AddisWalta - AW
45.8K subscribers
42.4K photos
208 videos
20 files
16.7K links
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
Download Telegram
በድሬዳዋ በአሸዋ የገበያ ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ ንብረት ወደመ

ሰኔ 25/2016 (አዲስ ዋልታ) በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አሸዋ ገበያ ሰልባጅ ተራ ሰፈር በተነሳ የእሳት አደጋ ከፍተኛ የሆነ ንብረት ወድሟል።

ከአካባቢው ምንጮች ባገኘነው መረጃ መሰረት የእሳት አደጋው በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት አላደረሰም።

ከስፍራው ተቀርጸው በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ እየተዘዋወሩ ከሚገኙ ተንቀሳቃሽ ምስሎች እንደተመለከትነው አደጋው በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት አስከትሏል።

አሁን ላይ አደጋውን ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠር ተችሏል።

በሔለን ታደሰ
ሽረ እንዳሥላሰ
#ከተሞቻችን

በ14ኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ በመንደርነት ተመስርታ በ1928 ዓ.ም ወደ አውራጃነት ያደገችው ሽረ በአሁን ሰዓት የሰሜን ምዕራብ ትግራይ ክልል ፈርጥ ከተማ ስትሆን የታህታይ ቆራሮ ወረዳ አስተዳደር ማዕከል ነች።

ሽረ ከባህር ጠለል በላይ 1ሺሕ 953 ሜትር አማካኝ ከፍታ እና ወይና ደጋ የአየር ፀባይ ያላት በኮረብታማ መልከዓ ምድር የተከበበች ከተማ ስትሆን ከመዲናችን አዲስ አበባ በስተሰሜን 1ሺሕ 87 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች።

ከስያሜዋ ጋር በተያያዘ በጊዜው የነበረ ጀግና ኩናማዎችን አሸንፎ ከተማውን እንደተቆጣጠረ ለሕዝቡ ማሸነፉን ለመግለፅ በትግርኛ ቋንቋ "ስዒረ" ማለቱን ተከትሎ ሽረ ተብላ መጠራት እንደጀመረች በአፈታሪክ የሚነገር ሲሆን ጥንታዊቷ የቅድስት ስላሴ ገዳም ከከተማዋ ስም ጋር ተቀፅላ ሆና ትጠራለች።

በጣሊያናዊ መሀንዲስ ማስተር ፕላን የተሰራላት ሽረ ታዋቂ ከሆኑ የሰፈር ስያሜዎቿ መካከል ኣጓዱ፣ ተክልዬ(24)፣ ዲቦራ፣ እንዳ ጀርመን፣ ቀይ ለከፍ፣ ድልድል፣ መድየ እና ቄራ ተጠቃሾች ናቸው።

በከተማዋ አማካኝ ስፍራ ላይ ከሀገር ባለውለታ የጦር ጀነራሎች መካከል ስሙ በጉልህ የሚነሳው የሜጀር ጀነራል ሓይሎም አርአያ ሐውልት ይገኛል።

ሽረ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች የሚገኙባት ከተማ ስትሆን ከእነዚህም መካከል ገባር ሽረ፣ ቃሌም፣ አፍሪካ፣ ሀዳስ ኢንተርናሽናል እና ደጀና ሆቴሎች ተጠቃሽ ናቸው።
ተጨማሪውን ለማንበብ👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0w94my5XJ5kGCJWbx6A7qMRqJmqQ6YbqcFB4TyeA2g9VU7ZzE1CKaWehjjjLgTxbvl
ተወዳጁ ተዋናይ #ዘሪሁን አስማማው በእንደራሴ ሲትኮም መጥቷል።

#እንደራሴ በቅርብ ቀን በአዲስ ዋልታ ቴሌቪዥን

#አዲስ_ዋልታ #ሲትኮም #እንደራሴ
በዛሬው #አመሻሻችን፡-

👉#ዋልታ_በዘመናት - ኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫ አዘጋጅነት
👉#ጤናማ - ቢላሉል ሀበሺ የልማት እና መረዳጃ እድር የበጎ አድራጎት ሥራ
👉#የእርስዎ_መክሰስ - የሐመሮች “ወጠሌ” ጥብስ
👉#እጥፋት - ወረቀትን የፈጠረው ቻይናዊ ፃይ ሉን እንዲሁም ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ።

ከ12፡00 እስከ 1፡00 ሰዓት በአዲስ ዋልታ ቴሌቪዥንና በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችን ይጠብቁን!
የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብርን አስጀመሩ

ሰኔ 25/2016 (አዲስ ዋልታ) የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብርን በዛሬው ዕለት አስጀምረዋል።

የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብሩ የተጀመረው በትግራይ ደቡባዊ ዞን ውስጥ ነው።

በማስጀመሪያ በመርኃ ግብሩ ላይ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ እንደተናገሩት በክልሉ የተራቆቱ ተራሮች መልሰው እንዲያገግሙ ሁሉም ህብረተሰብ በችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በንቃት ተሳታፊ መሆን ይጠበቅበታል።

ባለፉት ዓመታት የወደሙ ደኖችን ለመመለስና አረንጓዴ አካባቢን ለመፍጠር ችግኝ መትከልና መንከባከብ ወሳኝ ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል።

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዓለምብርሃን ሀሪፈዮ በበኩላቸው በዚህ ዓመት በ144 የችግኝ ማዕከላት ችግኞች የማፍላት ስራ መከናወኑን ገልጸዋል።

በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩም 38 ሺህ ሄክታር መሬት የማዳን ስራ እንደሚከናወን ተናግረዋል።

ህብረተሰቡ የተከላቸውን ችግኞች በመንከባከብ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ እውን እንዲሆን ማድረግ አለበት ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
ቢቢሲ በሮናልዶ ፍጹም ቅጣት ምት መሳት ላይ በመሳለቁ ተተቸ

ሰኔ 25/2016 (አዲስ ዋልታ) ቢቢሲ ትናንት ፖርቹጋል ከስሎቫኒያ ጋር በነበረ የአውሮፓ ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ የፍጹም ቅጣት ምት በሳተው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ላይ በጻፈው ሽሙጥ በእግር ኳስ ወዳጆች ተተቸ።

ሮናልዶ ቡድኑ በጭማሪ ሰዓት ያገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ከሳተ በኋል ሲያለቅስ የታዬ ሲሆን ቢቢሲ ሁኔታውን “ሚስቲያኖ ፔናልዶ” በማለት ተጫዋቹ ላይ በመቀለዱ በርካታ የእግር ኳስ ቤተሰብን አስቆጥቷል።

የቀድሞው የቸልሲ ተከላካይ ጆን ቴሪ በኢንስታግራም ገጹ “ልታፍሩ ይገባል” ሲል ቢቢሲን ወርፏል።

ሌላ የእግር ኳስ ታዳሚ ደግሞ የቢቢሲን ተግባር “ርኩስ ድርጊት” ሲለው “ሚስቲያኖ ፔናልዶ የቢቢሲ ጥላቻ ነው” ሲል ገልጾታል።

የቢቢሲ ከሙያዊ ስነምግባር ያፈነገጠ ድርጊት በርካታ የእግር ኳስ አድናቂዎችን ያበሳጨና ያሳዘነ ድርጊት እንደነበር ኢንድፔንደንት ዘግቧል።

በትናንት ምሽቱ ጨዋታ ሮናልዶ የመለያ ምቱን በማስቆጠርና የፖርቱጋል በረኛ ዲያጎ ኮስታ ሶስት የፍጹም ቅጣቶችን በማዳን ቡድኑ ወደ ቀጣዩ ዙር እንዲያልፍ አስችለውታል።
መደጋገፋችን የቆየ እሴታችን ቢሆንም ይበልጥ በማጎልበት አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ሰኔ 26/2016 (አዲስ ዋልታ) መደጋገፋችን የቆየ እሴታችን ቢሆንም ይበልጥ በማጎልበት አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ፡፡

የ2017 ዓ.ም ክልል አቀፍ የክረምት በጎ ፈቃድ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር በኮምቦልቻ ከተማ ተጀምሯል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በየአካባቢያችን የሚገኙ አቅመ ደካሞችን በመደገፍ እና በተለያዩ በጎ ሥራዎች በመሰማራት የ2016 ዓ.ም የክረምት ወራትን ማሳለፍ እንደሚገባ ገልጸዋል።

የሰው እና የተፈጥሮ ግንኙነት የተስማማ ይሆን ዘንድ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአረንጓዴ አሻራ ሊሳተፍ ይገባልም ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የክረምት በጎ ፈቃድ ማስጀመሪያ መርኃግብር የአረጋዊያንን ቤት በመጠገን፣ በችግኝ ተከላ እና የጎዳና ላይ ሩጫ በማከናወን፣ ለአቅመ ደካሞች ማዕድ በማጋራት፣ ለአካል ጉዳተኞች የዊልቸር ድጋፍ በማድረግ እና የደም ልገሳ በማከናወን መካሄዱን አሚኮ ዘግቧል።

በመርኃ ግብሩ ርእሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ እና ከፍተኛ የክልል የሥራ ኃላፊዎቸ ተገኝተዋል።
#የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ከ700 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች ይሰጣል።

ፈተናው በኦንላይን በመሆኑ ተማሪዎች እና ወላጆች ይጠቅማልም ይጎዳልም ያሉትን የተለያዩ አስተያየቶች ሲሰጡ ተመልክተናል።

የተማሪዎችን የወደፊት እጣፋንታ በሚወስነው በዚህ ፈተና ዙሪያ መምህራን፣ ተማሪዎችና ወላጆችን ጨምሮ የቀድሞ ተፈታኞች ሐሳብ አስተያየታችሁን አጋሩን

#እንወያይበት
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ከማርዮት ኢንተርናሽናል ፕሬዝዳንትና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጋር ተወያዩ

ሰኔ 26/2016 (አዲስ ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ጠዋት የማርዮት ኢንተርናሽናል ፕሬዝዳንት እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አንቶኒ ካፑአኖ ጋር ተገናኝተው በማደግ ላይ በሚገኘው የኢትዮጵያ የጉዞ እና የሆስፒታሊቲ ዘርፍ ላይ ተወያይተዋል።

በውይይቱም በባህል ሀብቷ እና ታሪካዊ ቅርስ ይዞታዋ ብሎም በአስደናቂ የመልክዓ ምድር ገፅታዋ የታወቀችው ኢትዮጵያ የቱሪዝም ኢንዱስትሪዋን በማስፋፋት ላይ ማተኮሯ ተገልጿል።

በዓለም ዙሪያ 8785 ያህል ቅርንጫፎች እና የሀብት አድራሻዎች በመያዝ በመስተንግዶ እና ማረፊያ አገልግሎት ዘርፍ መሪ የሆነው ማሪዮት ኢንተርናሽናል በዚህ ስራ ጉልህ ሚና ለመጫወት ትልም መያዙንም ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
"ከማርዮት ኢንተርናሽናል ፕሬዝዳንት እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አንቶኒ ካፑአኖ ጋር በቱሪዝም ዘርፍ ኢትዮጵያ ያላትን ፍላጎት እና የሀገራችንን እምቅ የቱሪዝም ሀብት ለመጠቀም በትብብር ለመሥራት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ውይይት አድርገናል።" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
ደራሲ፣ ገጣሚና ጋዜጠኛ ነብይ መኮንን አረፈ

ደራሲ፣ ገጣሚና ጋዜጠኛ ነብይ መኮንን ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

በወግ አዋቂነቱ ብዙዎች የሚያደንቁት ጋዜጠኛ ነብይ ነገም ሌላ ቀን ነው፣ የኛ ሰው በአሜሪካ፣ ስውር ስፌት እና የመጨረሻው ንግግር የተሰኙ መጻሕፍትን ጨምሮ ሌሎች መጻሕፍትን አሳትሞ ለአንባቢያን አብቅቷል።

ዋልታ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬት ለቤተሰቦቹ ለጓደኞቹ እንዲሁም ለጥበብ አፍቃሪዎች መጽናናትን ይመኛል።
የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ስፋት እና ይዘት አዲስ ከተማን የመገንባት ያህል ነው።
በኮሪደር ልማት ስራዎቻችን ከተሰሩት መካከል፡-

1. የመንገድ መሰረተ ልማቶች
• ከ48 ኪ.ሜ በላይ የተሽከርካሪ መንገድ፣
• ከ96 ኪሎ ሜትር በላይ ሰፋፊ የእግረኛ መንገድ በግራና በቀኝ ተሰርቷል
• 100 ኪ.ሜ የብስክሌት መንገድ፣
• 4 የመሬት ውስጥ የእግረኛ (underpass) መንገዶች፣
• 5 ኪ.ሜ የመሮጫ ትራክ፣
• ⁠2 ትልልቅ የተሽከርካሪ ድልድዮች፣
• ⁠3 ዘመናዊ የእግረኛ ድልድዮች፣
• አጠቃላይ ከ240 ኪ.ሜ በላይ መንገድና ተያያዥ መሠረተልማቶች፣

2. የትራንስፖርት ስርዓት
• በአንድ ጊዜ 6,369 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችሉ 32 ዘመናዊ ፓርኪንጎች (ከዜሮ ወለል እስከ ሶስት ቤዝሜንት ያላቸው)፣
• በአንድ ጊዜ 517 ተሸከርካሪዎችን የማስተናገድ አቅም የሚያስችሉ 9 የባስ እና ታክሲ ተርሚናሎች፣
• በአንድ ጊዜ 268 ባሶችንና ታክሲዎችን ለአጭር ጊዜ የመጫንና ማውረድ አገልግሎት የሚሰጡ 85 የመንገድ ዳር የባስና ታክሲ ቤይ፣
• 50 ኪሎ ሜትር የትራንስፖርት ደህንነት ማረጋገጥ የሚያስችል የብልህ (ITS) ስርዓት።
👇👇
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0RscYUFKNGnqSysMEnvTaFc6sLwcMK5Lt6Smxs5JZZW5TbWSMtisfB4yLnW9anBvpl
የአሳማ ደምን ወደ ውኃ ለመቀየር የሚያስችል ቴክኖሎጂ
#ቴክኖ_ቅምሻ

አንድ የቤልጂየም ኩባንያ የአሳማን ደም ለሰው ፍጆታ ተስማሚ ወደሆነ ውኃ ለመለወጥ የሚያስችል የውኃ ማቀነባበሪያ አዘጋጅቷል።

ቬኦስ በዝዌቬዜሌ ዌስት ፍላንደርስ ላይ የተመሠረተ የእንስሳት ደም እና ኮላጅን ለሰው እና ለእንስሳት የምግብ ምርቶች ጥቅም ላይ ወደሚውለው ከፍተኛ ጥራት ያለው የፕሮቲን ፓውደር በማሰራት ለምግብ ኢንዱስትሪ የእንስሳት ፕሮቲኖችን በማምረት ላይ የተሰማራ ኩባንያ ነው፡፡

እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ኩባንያው ያከማቸውን የአሳማ ደም ግዙፍ ታንከሮች ለማጽዳት ከፍተኛ መጠን ያለው የከርሰ ምድር ውኃ ይጠቀም ነበር። ይሁን እንጂ ቬኦስ ለውሃ ማጣሪያ ተከላ ኢንቨስትመንት 2 ሚሊዮን ዩሮ በመመደብ የተጠራቀመውን የአሳማ ደም ወደ ንጹህ የመጠጥ ውኃ ለመቀየር እየሰራ እንደሚገኝ ኦዲቲ ሴንትራል ዘግቧል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ይሰጣሉ

ሰኔ 26/2016 (አዲስ ዋልታ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የፌዴራል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል።

ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎችም ማብራሪያና ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ3ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ ሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሚገኙበት 36ኛ መደበኛ ስብሰባውን ይካሂዳል፡፡

በኢፌዲሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 55 (17) እና በምክር ቤቱ የአሰራርና የአባላት ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 81 (3) እና አንቀፅ 92 መሰረት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደበኛ ስብሰባው በመገኘት በፌዴራል መንግስቱ የ2016 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እና በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ይሰጣሉ፡፡

በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 55 (11) እና በምክር ቤቱ የአሰራርና የአባላት ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 76 መሰረትም ምክር ቤቱ የ2017 የፌዴራል መንግስት በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ አዳምጦ ረቂቅ በጀቱን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በምክር ቤቱ 36ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ

ሰኔ 26/2016 (አዲስ ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሹመቶች መስጠታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

በዚህም፡-
- ሽዊት ሻንካ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር

- ካሳሁን ጎፌ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር

- ቀጀላ መርዳሳ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወጣቶች እና ስፖርት አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
በዛሬው #አመሻሻችን👇

#ባለታሪካችን ስለሁለገብ አርቲስቷ ሙናዬ መንበሩ ያስቃኘናል

#ሳና_አፍሪካ ዴንቨር ስለሚገኘው ፖል ሃሚልተን አስደናቂ የአፍሪካ ጥበብ ስብስብ

#ሀገርዎን_ይወቁ ስለጥንታዊቷ ከተማ ሀረር

#ስፖርት ስለአውሮፓ ዋንጫ ድንቅ ፉክክሮች

ከ12፡00 እስከ 1፡00 ሰዓት በአዲስ ዋልታ ቴሌቪዥንና በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችን ይጠብቁን!
#አጃ 🌾 ለጤና ያለው ጥቅሞች

👉ፊትና አንገት ላይ የሚወጣ የቆዳ በሽታን ለመከላከል ይረዳል

👉የደረቀ የሰውነት ቆዳን ያለሰልሳል

👉ሰውነት ላይ የሚወጣ አላርጂን ይከላከላል

👉ቆዳችን ወዛማ እንዲሆን በማድረግ ያሳምራል

👉በፊታችን ላይ ያሉ የሞቱና የተጎዱ ህዋሶች እንዲወገዱ ያደርጋል

👉በሰውነታችን ውስጥ ያሉትን ቆሻሻና ዘይት ያስወግዳል

👉የደረቀና የሚያሳክክ የራስ ቆዳን ያክማል

👉ፎረፎርን ይከላከላል

👉ፀጉራችን እንዲያድግ ይረዳል

👉መጥፎ ጠረንን ያስወግዳል

👉ኮሊስትሮልን ይቀንሳል

👉ጠንካራ አጥንት እንዲኖረን ያደርጋል

👉የፎሊክ አሲድ፣ የታያሚን እና የናያሲን መገኛ ነው
ሀገርህ ናት በቃ!

#ነቢይ መኮንን #ስውር_ስፌት