አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ
ኅዳር 27/2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ተስፋሁን ጎበዛይ ከህዳር 25/2017 ዓ.ም ጀምረው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እንዲያገለግሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተሹመዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው በዛሬው ዕለት በአገልግሎቱ አመራሮችና ሠራተኞች የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ተደርጎላቸው ሥራቸውን መጀመራቸውን ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።
ኅዳር 27/2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ተስፋሁን ጎበዛይ ከህዳር 25/2017 ዓ.ም ጀምረው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እንዲያገለግሉ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተሹመዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው በዛሬው ዕለት በአገልግሎቱ አመራሮችና ሠራተኞች የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ተደርጎላቸው ሥራቸውን መጀመራቸውን ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።
ሰክሮ አካባቢን ማወክ
#ሕግ_ይዳኘኝ
ከልክ ያለፈ የአልኮል መጠጦችን መውሰድ ለስካር ይዳርጋል፡፡ ከመጠን በላይ አልኮል መጠጣት የሚያስከትለው የጤና ችግር እንደተጠበቀ ሆኖ ሰዎች በስካር መንፈስ የመኖሪያ አካባቢያቸውን ለረብሻሉ ይችላሉ፡፡
ስካር ድፍረትን የሚሰጥ በመሆኑ የሰከሩ ሰዎች ከአልኮል ግፊት ነጻ በነበሩበት ወቅት ማድረግ የማይደፍሩትን፣ የማይፈልጉትን እና የማይችሉትን ነገሮች ለማድረግ ይደፋፈራሉ፡፡ ይጮሃሉ፤ ይረብሻሉ፡፡
ይህ ድርጊት ግን በስካር መንፈስ ስለተደረገ ብቻ ችላ ተብሎ አይታለፍም፡፡ በሕግ ያስጠይቃል፡፡ ተገቢ እና ተመጣጣኝ ቅጣትም ያስከትላል፡፡
በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 819 መሰረት ማንም ሰው ሰክሮ ወይም አዕምሮ የሚያናውጥ ነገር ቀምሶ በሕዝብ አደባባይ የሚያስነቅፍ እና የሚያስነውር ስራ የፈጸመ፣ የማስፈራራት ንግግርን የተናገረ እንደሆነ ከስምንት ቀን በማይበልጥ በማረፊያ ቤት ይቀጣል፡፡
ይሄም ሰክሮ ሕዝብን ማወክ ሲሆን ምንም እንኳን ለከባድ አደጋ የሚያጋልጥ ባይሆንም በየሰፈራችን፣ በመጠጥ ቤቶች፣ በመንገዶች እና በተለያዩ ቦታዎች ድርጊቱ በተደጋጋሚ ሲፈጸም ይስተዋላል፡፡
በወንጀል ሕግ አንቀጽ 531 በተደነገገው መሰረት ደግሞ አልኮል በመጠጣት የሌላውን ሰው ጤንነት ለአደጋ ያጋለጠ እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራትና በመቀጮ ይቀጣል፡፡
ይሁን እንጂ አንድ ሰው ጠጥቶ ከባድ ወንጀል ቢፈጽም የፈጸመው ወንጀል በሕግ አግባብ የሚያስቀጣውን ቅጣት ይቀበላል፡፡
በብርሃኑ አበራ
#ሕግ_ይዳኘኝ
ከልክ ያለፈ የአልኮል መጠጦችን መውሰድ ለስካር ይዳርጋል፡፡ ከመጠን በላይ አልኮል መጠጣት የሚያስከትለው የጤና ችግር እንደተጠበቀ ሆኖ ሰዎች በስካር መንፈስ የመኖሪያ አካባቢያቸውን ለረብሻሉ ይችላሉ፡፡
ስካር ድፍረትን የሚሰጥ በመሆኑ የሰከሩ ሰዎች ከአልኮል ግፊት ነጻ በነበሩበት ወቅት ማድረግ የማይደፍሩትን፣ የማይፈልጉትን እና የማይችሉትን ነገሮች ለማድረግ ይደፋፈራሉ፡፡ ይጮሃሉ፤ ይረብሻሉ፡፡
ይህ ድርጊት ግን በስካር መንፈስ ስለተደረገ ብቻ ችላ ተብሎ አይታለፍም፡፡ በሕግ ያስጠይቃል፡፡ ተገቢ እና ተመጣጣኝ ቅጣትም ያስከትላል፡፡
በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 819 መሰረት ማንም ሰው ሰክሮ ወይም አዕምሮ የሚያናውጥ ነገር ቀምሶ በሕዝብ አደባባይ የሚያስነቅፍ እና የሚያስነውር ስራ የፈጸመ፣ የማስፈራራት ንግግርን የተናገረ እንደሆነ ከስምንት ቀን በማይበልጥ በማረፊያ ቤት ይቀጣል፡፡
ይሄም ሰክሮ ሕዝብን ማወክ ሲሆን ምንም እንኳን ለከባድ አደጋ የሚያጋልጥ ባይሆንም በየሰፈራችን፣ በመጠጥ ቤቶች፣ በመንገዶች እና በተለያዩ ቦታዎች ድርጊቱ በተደጋጋሚ ሲፈጸም ይስተዋላል፡፡
በወንጀል ሕግ አንቀጽ 531 በተደነገገው መሰረት ደግሞ አልኮል በመጠጣት የሌላውን ሰው ጤንነት ለአደጋ ያጋለጠ እንደሆነ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራትና በመቀጮ ይቀጣል፡፡
ይሁን እንጂ አንድ ሰው ጠጥቶ ከባድ ወንጀል ቢፈጽም የፈጸመው ወንጀል በሕግ አግባብ የሚያስቀጣውን ቅጣት ይቀበላል፡፡
በብርሃኑ አበራ
የቱሪስት መስህቦችን መጎብኘታችን ለማስተዋወቅ መነቃቃት ፈጥሮብናል- የሚክታ አባል ሀገራት አምባሳደሮች
ኅዳር 27/2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቱሪስት መስህቦችን መጎብኘታችን ለማስተዋወቅ መነቃቃት ፈጥሮብናል ሲሉ የሚክታ አባል ሀገራት አምባሳደሮች ገለጹ።
ከሜክሲኮ፣ ኢንዶኔዢያ፣ ደቡብ ኮርያ፣ ቱርክ እና አውስትራሊያ (ሚክታ) ያቀፈው የጥምረቱ አምባሳደሮቸ የቱሪዝም ሚኒስቴር ድኤታ ሽለሺ ግርማ ጋር በጋራ መስራት በሚችሉበት ጉዳይ ላይ ተወያይተዋል።
በሚኒስቴሩ ጋባዥነት የተደረገላቸው የሁለት ቀናት የድሬዳዋ እና የሀረሪ ጉብኝት እንዳስደሰታቸው ተናግረው የቱሪስት መስህቦችን መጎብኘታቸው ለማስተዋወቅ መነቃቃት እንደፈጠረላቸውም መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።
ኅዳር 27/2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቱሪስት መስህቦችን መጎብኘታችን ለማስተዋወቅ መነቃቃት ፈጥሮብናል ሲሉ የሚክታ አባል ሀገራት አምባሳደሮች ገለጹ።
ከሜክሲኮ፣ ኢንዶኔዢያ፣ ደቡብ ኮርያ፣ ቱርክ እና አውስትራሊያ (ሚክታ) ያቀፈው የጥምረቱ አምባሳደሮቸ የቱሪዝም ሚኒስቴር ድኤታ ሽለሺ ግርማ ጋር በጋራ መስራት በሚችሉበት ጉዳይ ላይ ተወያይተዋል።
በሚኒስቴሩ ጋባዥነት የተደረገላቸው የሁለት ቀናት የድሬዳዋ እና የሀረሪ ጉብኝት እንዳስደሰታቸው ተናግረው የቱሪስት መስህቦችን መጎብኘታቸው ለማስተዋወቅ መነቃቃት እንደፈጠረላቸውም መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ ከፀረ- አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን ማኔጅመንት አባላት ጋር ተወያዩ
ኅዳር 27/2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ ከፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን ማኔጅመንት አባላት ጋር ተወያይተዋል።
በውይይቱ ተቋሙ የተቋቋመበትን ዓላማ፣ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት እና ትኩረት የሚሸ ጉዳዮችን የሚዳስስ ሰነድ ቀርቧል።
ሚኒስትሯ በውይይቱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተጣለበትን ሀላፊነት ከመወጣት አንጻር እየሰራቸው ያሉ ስራዎች አበረታች ናቸው ያሉ ሲሆን በአለም አቀፋ ጸረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን የበለጠ ቅቡልነት ለማግኘት መስራት ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ መክዩ መሀመድ በበኩላቸው የላብራቶሪ ስራውን ትኩረት ሰጥተን በመስራት ለምርመራ ወደ ሌላ አገር በመሄድ የምናወጣው ወጭና እንግልት መቀነስ ያስፈልጋል ማለታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መኮንን ይደርሳል ጥፋተኛ ሁነው የተገኙ አካላት ተገቢውን አስተዳደራዊና የወንጀልኛ እርምጃ እንዲወስድባቸው ከፍትህና ከጤና ሴክተር ባለድረሻ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት የዋና መስሪያ ቤት ድጋፍ ያስፈልጋል ብለዋል።
ኅዳር 27/2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሽዊት ሻንካ ከፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን ማኔጅመንት አባላት ጋር ተወያይተዋል።
በውይይቱ ተቋሙ የተቋቋመበትን ዓላማ፣ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት እና ትኩረት የሚሸ ጉዳዮችን የሚዳስስ ሰነድ ቀርቧል።
ሚኒስትሯ በውይይቱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተጣለበትን ሀላፊነት ከመወጣት አንጻር እየሰራቸው ያሉ ስራዎች አበረታች ናቸው ያሉ ሲሆን በአለም አቀፋ ጸረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን የበለጠ ቅቡልነት ለማግኘት መስራት ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ መክዩ መሀመድ በበኩላቸው የላብራቶሪ ስራውን ትኩረት ሰጥተን በመስራት ለምርመራ ወደ ሌላ አገር በመሄድ የምናወጣው ወጭና እንግልት መቀነስ ያስፈልጋል ማለታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መኮንን ይደርሳል ጥፋተኛ ሁነው የተገኙ አካላት ተገቢውን አስተዳደራዊና የወንጀልኛ እርምጃ እንዲወስድባቸው ከፍትህና ከጤና ሴክተር ባለድረሻ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት የዋና መስሪያ ቤት ድጋፍ ያስፈልጋል ብለዋል።
የተሰረቁ ሞባይሎችንና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ከሌቦች በመቀበል የተጠረጠረ ግለሰብ ተያዘ
ኅዳር 27/2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተሰረቁ ሞባይሎችንና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ከሌቦች በመቀበል የተጠረጠረ ግለሰብ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታው ጦር ኃይሎች አካባቢ ጥናትን መነሻ አድርጎ በሞባይል ጥገና ስም በተከፈተ ሱቅ ውስጥ ባደረገው ፍተሻ 29 የተለያዩ መጠን ያላቸው ሞባይል ስልኮች߹ 26 የእጅ ሰዓቶች߹ 6 የእጅ ብራስሌቶችን እና አንድ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር አውሏል።
ፖሊስ በጀመረው ምርመራ ግለሰቡ ምንም አይነት የንግድ ፈቃድ ሳይኖረው የሞባይል ጥገና አገልገሎት የሚሰጥ በመምሰል የተሰረቁ ሞባይሎችንና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ከሌቦች የሚቀበል መሆኑን አስታወቋል ፡፡
ፖሊስ የተሰረቀ እቃ የሚገዙ ህገ-ወጦች ለወንጀል መስፋፋት መንስኤ በመሆናቸው የሌባ ተቀባዮች ላይ እየተደረገ ያለው ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስቦ ንብረታቸው የተሰረቀባቸው ግለሰቦች ወደ ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በአካል በመሔድ መረከብ እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡
ኅዳር 27/2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተሰረቁ ሞባይሎችንና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ከሌቦች በመቀበል የተጠረጠረ ግለሰብ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታው ጦር ኃይሎች አካባቢ ጥናትን መነሻ አድርጎ በሞባይል ጥገና ስም በተከፈተ ሱቅ ውስጥ ባደረገው ፍተሻ 29 የተለያዩ መጠን ያላቸው ሞባይል ስልኮች߹ 26 የእጅ ሰዓቶች߹ 6 የእጅ ብራስሌቶችን እና አንድ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር አውሏል።
ፖሊስ በጀመረው ምርመራ ግለሰቡ ምንም አይነት የንግድ ፈቃድ ሳይኖረው የሞባይል ጥገና አገልገሎት የሚሰጥ በመምሰል የተሰረቁ ሞባይሎችንና የተለያዩ ቁሳቁሶችን ከሌቦች የሚቀበል መሆኑን አስታወቋል ፡፡
ፖሊስ የተሰረቀ እቃ የሚገዙ ህገ-ወጦች ለወንጀል መስፋፋት መንስኤ በመሆናቸው የሌባ ተቀባዮች ላይ እየተደረገ ያለው ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስቦ ንብረታቸው የተሰረቀባቸው ግለሰቦች ወደ ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በአካል በመሔድ መረከብ እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡
ሀዲያ ሆሳዕና አዳማ ከተማን አሸነፈ
ሕዳር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 10ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሀዲያ ሆሳዕና አዳማ ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ሀዲያ ሆሳዕና ኢዮብ አለማየሁ እና በረከት ወ/ዮሐንስ ባስቆጠሯቸው ሁለት ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
በተመሳሳይ ቀን 10 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው የሊጎ 10ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ስሑል ሽረ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተለያይተዋል።
ሕዳር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 10ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሀዲያ ሆሳዕና አዳማ ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ሀዲያ ሆሳዕና ኢዮብ አለማየሁ እና በረከት ወ/ዮሐንስ ባስቆጠሯቸው ሁለት ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
በተመሳሳይ ቀን 10 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው የሊጎ 10ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ስሑል ሽረ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተለያይተዋል።
በጂንካ ከተማ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሄደ
ኅዳር 28/2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ ታዋቂ አትሌቶች የተሳተፉበት የስምንት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሄደ።
ታህሳስ 1 ቀን 2017 ዓ.ም የሚከበረውን የአሪ ህዝብ የዘመን መለወጫ “የድሽታ ግና'' በዓልን እና የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀንን ምክንያት በማድረግ በተካሄደው የስምንት ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ላይ በርካታ የከተማው ነዋሪዎች፣ ከተለያየ አካባቢ የመጡ እንግዶች እና አትሌቶች ተሳትፈዋል።
የአሪ ዞን አስተዳደር ከፋን ኢትዮጵያ ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጀው የሩጫ ውድድር "ታላቁ ሩጫ ለድሽታ ግና፤ ለሰላም እና አንድነት እሮጣለሁ!" በሚል መሪ ሀሳብ መካሄዱን ኢዜአ ዘግቧል።
በመርኃ ግብሩ ላይ አትሌት ፋንቱ ሚጌሶን ጨምሮ ሌሎች አትሌቶች እና የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ተፅእኖ ፈጣሪ ሰዎች እንዲሁም አርቲስቶች ታድመዋል።
ኅዳር 28/2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ ታዋቂ አትሌቶች የተሳተፉበት የስምንት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ተካሄደ።
ታህሳስ 1 ቀን 2017 ዓ.ም የሚከበረውን የአሪ ህዝብ የዘመን መለወጫ “የድሽታ ግና'' በዓልን እና የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀንን ምክንያት በማድረግ በተካሄደው የስምንት ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ላይ በርካታ የከተማው ነዋሪዎች፣ ከተለያየ አካባቢ የመጡ እንግዶች እና አትሌቶች ተሳትፈዋል።
የአሪ ዞን አስተዳደር ከፋን ኢትዮጵያ ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጀው የሩጫ ውድድር "ታላቁ ሩጫ ለድሽታ ግና፤ ለሰላም እና አንድነት እሮጣለሁ!" በሚል መሪ ሀሳብ መካሄዱን ኢዜአ ዘግቧል።
በመርኃ ግብሩ ላይ አትሌት ፋንቱ ሚጌሶን ጨምሮ ሌሎች አትሌቶች እና የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ተፅእኖ ፈጣሪ ሰዎች እንዲሁም አርቲስቶች ታድመዋል።