የጊንር ጽጌ ተዋህዶ ሰ/ት ቤት
279 subscribers
863 photos
14 videos
12 files
19 links
ይህ ቻናል ዓላማውን የሰንበት ት/ ቤቱን ጠቃሚ መረጃዎች እና መልእክት ማስተላለፍ አድርጎ ጥር 19/2012ዓም ሌሊት 6:50 ላይ ተከፈተ፡፡
Download Telegram
ዓርብ

የስቅለት ዓርብ ይባላል

ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና ማቴ ፳፯፥፴፭ የስቅለት ዓርብ ይባላል።

መልካሙ ዓርብ ይባላል

ከጌታ ስቅለት በፊት በተለይም በሮማውያን ህግ የወንጀለኛ መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል ጌታችን በደሙ ቀድሶ የምህረት፣ የሕይወት አርማ፣ የዲያቢሎስ ድል መንሻ ስላደረገው፤ በሞቱ መልካሙን ሕይወት ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ይባላል።

-----------------------------------------

“ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም።” 1ኛ ዮሐንስ 4፥10

እንኳን አደረሳችሁ !!
"በላይ በሰማያት በኪሩቤል ክንፍ የምትከለለው በኢየሩሳሌም ግን የእሾህ አክሊል ተቀናጀህ".... ውዳሴ መስቀል....
"በባሕርዩ የማይመረመር እርሱ ጀርባዬን ለግርፋት ፊቴን ለጽፋት ሰጠሁ፤ ከማያሳፍር ምራቅም ፊቴን አልመለስኩም አለ"....ድርሳነ አትናቴዎስ....
አውቀውስ ቢሆን የክብር ባለቤት ጌታን ባልሰቀሉትም ነበር ሰማይ ዙፋኑ ምድር በእግሮቹ የተረገጠች ስትሆን ስለኛ በእንጨት ተሰቀለ
....ድርሳነ ማኅየዊ ዘዐርብ....