TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.6K photos
1.39K videos
200 files
3.74K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ነፃ_የትምህርት_ዕድል

ጠብታ ፓራሜዲክ ኮሌጅ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በግል ከፍለው መማር ለሚቸገሩና የመግቢያ መስፈርቱን ለሚያሟሉ የኢመርጀርሲ ሜዲካል ቴክኒሽያን ባለሙያ ደረጃ 4 ውስን ሰልጣኞችን ተቀብሎ የነጻ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማመቻቸቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በላከው መልዕክት አሳውቋል።

የመግቢያ መስፈርቶች ፦

1. ከ2011 - 2013 ባለው የትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁና ውጤታቸው ለወንዶች ከ293 በላይ ለሴቶች ከ278 በላይ  ያመጡ፡፡

2. የ2014 ዓ.ም (በ2015 ዓ.ም ) ፈተና ለወሰዱ
ሀ.ለተፈጥሮ ሳይንስ  ተማሪዎች ለወንዶች ከ158 በላይ ለሴቶች ከ157 በላይ፤

ለ. ለሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች ለወንዶች 149 በላይ ለሴቶች ከ145 በላይ ውጤት ያለቸው

3. ዕድሜ ከ30 ዓመት ያልበለጠ/ያልበለጠች፡፡

4. የኮሌጁን መግቢያ ፈተና  ማለፍ  የሚችል/የምትችል፡፡

5. ከፍለው ለመማር  የማይችሉ  መሆኑን   የሚገልጽ  ከሚኖሩበት ቀበሌ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡

6. ለሴት ተወዳዳሪዎች ቅድሚያ ይሰጣል

7. ስልጠናውን ለ20 ወራት በመደበኛ ፕሮግራም የሚሰጥ በመሆኑ ሙሉ ጊዜውን ለስልጠናው ለመጠቀም ፈቃደኛ የሆነ/የሆነች፡፡

የምዝገባ ጊዜ ከየካቲት 27 - መጋቢት  2/2015 ዓ.ም ድረስ ከላይ መስፈርቱን በሟሟላት በጠብታ ፓራሜዲክ ኮሌጅ በመገኘት መመዝገብ ትችላላችሁ። ( 👉 አድራሻውን ለማግኘት እዚህ ይጫኑ)

ለምዝገባ ሲመጡ 4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣ ትራንስክሪፕት፤ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡

ለበለጠ መረጃ  በ8035 ወይም 0943302400 /0923514151 በስራ ሰዓት መደወል ይቻላሉ።

@tikvahethiopia
#ነፃ_የትምህርት_ዕድል

LG-KOICA Hope የቴክኒክና ሞያ ኮሌጅ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በግል ከፍለው መማር ለሚቸገሩ የመግቢያ መስፈርቱን ለሚያሟሉ ተማሪዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን #በነጻ ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል።

ኮሌጁ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በላከው መልዕክት በዚህ ዙር እስከ 150 ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር መዘጋጀቱን ገልጾ የሀገር ዉስጥና የዉጭ ሀገር የሥራ ዕድል አማራጮችም እንዳሉት ጠቅሷል።

ከዚህ በተጨማሪ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸውና መስፈርቱን አሟልተው ለሚመረጡ የተመረጡ ተማሪዎች የምግብ፣ የትራንስፖርት እና ሌሎች ወጪዎችን እንደሚሸፍን ገልጿል።

ተጨማሪ ይመልከቱ : https://t.me/tikvahethmagazine/18949

@tikvahethiopia