TIKVAH-ETHIOPIA
1.38M subscribers
54.5K photos
1.35K videos
197 files
3.61K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ህወሃት⬇️

ህወሓት በቀጣይ ግንባሩን የሚመሩ ድርጅቱን #ስራ_አስፈፃሚ አባላት መረጠ፡፡

በዚህም መሰረት፦

1. ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል-ሊቀመንበር
2. ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/እግዚያብሄር- ም/ ሊቀመንበር
3. አቶ ጌታቸው ረዳ
4. አቶ አለም ገብረዋህድ
5. አቶ አስመለሽ ወልደስላሴ
6. ዶ/ር አብርሃም ተከስተ
7. ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም
8. አቶ ጌታቸው አሰፋ
9. ዶ/ር አዲስ አለምባሌማ በቀጥታ በኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ አባላነት ህወሓትን የሚወከሉ ሲሆን፣
10. አቶ በየነ ምክሩ እና
11. ዶ/ር አክሊሉ ኃይለሚካኤልን ጨምሮ አስራ አንዱ አባላት ህወሓትን በስራ አስፈፃሚነት የሚያገለግሉ መሆናቸው ተዘግቧል።

ግንባሩ ዛሬ ባካሄደው ምርጫም 55 አባላት ያሉት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ ተካሂዷል፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአራዳ ~ ወረዳ 5 ወጣቶች🔝

አራዳ ወረዳ 5 የሚገኙ #ወጣቶች "በቂ ማስረጃ እጃችን ላይ እያለ፤ ሁሉን ነገር ጨርሰን የድጋፍ ደብዳቤ ተፅፎልን (ኮንቴነር ይሰራ የሚል)፣ ውል ተዋውለን፤ የቲን ቁጥር አውጥተን #ስራ_ከጀመርን በኃላ #አፍርሱ ብለውናል።" ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል። የሚመለከተው አካል ጉዳዩን በትኩረት ተመልክቶ መፍትሄ ይስጠን ሲሉም ጠይቀዋል።

•ጉዳዩ የሚመለለተው አካል ምልሻ መስጠት ከፈለገ +251919743630 ወይም @tsegabwolde መጠቀም ይችላል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸በ2012 ዓ/ም #ስራ የሚጀምረው አዲሱ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ኲሓ የሚገኘው መለስ ካምፓስ #MekUniETH

TIKVAH ETH MAGAZINE የዩኒቨርሲቲ ጥሪዎችን ብቻ በዚህ ተከታተሉ👇
https://t.me/joinchat/AAAAAEcez-UrldBjOpa-qQ
#ፀሀይ_ባንክ

ፀሀይ ባንክ ቅዳሜ ሀምሌ 16/2014 በይፋ ስራውን እንደሚጀምር ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

ባንኩ በ2.9 ቢሊዮን የተፈረመ ካፒታልና በ734 ሚሊዮን በስራ ላይ የዋለ ካፒታል የተቋቋመ ሲሆን ዝቅተኛ የአክሲዮን ግዢውን ብር 100 ሺህ በማድረግ በ373 ባለአክሲዮኖች የባንክ ኢንዱስትሪውን ተቀላቅሏል፡፡

ምን ይዞ መጥቷል ?

👉 የባንኩ ዓላማ የባንክ ኢንዱስትሪውን
መቀላቀል ብቻ ሳይሆን ፤ በፋይናንስ ዘርፉ በቂ ትኩረት ያላገኙትን የጥቃቅንና አነስቸኛ ፤ ግብርናውን ዘርፍ ፤ የአምራች ኢንዱስትሪውን እንዲሁም አዋጪ ለሆኑ #የፈጠራ_ስራዎች እና #ስራ_ፈጣሪዎች ተደራሽ መሆንና ለሁሉም የሆነ ባንክ ሆኖ አዳዲስ ስልቶችን በመንደፍ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታግዞ ቀልጣፋና ደንበኛ ተኮር የሆነ አገልግሎት ለመሥጠት መሆኑን አሳውቋል።

👉 የባንክ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን በማዘን ዘመኑን የዋጀ መደበኛውን የባንክ አገልግሎት እና ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎትን በማቅረብ በኢንዱስትሪው ውስጥ ተወዳዳሪ ብቻ ሳይሆን፤ የተሻለ የባክ አገልግሎት ይዞ በመግባት ለሁሉ የሚያገለግል ባንክ እንደሚሆን ገልጿል።

👉 ስራ ሲጀምር ከሕብረተሰቡ የሚሰበሰበውን ከፍተኛ ሆነ ሃብት መልሶ የሕብረተሰቡን ህይወት ለሚያሻሻልና ልማቱን ሊያፋጥን ለሚችሉ ስራዎች እንዲውል ትኩረት ሰጥቶ እደሚሰራ ገልጿል።

👉 በባንኩ የምረቃ ዕለት በ30 ቅርንጫፎች በመጀመርና በቅርብ ቀን የቅርጫፎቹን ቁጥር ከ50 በላይ እንደሚያሳድግ የገለፀ ሲሆን በአንድ ዓመት ውስጥ 100 ቅርንጫፎችን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ለክፈት የሚያስችለውን ስራ እየሰራ መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ

1. አጭበርባሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ የእቃ ጭነት አገልግሎት (ካርጎ) በኩል ለተለያዩ ግለሰቦች ዕቃ እንደተላከላቸው አስመስሎ በመደወል እና ሐሰተኛ የእቃ ጭነት መለያ ቁጥር Air Waybill (AWB) በመጠቀም የተላከውን ዕቃ ለመቀበል የሚከፈል በሚል ክፍያ በመጠየቅ የማጭበርበርና የማታለል ስራ እየሰሩ ስለሆነ ጥንቃቄ ይደረግ።

2. አጭበርባሪዎች #ስራ_ፈላጊዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመቀጠር ለምዝገባ እና ለተለያዩ ወጪዎች በሚል ገንዘብ በማስከፈል የማታለል ተግባር ላይ በመሰማራታቸው አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።

3. የካናዳ መንግስት የስራ እና የትምህርት እድል እንዳወጣ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ሰው እንደወከለ እንዲሁም መመዝገብ ለሚፈልጉም ሁሉ ክፍያ የሚፈፅሙበት የባንክ አካውንትም አንዳሳወቀ በማስመሰል ደብዳቤ በማዘጋጀት ሰዎችን የማታለል ተግባር ላይ አጭበርባሪዎች በመሰማራታቸው ተገቢው ጥንቃቄ ይደረግ።

እንድታውቁት ፦

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዕቃ ለተላከላቸው ደንበኞቹ ዕቃቸው መድረሱን እና ወደ ድርጅቱ በመምጣት አስፈላጊ ሂደቶችን እንዲያስጀምሩ ከማሳወቅ ውጪ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ እንዲከፍሉ በስልክ አይጠይቅም።

ለስራ ቅጥር በሚል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ አይጠይቅም ፤ ከማንኛውም አይነት ኤጀንት ጋር አብሮ አይሰራም ፤ ለስራም ሆነ ለትምህርት ወደ የትኛውም ሀገር ሰዎችን የመላክ ስራ ላይ አልተሰማራም።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
#ስራ #ደመወዝ

° " ያለስራና ደመወዝ በመቆየታችን ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀናል " - የመንግስት ሰራተኞች

° " ጉዳዩን እናውቀዋለን እየተወያየንበት ነው ፥ በአጭር ቀናት መፍትሄ ይሰጣቸዋል " - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለስልጣን

የደቡብ ክልል መበተኑን ተከትሎ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተመደቡ የ " ውሀ ስራዎች ኮንስትራክሽን ሰራተኞች " ከስራ እና ከደመወዝ ውጭ ሆነው ወራት እንደተቆጠሩ ገልጸዋል።

ሰራተኞቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባቀረቡት ቅሬታ ፥ ክልሉ ከፈረሰ በኋላ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቢመደቡም እስካሁን ስራ አለመጀመራቸውን በዚህም ለችግር መጋለጣቸውን ተናግረዋል።

ከ2 ወር በፊት ዘግይቶ በተሰጣቸው ደብዳቤ ሆሳዕና ከተማ መመደባቸው እንደተነገራቸው ጠቁመዋል።

ቦታው ላይ ተገኝተው ሪፖርት በማድረግ ደመወዝ እና ጥቅማጥቅም እንደሚሰጣቸውም ተገልጾላቸው ነበር።

በዚህም ግማሽ ሰራተኞች እቃቸውን በገንዘብ እጥረት ሽጠው እንዲሁም ቀሪውን በሌለ ገንዘብ ትራንስፖርት ከፍለው ቦታው ቢደርሱም አንድም የሚያስተናግዳቸው ሆነ የሚቀበላቸዉ አካል ማጣታቸውን አስረድተዋል።

በመሆኑም ያለደሞዝና ስራ በተመደቡበት ከተማ ለ2 ወራት መቆየታቸው ህይወትን ከባድ እንዳደረገባቸዉ ገልጸዋል።

በገንዘብ እጦት የምግብ መግዣ እንኳ እንስከማጣት መድረሳቸውን ከዚህም በላይ በቤት ኪራይ ችግር አብዛኛዉ ሰራተኛ ጎዳና ለመውጣት ጫፍ መድረሱን ተናግረዋል።

" ሆሳዕና የሚገኘው አዲሱ ቢሮ ስንሄድ #ጸሀፊ_ብቻ ነው የምናገኘው " የሚሉት ሰራተኞቹ " የሚመለከተው አካል ሌላዉ ቢቀር ጥያቄያችን ሊያደምጥ ይገባል " ሲሉ ቅሬታቸው ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰራተኞቹን ጥያቄ ይዞ ያናገራቸዉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አማካሪ እና ልዩ ረዳት የሆኑትን አቶ ንጉሴ አስረስ ፥ ጉዳዩን እንደሚያውቁት በመግለጽ ችግሩ በቅርብ እንደሚፈታ ተናግረዋል።

ከሰሞኑ ሰራተኞችን በአካል አግኝተዋቸው ለማነጋገር እቅድ እንዳላቸውም የገለጹት አቶ ዘሪሁን " ለሁለት መቶ አስር ሰራተኞች ደሞዝ መክፈል ለክልሉ ቀላል ነው " ብለዋል።

በቅርቡ ችግሩ ላይ የተወሰዱ እርምጃዎች እንዲሁም ሌሎችም ተጨማሪ ጥያቄዎች ካሉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሊያነጋግራቸው እንደሚችል ቃል ገብተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
#CentralEthiopiaRegion

@tikvahethiopia
#ደመወዝ

° " ደመወዝ በአግባቡ #እየተከፈለን_አይደለም ፤ የሚመለከተዉ አካል ካላናገረን ማስተማር አንችልም " - የከምባ ወረዳ መምህራን

° " በየሶሻል ሚዲያ ' ደመወዝ አልተከፈለንም ' እያሉ ገጽታችንን የሚያበላሹትን በህግ እንጠይቃለን " - የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሀላፊ

° " ያልተከፈላቸው መምህራን
#ስራ_ስለማቆማቸው መረጃ አለኝ " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር

ከሰሞኑ በጋሞ ዞን ከምባ ወረዳ መምህራን " ደሞዝ በአግባቡ እየተከፈለን አይደለም " በማለት ቅሬታቸዉን አሰምተዋል።

" ዞኑ ውስጥ ካሉት ሀያ ክላስተሮች ተለይተን ደመወዝ አልተከፈለንም " ያሉ መምህራን ስራ ማቆማቸውንና የሚመለከተው አካል ካላናገራቸው ስራ እንደማይገቡ በመግለጽ ቅሬታቸዉን አቅርበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ይህንን የመምህራን ጉዳይ ሰምቶ ይመለከታቸው ያላቸውን አካላት ማለትም ፥ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበርና የዞኑን ትምህርት መምሪያ አነጋግሯል።

የክልሉ መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አማኑኤል ጳዉሎስ ምን አሉ ?

አቶ አማኑኤል ፥ " በዞኑ በከምባ ወረዳ #ለመምህራን እየተከፈለ ያለው ደሞዝ የተቆራረጠና አግባብ ባልሆነ መልኩ እየተፈጸመ ነው " ብለዋል።

አክለውም ፤ " በክላስተር ተቆራርጦ ከመክፈሉ ባለፈ በአንድ ትምህርት ቤት እንኳን ለጥቂት መምህራን ተከፍሎ ለአብዛኛው ደግሞ አለመከፈሉ ያበሳጫቸው መምህራን ስራ አለመግባታቸውን ተከትሎ ትምህርት ቤቶች ስለመዘጋታቸው መረጃ አለን " ብለዋል።

የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊው አቶ አብርሀም አምሳሉ ምን አሉ ?

አቶ አብርሀም ፤ " ያለኝ መረጃ ለመምህራን ደመወዝ በአግባቡ እየተከፈላቸው መሆኑን እና ስራም እየተሰራ መሆኑን ነው " ብለዋል።

" ይሁንና በየሶሻል ሚዲያው ላይ የአካባቢውን ገጽታ ለማጠልሸት በማሰብ ' ደመወዝ አልተከፈለንም ' እያሉ የሚንቀሳቀሱ አካላት ወሬውን እያናፈሱት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" እነዚህ አካላት በህግ እየተጠየቁ ሲሆን ወደፊትም ይጠየቃሉ " ብለዋል።

ምን አልባት ያልተከፈላቸዉ መምህራን ካሉ የዲስፕሊን እና መሰል ችግር ያለባቸው ሊሆኑ ይችላሉ ሲሉ አክለዋል።

በተጨማሪም በአካባቢው ላይ ትምህርት መቋረጡን የሚመለከት መረጃ እንደሌላቸዉ በመግለጽ ችግር ተከስቶ ከሆነ እንደሚስተካከል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia