TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#እንኳን_አደረሳችሁ

የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት እሁድ የሚከበረውን 1440ኛው የኢድ አል አድሃ (#አረፋ) በዓልን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሰይድ መሐመድ ኡመር 1440ኛው ሂጂራ የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ሲከበር የተቸገሩትን በመርዳት እና ለሀገር ሰላም ፀሎት በማድረግ መሆን እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

ሙስሊሙ ማኅብረተሰብ አቅም የሌላቸው እና የተቸገሩ የኃይማኖቱ ተከታዮች በአሉን ተደስተው እንዲያከብሩ የማድረግ ኃማኖታዊና ማኅበራዊ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ነው ፕሬዝዳንቱ ያስገነዘቡት፡፡

የእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች በሀገሪቱም ሆነ በአማራ ክልል በተከሰተው አለመረጋጋት ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና ወደ ቀድሞው ህይወታቸው እንዲመለሱ በመርዳት በዓሉን እንዲያከብሩም ሺህ ሰኢድ መሃመድ ኡመር ጠይቀዋል፡፡

ምእመኑ በዓሉን ከሌሎች የኃይማኖት ተከታይ ወገኖቻቸው ጋር በማክበር ለዘመናት የዘለቀውን የአብሮነትና የመተሳሰብ እሴት ማጎልበት ላይ እንዲያተኩሩም ነው ያሳሰቡት፡፡ በዓሉ በባሕር ዳር አለም አቀፍ ስታዬም የሚከበር ይሆናል፡፡ የባሕር ዳር ከተማ ከንቲባን ጨምሮ ሌሎች ተጋባዥ እንግዶችም በሥፍራው ተገኝተው መልዕክት እንደሚያስተላልፉ ይጠበቃል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አረፋ

1440ኛው የኢድ-አል-አድሐ (አረፋ) በዓል በቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች እየተከበረ ይገኛል። በክልሉ የአረፋ ሶላት ሥነ-ሥርዓት በመንጌ ወረዳ በፎቶ ይህንን ይመስላል፡፡

ፎቶ፡- ከቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አረፋ

1440ኛው የኢድ-አል-አድሐ (አረፋ) በዓል በጅማ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

ፎቶ፡- TIKVAH-ETH Family
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አረፋ

(Tikvah 🕌 Family)

የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል እየተከበረ ይገኛል።

በዓሉ በሀገራችን #ኢትዮጵያ እንዲሁም በተለያዩ ሀገራት ነው የተከበረ የሚገኘው።

በዚሁ አጋጣሚ የእስልምና ተከታይ ቤተሰቦቻችን እንኳን ለበዓሉ አደረሳችሁ ፤ አደረሰን እያልን በዓሉን ስናከብር በፀጥታ ችግር ፣ በጦርነት ፣ በሰላም እጦት የሚወዱትን የተነጠቁ ፣ በሀዘን ውስጥ ሆነው በዓሉን የተቀበሉትን ወገኖቻችን እያሰብን እንዲሆን አደራ እንላለን።

በተጨማሪ እንደሁል ጊዜው በዓሉን ካጡት ጋር ተካፍለን፣ የታመሙትን በመዘየር ፣ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም እና ደህንነት ፣ ህዝባችንም ከሰቆቃ፣ ከችግር ያርፍ ዘንድ ፈጣሪያችንን እየተማፀንን እንድናከብረው አደራ እንላለን።

በድጋሚ በዓሉ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ እንዲሁም የአንድነት ይሆን ዘንድ እንመኛለን!!

በኢትዮጵያና በተለያዩ ሀገራት የበዓሉን ድባብ የሚያሳዩ ፎቶዎችን በዚህ ማግኘት ትችላላችሁ 👇
https://t.me/+Rx7P5YHQp_G16wyX

@tikvahethiopia
#አረፋ

(Tikvah 🕌 Family)

የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል እየተከበረ ይገኛል።

በዓሉ በሀገራችን #ኢትዮጵያ እንዲሁም በተለያዩ ሀገራት ነው የተከበረ የሚገኘው።

የእስልምና ተከታይ ቤተሰቦቻችን እንኳን ለበዓሉ አደረሳችሁ ፤ አደረሰን ለማለት እንወዳለን።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ እንመኛለን።

ተጨማሪ ፎቶዎችን በ @tikvahethmagazine ላይ ይመልከቱ።

@tikvahethiopia
#አረፋ

መልካም በዓል !

" ይህን የተባረከ #የአረፋ_ቀን እምነታችንን በልባችንና በተግባራችን የምናድስበት ፤ ስላጠፋነው ጥፋት / ስህተት ከልብ አዝነን ዳግመኛ ወደዛ ላለመመለስ ቃል የምንገባበት እና ወደ ሁሉን ቻይ አምላካችን #አሏህ 🤲 የምንቀርብበት ቀን ነው። " - ሙፍቲ ኢስማኤል ሜንክ (ዶ/ር)

#መልካም_በዓል !!
#TikvahFamily ❤️

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ኢትዮጵያ

የ2016 የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ይገኛል።

ጥዋት የኢድ ሶላት ስነስርዓት በተለያዩ ከተሞች ተከናውኗል።

ከኢድ ሶላት በኃላ ምዕመኑን በየቤቱ ፣ ከዘመድ አዝማዱ፣ ከወዳጆቹ ጋር በመሆን በዓሉን እያከበረ ነው።

#ኢድአልአድሃ #አረፋ

መልካም በዓል

ፎቶ ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ

@tikvahethiopia