TIKVAH-ETHIOPIA
1.41M subscribers
55K photos
1.37K videos
199 files
3.67K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው‼️

#ሀላባ

#የፕሮቴስታንት እምነት ቤተክርስትያን ላይ በዛሬው ዕለት የተቃጣው ጥቃት ፍፁም የሀላባን ሕዝብና የየትኛውንም ኃይማኖቶችን #እንደማይወክል የሀላባ ዞን አስተዳዳሪ ገልፁ፡፡

ተግባሩ #የጥቂት ግለሰቦችን የግል ፍላጎት ከሟሟላት ጋር ተያይዞ የተፈፀመና ሁሉንም ኃይማኖቶች የማይወክል ሲሆን በድርጊቱ የተሳተፉና የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቀጣይ ጊዜያት ለሕግ የማቅረቡ ሥራም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የተጠረጠሩ ግለሰቦችም ተይዘው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም የደረሰውን ማንኛውንም ጉዳት በዞኑ አስተዳደር እና ለዞኑ ብቻ ሳይሆን ለአካባቢው ሕብረተሰብ ጭምር ከጎኑ በሚሆነው የሀላባ ሕብረተሰብ ድጋፍ እንደሚተካም አስተዳዳሪዋ ገልፀዋል፡፡

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሀላባ ዞን ደኢህዴን ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሂዲን ሁሴንም ለኃይማኖት ተቋማት እና በሠላሟ ለምትታወቀው ሀላባ ሁሉም አካል ዘብ ሊቆም እንደሚገባ አሳስበው በዛሬው የፕሮቴስታንት እምነት ተቋማት ላይ የደረሰውን ጥቃት በፅኑ #አውግዘዋል፡፡

ጥቃት የደረሰባቸውን የኃይማኖት ተቋማት የሀላባ ዞን አስተዳዳሪ ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን፣ የሀላባ ዞን ደኢህዴን ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሂዲን ሁሴን፣ የሀላባ ዞን ደኢህዴን ቅ/ጽ/ቤት የከተማ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አቶ አ/ባሲጥ አባኮ፣ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ደኢህዴን ን/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀሩና አህመድ እና የሀላባ ዞን፣ የወረዳና የከተማ መካከለኛ አመራሮች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ ጥቃቱ የደረሰባቸውን የኃይማኖት ተቋማት በቦታው ተገኝተው በመመልከት ደርጊቱንና የድርጊቱን ፈፃሚዎች በፅኑ አውግዘው የፕሮቴስታንት ኃይማኖት ተከታዮችን #አፅናንተዋል

ማንኛውም አካል በኃይማኖት ሽፋን ለሚያደርሰው ጥቃት ከተጠያቂነት እንደማያመልጥና የየትኛውም ኃይማኖት ለዚህ ተግባር ሽፋን እንደማይሰጥ አውቆ ከዚህ እኩይ ተግባር እንዲቆጠብ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ደኢህዴን ን/ቅ/ጽ/ቤት አሳስቧል፡፡

Via HK sub Branch office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DrLiaTadesse በኢትዮጵያ ተጨማሪ 2 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል! ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 912 ላቦራቶሪ ምርመራ 2 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያቸው ተረጋግጧል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 133 ደርሷል። የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦ ታማሚ 1 - የ25 ዓመት ኢትዮጵያዊ #ከኬንያ የተመለሰና #በሞያሌ አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ። ታማሚ 2…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በደቡብ ክልል ሀላባ ዞን በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] መያዙ ስለተረጋገጠው የ25 ዓመት ወጣት ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አጥናው ካውዛ ፦

- በደቡብ ክልል በኮሮና ቫይረስ መያዙ የተረጋገጠው ወጣት በዛሬው ዕለት በጤና ሚኒስቴር መገለጫ የተገለፀው ሁለተኛው ታማሚ ነው።

- ወደ ሱማሌ ክልል ናሙና ተልኮ ምርመራ ተደርጎ የናሙናው ውጤት ሳይጠናቀቅ ሰዎቹ ከሞያሌ ወደ ደቡብ ክልል እንዲንቀሳቀሱ ነው የተደረገው።

- ቫይረሱ እንዳለበት የተረጋገጠው የ25 ዓመት ወጣት የከምባታ ጠምባሮ ዞን ነዋሪ ነው፤ ከኬንያ ነው የተመለሰው፤ ወጣቱ ትላንት ለሊት ወደ 11:30 #ሀዋሳ ገብቶ ነበር። 11:45 በሌላ መኪና ወደ ሀላባ ሄዷል፤ በኃላም በጤና ሚኒስቴር ሪፖርት ክትትል ተደርጎበት #ሀላባ ላይ ተይዟል።

- ከወጣቱ ጋር ወደ ሀላባ በአንድ መኪና የሄዱ ሰዎች በሙሉ ተለይተው ተይዘዋል። ሌሎች ከእሱ ጋር አብረውት ከሞያሌ የመጡም የተወሰኑ ሰዎች ተለይተው ተይዘዋል። አሁንም ቀሪ የማጣራት ስራዎች እየተሰሩ ነው።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#ሀላባ

- " ባለቤቴ ከወንድሙና እህቱ ጋር በመሆን ፊቴ እስኪበላሽ ደበደቡኝ " - ተበዳይ

- " እንዲህ አይነቱን የሴት ልጅ ጉዳት አንታገስም " - የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊዉ አቶ ሙደሲር ጉታጎ

በሀላባ ከተማ " ባለቤቴ ከእህትና ወንድሙ ጋር በመሆን አደጋ አድርሶብኛል " ያለች ተበዳይ የህግ ድጋፍ ስጡኝ ስትል በማህበራዊ ሚዲያ ጥያቄ አቅርባለች።

ጉዳዩን የተመለከተው የሀዋሳ የቲኪቫህ ቤተሰብ አባል ባደረገዉ ማጣራት ፥ ተጎጅዋ ፊቷ ላይ ጉዳት መደረሱን በተጨማሪ የሷና የመጀመሪያ ልጇ ሰዉነት ትክሻቸዉ አካባቢ ' ጥርስ ንክሻ ' እንደደረሰባቸዉ ለማወቅ ችሏል።

የግል ተበዳዩዋ እናት ለቲክቫ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ ልጃቸዉና የልጅ ልጃቸዉ በደም ተዘፍቀዉ በምሽት ወደቤት እንደመጡና በወቅቱ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገንተው እንደነበር ገልጸዋል።

የግል ተበዳዩዋ ወ/ሮ አበባ ቦረና ፤ " ምንም እንኳን የጋራ አራት ልጆች ቢኖሩንም ካሁን በፊት በመካከላችን በነበረ ግጭት ምክኒያት በፍርድ ቤት ለመለያየት ጫፍ ከደርሰን በኋላ  በሽማግሌ ተመልሰን አንድ ላይ መኖር ከጀመርን 3 ወር አልሆነም " ብላለች።

" ምንም እንኳን ቀን ላይ ቀላል ጭቅጭቅ ውስጥ ብንገባም ከቤተሰቡ ጋር ሆኖ እንዲህ ያደርጋል ብዬ ፍጹም አልጠበኩም " ስትል ተናግራለች።

" በተለይ ተሰብስበዉ ሲደበድቡኝ ለመገላገል የገባዉን የመጀመሪያ ልጃችን ላይ ላይ በዚህ ልክ ይጨክናል ብዬ አላሰብኩም ነበር "  ብላለች።

ጉዳዩን በተመለከተ የጸጥታ አካላት ምን እየሰሩ ነዉ ? በማለት የጠየቅናቸው የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ ሀላፊ አቶ ሙደሲር ጉታጎ ፤ " እንዲህ አይነቱን የሴት ልጅ ጉዳት አንታገስም " ብለዋል።

ጉዳዩን በሰሙ ቅጽበት የከተማው ፖሊስ በፍጥነት ችግር ፈጣሪዎችን  ይዞ እንዲያጣራ ማዘዛቸዉንም ነግረዉናል።

አቶ ሙደሲር  ጉዳዩ ተጣርቶ የሚደረስበትን ውጤት እንደሚያጋሩን ቃል ገብተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia