ኢትዮጵያዊ ወጎች #Ethiopian
1.46K subscribers
314 photos
3 videos
18 files
50 links
Download Telegram
ለመላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከተይ ቤተሠቦቻችን እንኳን አደረሣችሁ
©Fiker_love
#ስርዝ_ድልዝ_ደብዳቤ 🌷

እዚ ደብዳቤ ላይ
💚 ልነግርሽ ያሰብኩት
💛 አስቤ የፃፍኩት
❤️ ፅፌ የሰረዝኩት
ሰርዤ የላኩት
ስርዝ ድልዝ ሆኖ አልነበብ ካለሽ
ሳልሰርዘው በፊት
ምን ይላል መሰለሽ…
መግቢያውም
መደምደምያው ሀተታው በሞላ
ሌላ አይናገርም
ከናፈቅሽኝ እና ካፈቀርኩሽ ሌላ።

@Simetin_Begitim
ቃናዝ(ልዑል ሀይሌ)
.
ነግሬሽ ነበረ...
አልነግርሽም ብዬ፤
እንደማልጠብቅሽ ከመንገድ ተጥዬ፤
እንደማልነሳ ከጣልሽኝ ሜዳ ላይ፤
እንደማልመለስ
እየተንጠራራሁ ሳልነካው ያን ሰማይ፤
እንደማላወራ
እንዳልጠራ ስምሽን ዳግም ተመልሼ፤
ነግሬሽ ነበረ አልነግርሽም ብዬ ቃልሽን አስታውሼ።
.
ነግሬሽ ነበረ...
የምነግርሽን ቃል፤
ብቻ ምን አለፋሽ
አልነግርሽም ያልኩት ብነግርሽ ይበቃል፤
ሌላው ያስተረፍኩት
የማይነገረው ያልነገርኩሽ ነገር፤
እነግርሽ ነበረ
ቀድሜ ባልነግርሽ እንደማልናገር።
.
ግን እነግርሻለሁ!!
የብሶቴን ዳር ዳር የቁጭቴን ጫፉ፤
እንደማላዋይሽ
አዋይቼሻለሁ በግርድፍ ግርድፉ።
.
ነግሬሽ ነበረ...
ዳግመኛ እንደማይሽ ዓይኖቼ ከጠፉ፤
በፅልመቴ ነዪ
በብርሃኔ አትኖሪም ምን ዘመናት ቢያልፉ።
.
ነይ ያኔ!
ነይ ያኔ!
አይሻለሁ ብዬ የገባሁልሽ ቃል፤
በጣልሺኝ ፅልመት ውስጥ
እየሟሟ ያልቃል፤
ስለዚህ ነይ ልየው
ቀና ብዬ ዓይንሽን፤
ያልኩሽን አትዪው አጥፊ ዓይኖችሽን።
.
ነግሬሽ ነበረ....
የማልነግርሽን ቃል፤
ከምነግርሽ ነገር
አልነግርሽም ብዬ ብነግርሽ ይበቃል።
.
ነግሬሽ ነበረ...
አልነግርሽም ብዬ፤
በተከልሽው ጎጆ ባጥር ተንጠልጥዬ፤
ያ ፅልመት ሚመስል ቀኑ እንደሚገፈፍ፤
ሐጢያት፣ዕዳ፣ጦሱ ላንቺ እንደሚተርፍ፤
በአርምሞዬ ቅጣት እንደምትቀጪ፤
ነግሬሽ ነበረ.....
አልነግርሽም ብዬ ከቤቴ ስትወጪ፤
እናም እነግርሻለሁ የስንብቴን ቃል፤
ብቻ ምን አለፋሽ
አልነግርሽም ብዬ ብነግርሽ ይበቃል።
፲፪-፭-፳፻፲፩ ዓ.ም.
@Simetin_Begitim
©ዝንቅ
ደመቀ ሲፀልይ፣ ገዱ እየሰገደ፤
ከአማራ ሰማይ ላይ፣ #በረከት ወረደ፤
የክፋት በረከት መርገምት ከራቀ፣
ገዳችን ውል ይዞ ፍቅራችን ደመቀ።

Credit - ኮማቹ

@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim
😂ለፈገግታ
"ቡና ጠፋ ብለሽ ፣ ስታለቃቅሽ
በጅማ ተገኘ ፣ ያውም በርካሽ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ለሊት ካስቸገረሽ ፣ የቡና ሱስሽ
እኔ እወቅጠዋለሁ ፣ አንቺ ከቆላሽ፡፡

😂😂😂😂😂

@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim
<<በላይ በቀለ ወያ>>
ከነዚህ ውጪ
ነፃ አውጪ
ህዝቡን ጥሎ ፣ ሸሽቶ ነበር ፣ ወደ ውጪ (ኢመኑኝ ርዕስ ነው)

(ታላቁ ሩስያዊ ፈላስፋ በበወቪስኪ እንደፃፈው)
.
.
እውነት ግን እውነት ግን
ነፃ አውጪ ነኝ ብሎ ፣ ወደ ሀገር የመጣው
ድንገት የለማ ቲም ፣ ነፃ ባያወጣው
ምንድን ነበር እጣው?
።።።
ዛሬ እንደልባቸው
ነፃ አውጪ ነን ብለው ፣ ሀገር ሚቀውጡት
ያኔ የት ነበሩ...
ደርግ ጥሎት ሲሔድ ፣ ደርግ ሆነው የመጡት
ህዝቡን እንደጫማ ፣ ሲያስሩና ሲረግጡት?
የድል አጥቢያ አርበኞች ፣
የት ጠፍተው ነው ያኔ ፣ ዛሬ የሚቀብጡት?
ብዬ አልጠይቅም ፣ ምላሹን ሳላጣው
ነፃ አውጪ ነኝ በሚል...
መጨቆን ነውና ፣ የዚህ ህዝብ እጣው
እስከማውቀው ድረስ
ባለሁበት ሀገር
ነፃ አውጪ ብቻ ነው ፣ ነፃ የሚወጣው!
(እኔ ነፃ አውጪ ሳውቅ
የህዝቡን ደም ሳይሆን
እንደ አጤ ቴዎድሮስ ፣ ሽጉጥ ነው ሚጠጣው

@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim
🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐
. . . . በቃኝ . . .

እሳት ሆኘ ስነድ ፥ አንች ቆፈን ወርሶሽ
ሎሚ ብወረውር ፥ እንቧይ ሆኖ ደርሶሽ
ዝምድና ሳያንሰን ፥ እየቆየሽ ባዳ
መላመድ ሳይጎድለን ፥ እያደርሽ እንግዳ ፤

እንግዲህ ደህና ሁኝ !

ምኞቴም በረደ ፥ ቁጣየም አለፈ
ከእድሉ ጋር ታግሎ ፥ ማነው ያሸነፈ።

. . . በእውቀቱ ስዩም

@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim
👆👆👆👆👆👆👆👆👆
መሣጭ ግጥም ናት አዳምጧት
@Simetin_Begitim
# ዕድሌ

ፍቅሬ እንዲገባት
ቃላት...አጋጭቼ
ግጥም በገጠምኩኝ፣
ሰም ያልኩት ሁሉ
ወርቅ እያረገችው
ባያሌው...ታመምኩኝ!!

# ሀብታሙ_ወዳጅ

@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#ሠላም_ይስጠን!

ሠላም ይስጠን እግዜር ገናና
#ከጋረደን ጥቁር ደመና
ጊዜው ይሆን እላለሁ እኔ
የሚሆነውን ሳስተውል ባ'ይኔ

እንደው አንዳንዴ ይገርማል
አረ እንደው አንዳንዴስ ይደንቃል
እንዴት ተንዶ ፍቅራችን
ማነው ያራራቀን ከእውነት ቃል
በጊዜ አስታከን በዘመን
ራስን መውደድ አስቀድመን
ይቅርታ ራቀ ካ'ፋችን
ስናይ እየተጠማ ልባችን

አንቃን...

ይብቃችሁ በለን የፍቅር አምላክ ጌታ
አንቃን
ቅድስቷን ምድር ሠላም አውርሳት ደስታ
አንቃን
ከቁጣ አብርደህ ቀን ወዳጅ አ'ርገህ አንቀን
አንቃን

የት ይደረሳል
ምን ይወረሳል
ይብቃን
አቤቱ ..... አቤቱ
አውጣን ከመአቱ
ማረን ..... ማረን
ከክፉ አድነን

አፉ ቅዱስ ሰው ምግባሩ ሌላ
እንዳንሆን አውጣን ከዚህ #ፈተና
አፉ ቅዱስ ሰው ምግባሩ ሌላ
እንዳንሆን አውጣን እግዚኦ ማርና
.
.
ሠላም ይስጠን እግዜር ገናና
ከጋረደን ጥቁር ደመና
ጊዜው ይሆን እላለሁ እኔ
የሚሆነውን ሳስተውል ባ'ይኔ

በሀሜት በወሬ ታጅበን
በግላዊ ምቾት ተከበን
በዚች ጊዜያዊ ከንቱ ዓለም
ዘላ'ለም ቋሚ ግን አንድ የለም
ንብረት ከሰው ልጅ አብልጠን
ክፋት ምቀኝነትን መርጠን
ዘመን አለፈ ስንኖር
የፅድቁን መንገድ የሚያሳይ አጥተን

አንቃን
ይብቃችሁ በለን የፍቅር አምላክ ጌታ
አንቃን
ቅድስቷን ምድር ሠላም አውርሳት ደስታ
አንቃን
ከቁጣ አብርደህ ቀን ወዳጅ አ'ርገህ አንቀን
አንቃን
የት ይደረሳል
ምን ይወረሳል
ይብቃን
አቤቱ ..... አቤቱ
አውጣን ከመአቱ
#እግዚኦ
ማረን ..... ማረን
ከክፉ አድነን

አፉ ቅዱስ ሰው ምግባሩ ሌላ
እንዳንሆን አውጣን ከዚህ ፈተና
አፉ ቅዱስ ሰው ምግባሩ ሌላ
እንዳንሆን አውጣን እግዚኦ ማርና
አቤቱ ..... አቤቱ
አውጣን ከመአቱ
#እግዚኦ
ማረን ..... ማረን
ከክፉ አድነን

ድምፃዊ #ጎሳዬ_ተስፋዬ
#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ኢልመ ገልማ አባ ገዳ"
[አባት ዓለም ፀጋዬ እንደገጠመው]
ርቱዕ ጀማ፥ ብጹዕ ጀማ
ለካ አንተነህ...
አባ ገዳ፥ ኢልመ ገልማ
ያደ ኦሮሞ ሻማ
ዋቃ ገዲኒ፥ ነማ ኦሊኒ
ሱማ፥ አከ ሱማ
የተሰኘው፥ እንደአክሱማ
የተባልከው፥ ፍጹም ጀማ
ለካ አንተነህ......
-
አገ ኦጋ፥ ጂገ ሎጋ
አባ ሰርዳ፥ አባ ገዳ
አባ ፈርድ፥ ነበልባሉ
እም ቅድመ-ኦሪት፥ ባህሉ
ያኢ ቢያ፥ አባ ቃሉ
ቃ’ሉ’፥ የማይቀለበስ ቃሉ
ለካ አንተነህ........
-
ሴኧ’ት፥ አርካ
ኦ’ግ ገዳ፥ የአድባር ዋርካ
ያ’ዴ እናቴ፥ ያዴ እሴቴ
ያ’ዴ አቴቴ፥ ያዴ እቴቴ
ያቴ ኦራ፥ የኩሽ ነዶ
አባ ቦኩ፥ አከሚዶ
ባናትህ ጸሃይ፥ ከለቻ
የምትጠልቅ፥ አንተ ብቻ
የካም ኢደ ኢዶ ምድር
ተነባቢ፥ አስር ምስጢር
አባ ወሮ፥ አባ ወራ
አባ ባሮ፥ አባ በራ
አባ ካሮ፥ አባ ከራ
የጅቡቲም፥ ጀበጂሾ
የመቅዲሾም፥ መቀዲሾ
የነሙቴሳ፥ ከምበልኣ
እንደ ባሮ፥ ከምበልኣ
መነ..ደላ፥ አከ መንደላ
መቀ..ደላ፥ አከ መቅደላ
የፉላኒ፥ ካኖ ደላ
የምትሰኝ፥ የምታሰኝ
የጎና ቤት፥ አባ ከራ
የላሊ ቤት፥ ላሊ በራ
የከረዩ፥ አባ ከራ
በጎፈሬህ፥ ስሪት ላባ
አዶ አዶዬ፥ ውብ ቀዘባ
አዳ የከለቻ ተሸላሚ
የአዱ ግንባር፥ ተቀዳሚ
የአዲስ ዘመን፥ መጸው አደይ
አዳ አዱኛን፥ እልል እሰይ
የምታሰኝ፥ የምትሰኝ
አዱ አዱኛ፥ አባ ቢሌ
የአካ ኪሌ፥ የአባቢሌ
ለካ አንተነህ........
-
ገዳ ገዳም፥ የአለም ሰላም
ገዳ ቢሉሱማ ሳቃ
ፈካ ጉራቻ፥ አካ ዋቃ
የጻህፍት አምላኩ አኒ
ያለበሰህ ድርብ ከኒ
የጥቁር ፥ ፈርኦን ልሳን
የአዴ ኣዳ፥ ፀሃይ ብርሃን
የአዱሊስ፥ አዱኛ ኪዳን
አባ ገዳ፥ አባ በኣል
የቅድመ አክሱማዊት ቃል
የአስርቱ በሮች፥ መሰላል
የማለዳ ንጋት፥ ፀዳል
የኦሩስ፥ ኦሪሳ ተምሳል
ለካ አንተነህ...........
-
ኣገ ኦጋ፥ ጂገ ሎጋ
ያኢ ቢያ፥ አባ ቃሉ
የማይቀለበስ፥ ቃሉ
ርቱዕ፥ ጀማ
የተባልከው፥ አገሱማ
እንደ አክሱማ
ያደ ኦሮሞ፥ ሻማ
አባ ገዳ፥ ኢልመ ገልማ
ለካ አንተነህ........
ፀጋዬ ገ/መድህን 1964

@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim
#Meron_Getnet
በሜሮን ጌትነት

"አበበ በሶ በላ
ጫላ ጩቤ ጨበጠ
ጨቡዴ ጣሳ አጠበ"
ሲሉን መምህራችን
ያንን መድገም ነበር ዋና
ተግባራችን
ከዓረፍተ ነገሩ ስኬት የዘለለ
ጠያቂም ተማሪ መሀላችን የለ
ፈተናም ሲመጣ...
ያችኑ ከመድገም የለም ሌላ
ጣጣ
አበበ ዳሽ በላ ዳሽ ጩቤ
ጨበጠ
ቢበዛ ቢበዛ ዓረፍተ ነገሩ
የተገለበጠ
ኋላ ግን ተማሪ ያሉትን
ከመድገም ከመከትል ወጥቶ
መጠየቅ ሲጀምር የሀሳቡን
መሰረት ይዘቱን አጥንቶ
አበበም ጨቡዴም ጠፉ ደግነቱ
ጫላንም ሰረዘው ስርዓተ
ትምህርቱ
እንጂ በዚያ ክፍል ለነበር
ተማሪ
የጊዜው ፈተና ሆኖ አደናጋሪ
"አበበ በላ የሚለው
በቀን ስንት ጊዜ ነው?
ሶስት ጊዜ ከበላ ምርታማ
ሆኗል ገበሬ
ማዳበሪያ ተጠቅሞ ገቢ
ጨምሯል ሀገሬ
እንዴት አድርጎ ነው የበላ?
ጭብጦዎቹ ስንት ናቸው?
ክልሎችን የሚወክል ይሆናል
ወይ ብዛታቸው?
በሶው ራሱ ሲታይ ገና
ከአፈጫጨቱ
ልሟል ወይስ ሽርክት ነው?
በደንብ ይጠና ዱቄቱ
አስፈጪዎችን ገምግሙ ...
የአፈፃፀም ችግርም ይኖረዋል
ወፍጮ ቤቱ
ጫላ ጩቤ ሲጨብጥ ዝም
ይባላል ወይ ታይቶ?
ወይስ በሽብር ይከሰሳል
ከወይህኒ ቤቱ ገብቶ
የትምክት ነው የጠባብነት
ጩቤውን አጨባበጡ?
ብለው ነበር እኚያ ሰውዬ
'በሳንጃ ይወጋ ቂጡ'
ርዝራዥ ነው የቀድሞ የሳቸው
ስርዓት ናፋቂ
ልማቱን አደናቃፊ የሽብር
ጩቤ ነቅናቂ!
ጨቡዴስ የሚያጥበው ጣሳ
ምንድነው አገልግሎቱ?
ጠላ ሊሸጥበት ነው? ውሃ
ሊቀዳ ልፋቱ?
ወጣም ወረደ ያተርፋል ስንት
ይክፈል ግብር በወቅቱ?"
ይልና በጥያቄ ውስጥ ምላሹን
ራሱ አብራርቶ
ተማሪውን ይሞግታል
በመደምደሚያው ፀንቶ
አበበን ለበሶ ጠርቶ
ለምግብ ለጥጋብ አጭቶ
ጫላን ጩቤ ማስጨበጥ
ጨቡዴን አጣቢ ብሎ
ህገ መንግስት ይፃረራ ይባላል
የብሄር መድሎ!
. . .
አበበ በሶ በላ
ጫላ ጩቤ ጨበጠ
ጨቡዴ ጣሳ አጠበ"
ሲሉን መምህራችን
ያንን መድገም ነበር ዋና
ተግባራችን
ከዓረፍተ ነገሩ ስኬት የዘለለ
ጠያቂም ተማሪ መሀላችን የለ
ግና በዚያ ሰሞን የነበር ተማሪ
የጊዜው ፈተና ሲሆን አስቸጋሪ
ጥያቄ አስቀይሮ መልስ
እንደማቃናት
ስህተቱን ሊያርም በሌላ
ስህተት
የምናብ እውነቱን ከሃቁ
ደባልቆ
መምህር ይሞግታል ከተፈታኙ
ፊት ፈተናውን ሰርቆ
"አበበ በላ" ለሚለው...
"ከየት አምጥቶ ይበላል? ረሀብ
ገብቶ በሀገሩ
አደግን ሊሉን ነው እንጂ አሀዝ
እየጨመሩ
አበበማ እንዴት ይበላል በሶውን
የት አስፈጭቶ?
አንድ ወር አለፈው አሉ
መብራት ከቀረ ጠፍቶ
የወፍጮ ቤቱን ወርፋ ሲጠብቅ
ሲጠብቅ ከርሞ
አልደርስ ሲል ጨረሰው
ጥሬውን እህል ቆርጥሞ
በዚህ ምክንያት አበበ ስለተኛ
ሆዱን ታሞ
መብት አስጠባቂ ድርጅት
ያጣራ ጉዳዩን ቀርቦ
ጫላ ጩቤ ጨበጠ
ምድር ተገለበጠ
ጨቡዴ ጣሳ እያጠበ የዕለት
ጉርሱን ከሸፈነ
ከጠላ ጠጪ ተወዳጀ ከባለጊዜ
ወገነ"
በሚል የፅንፍ ሃሳብ መልሱን
አዘጋጅቶ
ይወድቃል ተማሪ ከአስር ዜሮ
አምጥቶ
. . .
አበበ በሶ በላ
ጫላ ጩቤ ጨበጠ
ጨቡዴ ጣሳ አጠበ"
ሲሉን መምህራችን
ያንን መድገም ነበር ዋና
ተግባራችን
ዘንድሮ ትምህርቱ በኖረ ፖሊሲ
መምህሩን ቀይሮ
ፈተና ያደቆነው ተማሪ ደርድሮ
ሊያስተምር ይተጋል የየኔታን ሀ
ሁ በፍቅር ቀምሮ
ተማሪውም ነቅቷል!
ደርዝ ያለው ጥያቄ ስንል ደርሶ
ይበዛል
አልፈተን ባዩ ቀድሞ መምህር
ያዛል
'በአንድነት ተባበር የቤት ስራ'
ሲባል በትር ይማዘዛል::
"አበበ በሶውን ቋጥሮ ...ጫላም
ጬቤ እንደጨበጠ
ጨቡዴም በባዶ ጣሳ
በህብረት ለለውጥ ይነሳ!"
ተብሎ በሶ ለመብላት የጋራ
ገበታ ቀርቧል
ትልቅ መዳፍ አለኝ ባይ....
ሳህን ሙሉ በሶ ዱቄት በአንድ
ጭብጥ ይተምናል
ሌላው በሌላ በኩል...
'ጭብጦዬን ቀሙኝ' ብሎ
በተራው ጨባጭ ይከሳል
የባሰበት 'ብላ' ሲሉት በመብቱ
መጠጥ ይመርጣል
ከዱቄቱ እፍኝ ወስዶ በሶውን
ይበጠብጣል
በዚህ ሁሉ መሀል...
በፅንፈኞች ሀሳብ በግራና በቀኝ
አጉል ተወጥሮ
ሊዛመድ በማይችል; ምርጫ
ባልተሰጠው ጥያቄዎች ታጥሮ
'እውነት/ውሸት' የሚል
አማራጭ ሲፈልግ ከሞኝ
ተቆጥሮ
ጠያቂ ተማሪ በሁለት ጥይት
ሞተ ከመሀል ቤት ሰፍሮ
የአበበ በሶ የጫላ ጬቤና
የጨቡዴ ጣሳ
በየፖለቲካው እየተጣመመ
ሲወድቅ ሲነሳ
"ትምህርት" ይሉት ነገር...
ይኸው ሆኖ አረፈው ለመምህር
ፈተና ለተማሪ አበሳ!

©kinchebchabi
@Simetin_Begitim
አትምጣ ብለሺኝ
.... (...ዶ.ር በድሉ ዋቅጅራ...) ....

ከነብስሽ ተሙዋግተሽ፣

ከራስሽ ተጣልተሽ፣

ህመም ነህ ብለሺኝ፤

ካለም ተቆራርጠሽ፣

ሱባኤ ተቀምጠሽ፣

ኃጥያት አድርገሽኝ፣

ደጅሽን ቆልፈሽ፣

መብራትሽን አጥፍተሽ፣

አትምጣ ብለሽኝ፣ ትጠብቂኛለሽ።

ስትገርሚ 😁😁😘😘😘

@Simetin_Begitim
"እኔ_ደግሞ …."
(አሌክስ አብርሃም)

ምንድነው እንደዚህ - ፊቴን በብረሃን
ከንፈሬን በውብ ሳቅ - የሚያጥለቀልቀው፣
ምንድነው ከልቤ - ኮለል ያለ ሰላም - በጧት የሚፈልቀው?።
እያልኩ አስባለሁ ……

እኔ ደግሞ …..
ምንድነው ሰው ሁሉ- ነጫጭ ክንፍ አብቅሎ - መ,ላክ የመሰለው፣
ምንስ ነው ሰማዩ - እንዲህ ተጠቅልሎ -
በጀ የምይዘው - መሃረም ያከለው።

ኧረ ምን ታምር ነው - መሬት መዞር ትታ - በፎይታ ያቆማት፣
ምንድነው ጨረቃን - ከሰማይ አወርዶ - ምድር -ያሳረፋት?።
እያልኩ አስባለሁ

እኔ ደግሞ …..
የጠሉኝን ሁሉ - ድንገት የመውደዴ፣
መሬቱን ለቅቄ - ባየር ላይ መንጎዴ።

ምንድነው ሚስጥሩ-ቆይ ውስጤን ምን ነካው፣
አለም እንዲህ ጠቦ - በርምጃ ሚለካው።

ውቂያኖስ በፍኘ - ተጨልፎ የሚደርቅ፣
ተራራው በክንዴ - ተጎሽሞ ሚደቅ።

ማነው በመንገዴ - ሳልፍ እልል የሚለው አበባ ነስንሶ፣
ማነው ግማሽ ልቤን - ሸርፎ የወሰደው -በትልቁ ቆርሶ?።
ኧረ ምን ታምር ነው ?
እያልኩ አስባለሁ

እኔ ደግሞ …..
መንገዳኛው ሁሉ - የተከፋ ፊቱን -
በማን ተነጠቀ፣
ከጨፍጋጋ ፊቶች - የዚህ አይነት ብርሃን - እንዴት ፈነጠቀ።

ሚሊየን ህፃናት - ቀልብ በሚነሳ -
ስርቅርቅ ድምፃቸው፣
የት ቢዘምሩ ነው - ልቤ ሚሰማቸው።

በምን ተአምር ነው - ዛፎች የሚያረግዱት፣
በምን ጉድ አስማት ነው - የሰማይ ከዋክብት
ቁልቁል የሚበሩት።
እያልኩ አስባለሁ ….

እኔ ደግሞ ….
ቤሳ ቤስቲን ፍራንክ - ኪሴ ሳይጨመር፣
አመት የለበስኩት - ልብሴ ሳይቀየር።

የዘወትር ጉርሴ - ጣሙ ሳይነካ፣
እኔነት እኔ ውስጥ - ተቀይሯል ለካ።

እኮ በምን ምክንያት - እኔ ተቀየርኩኝ፣
እንዴት እኔ ነኝ ስል - እኔ ሌላ ሆንኩኝ።
እያልኩ አስባለሁ ……..
ለ ካ ስ ……………………..አፍቅሬሽ ነው!!!

@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim
ውድ የኢትዮጵያዊ ወጎች ቤተሠብ እንደምን ቆያችሁን ሁሌም እንደምንለው ሠላማችሁ የበዛ ይሁን፡፡ ወጋችን ኢትዮጵያ ብቻ ናት ስለኢትዮጵያዊነት አብረን እንሠብካለን ብለን ተነስተናል ፡፡ ለዛም የሚሆን የኢትዮጵያ አንድነትን የሚያሳዮ ፅሁፎች ያላችሁ አና እኛም እንደግበአት ወስደን መልሰን ወደ እናንተ ለማቅረብ ስላሰብን @Simetin_Begitimbot በዚህ ቡት እንድትልኩልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
ያወቁትን ማሣወቅ ትልቅነት ነው፡፡
@Simetin_Begitim
አንድ መድረክ ላይ ቻርሊ ቻፕሊን ለተመልካቾቹ አንድ ቀልድ ቀለደና ሁሉም ታዳሚዎች በጣም ሳቁ። ቻርሊ ያንኑ ቀልድ ደገመላቸውና ጥቂት ሰዎች ብቻ ሳቁ... . አሁንም ያንኑ ቀልድ ደገመው በዚህ ጊዜ ማንም አልሳቀም...??? ከዛም እነዚህን የሚያማምሩ ቃሎች ተናገረ.... .

"በአንድ ቀልድ ደጋግማችሁ ካልሳቃችሁ ለምን በአንድ የሚያስጨንቃችሁ ችግር ወይም ስጋት ላይ ደጋግማችሁ የምታዝኑት?"
ህይወት ውብ ነች...!!

በዚህ አለም ላይ ምንም ዘላቂ ነገር የለም ችግራችንም ቢሆን..

Haile Melekot
@Simetin_Begitim
@ከመጻሕፍት ዓለም በ🇪🇹
"... [አለቃ ገብረሐና] የሚጠሉት አንድ ፉንጋ ቄስ ነበር፡፡ ታዲያ ቄሰ ሆዬ የአባ ገብረሐናን ሸፋፋነት ያውቅ ኖሮ ‹‹አባ ሽፍን ጫማ በሸዋ በኩል መጥቷል ይባላልና እንዳያመልጥዎ›› ሲል ያሽሟጥጣቸዋል፡፡ [አለቃ ገብረሐናን] በነገር የሚቀድማቸው የለም፣ ‹‹አንተ ፊት ግዛና›› ብለው ኩምሽሽ አደረጉት፡፡”

“[አለቃ ገብረሐና] ብቸኝነቱ ቢጫጫናቸው … ሴት ማዘውተር ጀመሩ፡፡ ሆኖም ጠላቶቻቸው ይከታተሏቸው ኖረው አንድ ቀን ሴት ቤት አድረው ሲወጡ ያያቸው ካህን ሲገሰግስ ራጉኤል ሄዶ ጉዳያቸውን ነገረባቸው፡፡ አለቃ አገር ሰላም ብለው ቤተክርስቲያን ሊገቡ ሲሉ ተከለከሉ፡፡
‹‹ለምን?››
‹‹ሴት ስለነኩ››
‹‹አይ ጥሩ›› ብለው አለቃም ተመለሱና ሳይታዩ የሴቶች መግቢያ በር ላይ ቆመው የመጡትን ሴቶች ሁሉ ‹‹መግባት ተከልክሏል›› ብለው መለሷቸው፡፡ ካህናቱ አንዲት የሔዋን አምሳል እንኳን በግቢ ውስጥ ቢያጡ ተደናግጠው ሁኔታውን ሲያጣሩ አለቃ ሁሉንም መመለሳቸውን ሰሙ፡፡
ካህናቱ ወዲያውኑ ንጉሡ ዘንድ ሄደው ከሰሷቸው፡፡ ‹‹ሴት ቤት አድረው ከመምጣታቸውም በላይ ሴቶችን ሁሉ ቤተክርስቲያን አትሳሙ ብለው መልሰዋል›› ሲሉም ወነጀሏቸው፡፡
‹‹ለምን እንዲህ አደረግህ ገብረሐና?››
‹‹እንዴ ጃንሆይ! እኔ ነካህ ተብዬ ስከለከል እነሱ ይዘውት ይግቡ እንዴ?›› ብለው ምኒልክን አሳቋቸው፡፡”

(“አለቃ ገብረሐና እና አስቂኝ ቀልዶቻቸው” ከሚለው የአረፈዓይኔ ሐጎስ መጻሕፍ የተወሰደ)


@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim
ኢትዮጵያዊ ወጎች
ኑ ኢትዮጵያዊነትን እንስበክ
ወጋችን ኢትዮጵያ ብቻ ናት ፡፡
በተጨማሪ ቢነበቡ የማይሠለቹ ግጥሞችን ትምህርት ሰጪ ፅሁፎችን ከ Surprise Gift ጋር ያገኛሉ፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለሙ ተከብራ ትኑር!

@Simetin_Begitim
©ግጥም ብቻ
የማርያም ንግስ ዕለት
(ኤፍሬም ስዩም)
የማርያም ንግስ ዕለት...
አዳፋ ነጠላ
የቀጠነ ገላ ፥ ነፋስ የሚጥለው
የነተበ ጫማ...
ጥቁር ያዘን ቀሚስ ፣ ኑሮ ያጨቀየው
ለብሳ የተገኘች...
ከቤተስኪያን አጸድ ፥ ቆማ ከዋርካ ስር
አንዲት ሚስኪን ባልቴት ...ትለማመን ነበር
አደራሽን ማርያም
አደራሽን ማርያም
እበላው የለኝም ፣ መሶቤ ተራቁቷል
እለብሰው የለኝም ፣ ጀርባዬ ተራቁቷል፡፡
ወድቃ እየተነሳች
እምባ እያፈሰሰች
ተስፋዋ ማርያምን ፣ ትለምናት ነበር
ከቤተስኪያን ጎሮ ፣ ቆማ ከዋርካው ስር፡፡
የደብሩ አለቃ
ካባ ላንቃ ለብሶ ፣ ምጣህቱን ደርቦ
ልክ የሌለው ቦርጩ ፣ ወደፊት ተስቦ
የንግሱን ምእመን ፣ ወደፊቱ ስቦ
ጮክ ብሎ ያወራል
ጮክ ብሎ ያስተምራል

የመቅደሱ ቀለም ፣ ሊታደስ ይገባል

የካህናት ደሞዝ ፣ ሊጨመር ግድ ይላል

ደጀሰላም ወንበር ፣ እጅጉን ያንሰናል
እናም...
ከዚህ ታላቅ ደብር ፣ ይህ ችግር ስላለ
ለማርያም የሚሆን ፣ እጃችሁ የታለ?
እያለ፡፡
ህዝቡን ያስተምራል
ህዝቡን ይደልላል፡፡
ለንግሱ የመጡ...
ባለ ብዙ ብሮች
ብዙ ባለጠጎች...
ጥለት የለበሱ ፣ በሽቶ የራሱ
ቆመው የነበሩ ...እፊት ከመቅደሱ
ቀለም እንዲቀባ ፣ እንዲታደስ ደብሩ
ለደጀ ሰላሙ ፣ ደሞም ለወንበሩ
በሺ..."የሚቆጠሩ
ብሮች ወረወሩ"
የደብሩ አለቃ ፣ ግንባር በጣም ወዛ
የሚወረወረው ፣ ብሩም በጣም በዛ፡፡
.
የዛች የምስኪን ነፍስ
ያች ታላቅ መቅደስ
ቆማ ከዋርካው ስር
ተስፋዋ ማርያምን ፣ ትለማመን ነበር
አደራሽን ማርያም
አደራሽን ማርያም
እበላው የለኝም ፣ መሶቤ ተራቁቷል
እጠጣው የለኝም ፣ ማድጋዬ ጎድሏል
እለብሰው የለኝም ፣ ጀርባዬን በርዶታል
አንቺ ነሽ 'ተስፋዬ' ፣ የኔ 'ተስፋ 'ሞቷል
ወድቃ እየተነሳች
እንባ እያፈሰሰች፡፡
ግና -ግን ለዛሬ ፣ለክብርሽ እንዲሆን
ተቀበይ ስጦታ ፣ ውሰጂ እንባዬን
የሟች ባሌን ማስታወሻ ፣ የአንገት ሀብሌን፡፡

@Simetin_Begitim
#ኢትዮጵያዊ ወጎች #Ethiopian
ሠላም ለኢትዮጵያ 🇪🇹
ሠላም ለህዝቦቿ 🇪🇹
ሠለም ለምድሪቷ 🌍
ሠላም ለሠው ዘር በሙሉ🕊


መልካም የትምህርት እና የሥራ ቀን ይሁንላችሁ !!
@Simetin_Begitim