ጋር በተያያዘ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ወጥቷል እየተባለ ስለሚነገረው በሚሊዮን የሚቆጠር የገንዘብ መጠን ምላሽ ለማግኘት ጥረት ብናደርግም ለጊዜው አልተሳካም።

በቀጣይ ከሚመለከተው አካል መረጃ የምናገኝ ከሆነ እናቀርባለን።

መረጃው በሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
#አፊኒ #ሲዳማ

በሲዳማ በህዝብ ዘንድ ቁጣ ፈጥሯል የተባለው መፅሀፍ ጉዳይ ምንድነው ?

ከሰሞኑ በዶ/ር አራርሶ ገረመዉ የተጻፈ " አፊኒ " የተሰኘ መጽሀፍ በአእምሮአዊ ንብረት ባለስልጣን ተመዝግቦ የባለቤትነት ፈቃድ ማግኘቱን ተከትሎ በሲዳማ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በኩል ጥያቄ ተነስቷል።

ቢሮው ለአእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን በላከው የቅሬታ ደብዳቤ " ለዶክተር አራርሶ ገረመዉ ' አፊኒ ' በሚል ስያሜ የተሰጠው የባለቤትነት እዉቅና በህዝቡ ዘንድ ቅሬታ ፈጥሯል " በማለት ገልጿል።

የተሰጠዉ እውቅና " የባለቤት " የሚል ሀሳብ የያዘ ሲሆን ይህም የድርሰት ስራ በመሆኑ የቅጅና ተዛማጅ መሆን እንደሚገባዉና " የፈጠራው ባለቤት " የሚለው ቃልም አግባብ አይደለም በማለት ገልጿል።

በመሆኑም ' አፊኒ ' የመላዉ የሲዳማ ህዝብ እንጅ የደራሲዉ የዶ/ር አራርሶ ገረመዉ የፈጠራ ንብረት አለመሆኑ ታዉቆ ማስተካከያ እንዲደረግ በማለት ማብራሪያና ማስተካከያ ጠይቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ጉዳዩን ሰምቶ የመጽሀፉን ደራሲ አነጋግሯል።

ዶ/ር አራርሶ ገረመው ፤ የተፈጠረዉ ሁኔታ ከርሳቸዉ ቀድሞ ሶሻል ሚዲያዉን ማጥለቅለቁን ገልጸዋል ፤ " በዚህም አዝኛለሁ " ብለዋል።

ሁኔታውን በንግግር እንደፈቱት ገልጸው ጥያቄውን ሰላማዊ በሆነ መልኩ ለመመለስና ማህበረሰቡን ለማስቀደም በማሰብ ' አፊኒ ' የሚለዉ ርእስ እንዲስተካከል በመወሰን ስራ መጀመራቸውን አስረድተዋል።

' አፊኒ ' የሚለው ርዕስ ተቆርጦ የወጣ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር አራርሶ ፥ አሁን ላይ መጽሀፉ ላይ ያለው ሙሉ አርእስት ' አፊኒ የሲዳማ ድንቅ ባህል ታላቅ ተቋም አስደማሚ የሰላም እሴት ' በሚል ለማስተካከል በደብዳቤ የአእምሯዊ ንብረት ባለስልጣንን መጠየቃቸውን ባለስልጣኑም እንደተቀበላቸውና ማስተካከያ እንደተደረገበት ገልጸዋል።

" ይህንን መጽሐፍ የጻፍኩት #የህዝቤን_ታሪክ ለማስተዋወቅ እና ለማጉላት መሆኑን በውስጡ ያሰፈርኩት አሳብ ይመሰክራል " ያሉት ደራሲው " በርዕሱ ምክኒያት የተፈጠረውን ቅራኔ በቀላሉ ከፈቃድ ሰጪው ጋር ተነጋግሮ መፍታት የሚቻል ቢሆንም በማህበራዊ ሚድያ የጥቂቶች ሀሳብ በዚህ ደረጃ መንጸባረቁ አስገርሞኛል " ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia