TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.66K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ET302

መጋቢት 1/2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲጓዝ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ET302 ማክስ 8 አውሮፕላን የተከሰከበት ቦታ ላይ ዛሬ የሙት አመት መታሰቢያ ስነስርአት ተከናውኗል።

ስነስርአቱ የተዘጋጀው በአካባቢው ነዋሪዎች ሲሆን በሚልኪ የማስታወቂያ ስራዎች አስተባባሪነት የሚከናወን መሆኑን የሚልኪ አድቨርታይዚንግ ስራ አስኪያጅ አቶ ቀልቤሳ መገርሳ ተናግረዋል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ETH302

ለቦይንግ 737 አውሮፕላን ሰለባዎች ሙት አመት መታሰቢያ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ካህናት ጸሎት አድርገዋል። የአካባቢው ፈረሰኞች ዛሬ ለአመት የዘለቀው ሀዘን የሚያበቃበት ቀን መሆኑን ለማሣወቅ ጥቁር እና ነጭ ሰንደቅ አላማዎችን በመያዘ ተገኝተው ነበር። አባ ገዳዎችም ምስጋና አቅርበዋል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪዎችን የትራንስፖርት ችግር ለመፍታት በተያዘው በጀት ዓመት አንድ ሺ የሚሆኑ የግል ታክሲዎችን ለማስገባት መታቀዱን የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ባለሥልጣን አስታውቋል። በመንግሥት ሦስት ሺ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሶችን ለማስገባት እየተሠራ መሆኑንም ተሰምቷል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ItsMyDam

ኢትዮጵያ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላትን አቋም ለማስረዳት በተለያዩ አገራት ከፍተኛ የልኡካን ቡድን በመላክ ላይ ትገኛለች።

በዚሁ መሰረት በኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ የተመራ ከፍተኛ የልኡካን ቡድን ዛሬ መጋቢት 3 ቀን 2012 ዓም ኬንያ ናይሮቢ በመገኘት ኢትዮጵያ በታላቁ የህዳሴው ግድብ ጋር በተያያዘ ያላትን ግልጽ አቋም ለፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ አስረድቷል።

ሁለቱ መሪዎች ከህዳሴው ግድብ ጋር በተያያዘ ያደረጉትን ውይይት ተከትሎም የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።

በፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሚመራው የልኡካን ቡድን በቀጣይም በሌሎቹ የአባይ ተፋሰስ አገራት ተመሳሳይ ጉብኝት በማድረግ ለአባል አገራቱ መሪዎች የኢትዮጵያን አቋም እንደሚያስረዳ ይጠበቃል።

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የመርካቶ የአውቶብስ ተርሚናል!

የመርካቶ የአውቶቡስ ተርሚናል ግንባታ በመፋጠን ላይ መሆኑን የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። የተርሚናሉ ግንባታ 84 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን፥ በ2012 በጀት አመት ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ርብርብ በመደረግ ላይ ነው፡፡

የአውቶቡስ ተርሚናሉ የተሳፋሪዎችን ምቾት በመጠበቀ በርካታ አገልግሎቶችን መስጠት ያስችላል፡፡ ተርሚናሉ በአንዴ ለ20 አውቶቡሶች አገልግሎት መስጠት የሚያስችል፤ የራሳቸው መግቢያ እና መውጫ ያላቸው ሁለት ወለሎችን አካቷል፡፡

#EPA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Attention

ተጓዳኝ ሕመም የሌለባቸውና በዕድሜ ወጣት የሆኑ ሰዎች በኮቪድ-19 ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑን በሚሊኒየም የኮቪድ19 ሕክምና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ውለታው ጫኔ አስታወቁ።

ቫይረሱ በራሱ ተጨማሪ ተጓዳኝ የጤና ችግሮችን እንደሚያስከትል አሳስበዋል።

ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ውለታው ፤ "የኮቪድ 19 ቫይረስ ተጓዳኝ ህመም ያለባቸውንና በዕድሜ የገፉትን ብቻ ነው የሚያጠቃው የሚለው የተሳሳተ ግንዛቤ አሁንም በስፋት ይስተዋላል። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የታየው ግን የተጠቁት ተጓዳኝ ህመም የሌለባቸው በ30ዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ጭምር ናቸው" ብለዋል።

ምንም ዓይነት ተጓዳኝ ህመም የሌለባቸውና በዕድሜ ወጣት የሆኑ ሰዎች በቫይረሱ ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተሩ፣ ምናልባት በዕድሜ የገፉና ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው ላይ የበለጠ ቢከፋም እየሞቱ ያሉት ግን በሁሉም የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ዜጎች መሆናቸውን ገልፀዋል።

አሁን ላይ ባለው ሁኔታ የጽኑ ህሙማን ታካሚዎችና በኮቪድ-19 ሕይወታቸው የሚያልፍ ወገኖች ቁጥር ጨምሯል። የማሽን ድጋፍና ኦክስጅን የሚያስፈልጋቸው ታካሚዎች ቁጥር ከዕለት ወደ ዕለት እያደገ መምጣቱን አስታውቀዋል።

እንደዶ/ር ውለታው ገለፃ፤ ከወራት በፊት 60 % የሚሆኑ ታካሚዎች ቶሎ አገግመው የሚወጡ ታካሚዎች ነበሩ፤አሁን ላይ ግን ከ50 በመቶ በላይ ያለው ታካሚ በፀና ታሞ የሚመጣ ነው። ይህም የሚያሳየው መዘናጋት መኖሩንና ከውጭ ተጎድተው መቆየታቸውን ነው።

ጥንቃቄ በጎደለ ቁጥር የቫይረሱ ዝውውር እየሰፋ እንደሚሄድ ያመለከቱት ዶክተሩ ከሰዎች ጋር ሳይገናኙ በቤት ውስጥ የቆዩ እናቶችና አባቶች መዘናጋት በመኖሩ ምክንያት በቫይረሱ የመጠቃት ዕድላቸው እየጨመረ መጥቷል። ይህም የሞት ቁጥር እንዲጨምር ማድረጉን አመልክተዋል።~ #EPA

@tikvahethiopia
የተማሪዎችን ቅበላ እና ድልደላ የሚያስተዳድርበት ሥርዓት ማዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል !

የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን ቅበላና ድልደላ የሚያስተዳድርበት ሥርዓት ማዘጋጅቱን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ዋና ዳይሬክተር ተሻለ በሬቻ ለኢፕድ እንደገለፁት፣ ዩንቨርሲቲው የተማሪዎችን ቅበላና ድልደላ የሚያስተዳድርበት ሥርዓት አዘጋጀቶ ለኢፊድሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲፀድቅ አቅርቧል።

በዚህም በቅርቡ ፀድቆ ዩንቨርሲቲው ተማሪዎችን መቀበል እንደሚጀምር ገልጿል።

እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ፤ ዩንቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን መቀበል የሚጀምር ሲሆን ተማሪዎቹ በኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የሚሰጥ የመግብያ ፈተናም እንደሚሰጣቸው ገልፀዋል።

በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት ወር ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን ተቀብሎ በመጀመሪያ ዲግሪ እንደሚያስተምርም ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። #EPA

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የሀዋሳ ታቦር ተራራ በባለሃብቶች እንዲለማ ለማድረግ እየተሰራ ነው ተባለ።

የሀዋሳ ልዩ መለያ የሆነው 'ታቦር ተራራ' ባላሀብቶች መዋዕለ ነዋያቸውን የሚያፈሱበትና የኢንቨስትመንት የስበት አካል እንዲሆን እይተሰራ መሆኑን የከተማይቱ ም/ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ተናግረዋል።

ምክትል ከንቲባው፥ የታቦር ተራራ ባለሃብቶች እንዲያለሙትና "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ሚስተካከል ልማት የሚከናወንበት ስፍራ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ሀዋሳ የመላው ኢትዮጵውያን ከተማ ከመሆን አልፋ የቱሪስቶች መዳረሻ በመሆኗ ሰፊ የኢንቨስትመንት ሥራ በማከናወን ሀገርን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

ምክትል ከንቲባው፥ ታቦር ተራራን ጨምሮ በሃዋሳ አቅራቢያ የሚገኙ ሃብቶችን ሥራ ላይ የማዋል ብርቱ ጥረት መጀመሩን ጠቁመው በቀጣይ ዘርፈ ብዙ ስራዎች እንደሚከናወኑ ገልፀዋል። #EPA

@tikvahethiopia
'የNISS ጥቆማ መቀበያ 910 '

ዜጎች ማንኛውም አይነት ለሀገርና ህዝቦች ሰላምና መረጋጋት እንቅፋት የሚሆኑና ከሀገራዊ ምርጫው ጋር በተያያዘ የደህንነት ስጋት ሊፈጥሩ የሚችሉ አጠራጣሪ ሁኔታዎችን በአቅራቢያቸው ሲመለከቱ ለብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አጭር የጥቆማ መስጪያ ቁጥር " 910 " በመጠቀም ጥቆማ መስጠት እንደሚችሉ ተገልጿል።

#EPA

@tikvahethiopia
#ATTENTION

" በቦረና ዞን የተከሰተው ድርቅ ወደ ምሥራቅ ባሌ ዞን እየተስፋፋ ነው " - የኦሮሚያ አደጋ ስጋትና የተነሽዎች ልማት ኮሚሽን

በቦረና ዞን የተከሰተዉ ድርቅ ወደ ምሥራቅ ባሌ ዞን እየተስፋፋ በመሆኑ ቀጣይነት ያለዉ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ የኦሮሚያ አደጋ ስጋትና የተነሽዎች ልማት ኮሚሽን አስታወቀ።

የኦሮሚያ አደጋ ስጋትና ተነሽዎች ልማት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሺነር ገረሙ ኦሊቃ ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፤ ቶሎ መፍትሔ ካልተበጀለት በስተቀር በቦረና ዞን የተከሰተዉ ድርቅ በተመሳሳይ ሁኔታ ወደ ምሥራቅ ባሌ ዞንና ሌሎች ኦሮሚያ ዞኖች እየተስፋፋ ነው።

በቦረና ዞን የተከሰተዉ ድርቅ በመንግሥት፣ በባለሀብቱና በኀብረተሰቡ በተደረገዉ ጥረት በሰዉ ሕይወት ላይ ጉዳት ሳያደርስ መከላከል ተችሏል ብለዋል።

እንደ ምክትል ኮሚሽነሩ ገለጻ፤ ምዕራብና ምሥራቅ ጉጂ፣ ምዕራብ ሀረርጌና ምሥራቅ ባሌ ዞኖች በቅርቡ ድርቅ ከታየባቸዉ አካባቢዎች ዉስጥ ይጠቀሳሉ።

ችግሩን ለመፍታት የክልሉና ፌዴራል መንግሥት ባለሀብቱና ኅብረተሰቡ በተለመደ መልኩ ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ።

የምግብና ዉሃ ችግርን ለመቅረፍ 25 ሺህ 330 ኩንታል እህልና 38 ቦቴዎችን በማቅረብ ችግሩን ለመቀነስት ጥረት እየተደረገ ነዉ።

የክልሉ መንግሥት ችግሩን ለመቅረፍ ከያዘዉ መቶ ሚሊዮን ብር በተጨማሪ ድርቁ በተስፋፋባቸዉ አካባቢዎች ለምግብና ለዉሃ አቅርቦት የሚዉል ተጨማሪ በጀት መመደቡን ተናግረዋል።

ችግሩ ሰፊና ዉስብስብ በመሆኑ በመንግሥት ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ ሌሎች አካላትም ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።

#EPA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲን አስጠነቀቀች። በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ እንዲሁም ድርጅቶች የሀሰት መረጃዎችን በማሰራጨት መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ መንግስት አስታውቋል። ከዚህ ቀደም አዲስ አበባ ተከባለች የሚል መረጃን ያሰራጩ እንደነበር ያስታወሰው መንግስት አሁን ደግሞ የሽብር ጥቃት ይፈፀማል የሚል ሀሰት መቀጠሉን ገልጿል። ኤምባሲው እና የአሜሪካ መንግስት የሀሰት መረጃዎችን ከማስተላለፍ እንዲቆጠቡ የኢትዮጵያ…
የአሜሪካ ኤምባሲ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቀማት ላይ ጫና በማድረግ ከአዲስ አበባ ለቀው እንዲወጡ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ መንግስት አስታውቋል።

በተለይም በህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ጥያቄ ያላቸውን ሀገራት በማስተባበር የአፍሪካ ህብረት መቀመጫን ከአዲስ አበባ ወደሌላ ሀገር እንዲዛወር ግፊት በማድረግ ላይ መሆኑንም መንግስት ገልጿል።

ኤምባሲው ከነዚህ እና ተመሳሳይ ተግባሮቹ እንዲታቀብ መንግስት አስጠንቅቋል። - #EPA

@tikvahethiopia
#ቅዱስ_ገብርኤል

• " ምንም የጸጥታ ስጋት አይኖርም " - የኦሮሚያ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ

• " የሀዋሳ ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ላይ ነው ያለው " - የሀዋሳ ፖሊስ መምሪያ

ነገ የሚከበረውን የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውን የኦሮሚያ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ እና የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አሳውቀዋል።

በዓሉ በተለይ በቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ከተለያዩ ቦታዎች የሚመጡ በርካታ እንግዶች የሚታደሙበት እንደመሆኑ ያለምንም የጸጥታ ስጋት እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የኦሮሚያ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው እንደ ክልል በቂ ዝግጅት በመደረጉ ምንም የጸጥታ ስጋት አይኖርም ብሏል።

የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ በበኩኑ የቅዱስ ገብርኤል በዓል በከፍተኛ ድምቀት በሚከበርባት ሀዋሳ በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ዝግጅት ተጠናቋል ሲል አሳውቋል።

የከተማው ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ላይ መሆኑንም አረጋግጧል።

በአሁኑ ወቅት ኅብረተሰቡ አካባቢውን በመጠበቅ እና መረጃ በመለዋወጥ ትልቅ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።

ከዚህ በተጨናሪ በጠ/ሚኒ ዐቢይ አሕመድ ጥሪ ከውጭ አገራት የሚመጡትን እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት መደረጉን ሀዋሳ ፖሊስ አሳውቋል።

የእንግዶችን ሰላም ለማስጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች አስተማማኝ ዝግጅት ማድረጋቸው ተጠቁሟል። እንግዶች ምንም ዓይነት የጸጥታ ስጋት ሊኖራቸው አይገባም ተብሏል።

ነጋዴዎች በተለይ ሆቴሎች አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እንዳያደርጉ ጠንካራ ቁጥጥር እንደሚደረግ እና የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ለእንግዶች መኪና ማቆሚያ እንደተዘጋጀ የሀዋሳ ፖሊስ አሳውቋል።

#Kulubi #Hawassa #EPA

@tikvahethiopia
" መንግስት አጥፊዎችን ተከታትሎ ለህግ ማቅረብ ይገባዋል " - የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ

በጥምቀት በዓል ላይ በቡራዩ ከተማ አስተዳደር ወይብላ ቅድስት ማሪያም ቤተክርስቲያን ላይ የተፈጸመውን ድርጊት እንደሚያወግዝ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አስታውቋል።

ጉባኤው ሃይማኖቶች የትህትና፣ የሰላምና የአንድነት፣ የፍቅርና መከባበር መሠረቶች ናቸው ብሏል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለዘመናት የሰላም መሠረት ሆና ዘልቃለች ያለው የጉባኤው መግለጫ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሃይማኖትን ሽፋን አድርገው ግጭት ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን አጥብቀን እንቃዎማለን ሲልም ገልጿል።

ጉባኤው ፤ ጥር 12/2014 ዓ.ም በቡራዩ ከተማ አስተዳደር በሕግ ማስከበር ሽፋን በቤተክርስቲያኗ ላይ የተቃጣው ድርጊት ፍጹም ሕገ ወጥ ነው ያለው መግለጫው መንግሥት አጥፊዎችን ተከታትሎ ለሕግ እንዲያቀርብም ጠይቋል።

መንግሥት የሃይማኖትን እና የዜጎችን ሰላም እና ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የጠየቀው ጉባኤው የሕይዎት፣ የአካልና የመንፈስ ስብራት በደረሰባቸው ወገኖች የተሠማንን ጥልቅ ሐዘንም በተሰበረ ልብ እንገልፃለን ብሏል።

#EPA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፈው ዓርብ በሃይማኖት አባቶች ፀሎትና ከተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች በተውጣጡ የአገር ሽማገሌዎችና እናቶች ምርቃት የተከናወነበት የሥራ ማስጀመሪያ ፕሮግራም አከናውኗል። የምክክር ኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን አርዓያ በወቅቱ ባሰሙት ንግግር፤ በኢትዮጵያ እርስ በርስ የማያግባቡ ጉዳዮችን ነቅሶ በማውጣት፣ በመነጋገርና በመደማመጥ " የሕዝብ ለቅሶና ዋይታ መርገብ…
#ETHIOPIA

ፕ/ር መስፍን አርዓያ (የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር) ፦

" ... የምክክር ኮሚሽኑ አመቻች እንጂ አደራዳሪም ሆነ እርቅ አስፈጻሚ አይደለም።

ኮሚሽኑ የድርድር ሥራ እንደማይሰራ፤ ዕርቅ እንደማያስፈጽም ሕዝብ ሊያውቅ ይገባል።

የአገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮችና አባላትን ለምክክሩ የሚረዱ መድረኮችና አጀንዳዎችን በማመቻቸት አስፈላጊው ሥራ ለማከናወን የተመረጥን መሆኑን ሁሉም ሊገነዘብ ይገባል።

የኮሚሽኑ ሥራ አጀንዳ ነቅሶ ሕዝብን ለውይይት መጋበዝ ነው። ለሕዝብ ከሚቀርቡት አጀንዳዎች ውስጥ መግባባት ላይ የሚያደርሰውን መንገድ እናመቻቻለን።

በዚህ አካሄድ ኮሚሽኑ አመቻች ሲሆን ዋናው ወሳኙ ሕዝብ ነው።

ምክክሩ ወደ ' ብሔራዊ እርቅ ' የሚወስድ ከሆነም በእራሱ አሰራርና አካሄድ መሰረት ወደ እርቅ ይሄዳል እንጂ ኮሚሽኑ ሽምግልና እና አሊያም ብሔራዊ እርቅ ማስፈጸም ውስጥ አይገባም።

አንዳንድ ጊዜ በተሳሳተ መንገድ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑን አሸማጋይ አሊያም አደራዳሪ አድርጎ የሚያይ ካለም የተሳሳተ ነው። የኮሚሽኑ ኃላፊነት አካታች በሆነ መንገድ ሁሉንም ጉዳይ አለኝ የሚል ወገንን በተመረጡ አጀንዳዎች ላይ እንዲመክር ማድረግ ነው። "

#EPA

@tikvahethiopia
#ከፍተኛ_የደም_እጥረት_ተከስቷል !

በብሔራዊ ደም ባንክ አገልግሎት የደም ለጋሾች ዘርፍ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶክተር ተመሥገን አበጀ ፦

" በአገሪቱ ያሉት የሁለቱ ትላልቅ ሃይማኖቶች ተከታዮች ፆም ላይ መሆናቸውን ተከትሎ በመላ አገሪቱ ከፍተኛ የደም እጥረት ተከስቷል።

በአገሪቱ ያለውም የመጠባበቂያ ደም ክምችት ከ5 ቀናት የማይበልጥ ነው።

በአገር ደረጃ ሲታይ ከፆም በፊት በዚህ ዓመት የነበረው የደም ክምችት አመርቂ የሆነበት ዓመት ነበር ብሎ መውሰድ ይቻላል።

የዐቢይና ረመዷን አፁዋማት ከገቡ በኋላ የመደበኛ ደም ለጋሾችም ሆነ ሌሎች ለጋሾች ቁጥር አሽቆልቁሏል።

ይህም የደም ክምችት ላይ ከፍተኛ እጥረት እንዲፈጠር አድርጓል።

በተለይ እንደ ፕላትሌት የደም ተዋፅዖ እና ‘ኦ’ የደም ዓይነት ክምችቶች እጥረት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።

ፕላትሌት የሚባለው የደም ተዋፅዖ ለካንሰር ታማሚዎች እና የደም መፍሰስ ችግር ላለባቸው ታካሚዎች የሚሰጥ የደም ዓይነት ነው፤ ክምችቱ ለአንድ ቀን ብቻ ሲሆን ‘ኦ' የተባለው የደም ዓይነትም በዛ ቢባል ለ2 ቀናት የሚሆን ክምችት ነው ያለው "

ያንብቡ : https://telegra.ph/EPA-04-19-2

#EPA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በሀገራችን በተለይ በአዲስ አበባ እጅግ በጣም ሙስና ስር ከሰደደበት አንዱ የመሬት ዝውውር ጉዳይ ነው። በዚህ ሂደት አንዳንድ የአስተዳደሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ደላላ ሆነው የተገኙበት ጊዜ መኖሩ ተጠቁሟል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሂክማ ከይረዲን ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፥ " " በመሬት ጉዳይ…
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ ከመሬት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን ከተናግሩት ፦

" ... በአዲስ አበባ ከተማ በእጅ መንሻ፣ በዝምድናና በተለያዩ ህገወጥ አካሄዶች ጉዳዮቻቸው #በፍጥነት የሚፈጸምላቸው ሰዎች አሉ። በአንጻሩ ደግሞ ህግን ተከትሎ የሚመጣው ደንበኛ ሲንገላታ ይስተዋላል። ችግሩ በተለይ በክ/ከተሞችና ወረዳዎች ላይ ሰፊውን ህዝብ ለእንግልት እየዳረገው ነው። በመሆኑም ከተማ አስተዳደሩ አፋጣኝ ማስተካከያዎችን እየወሰደ ይገኛል። "

#EPA

@tikvahethiopia
🤔

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፍቃደኛ አለመሆን የሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን ለማጣራት እያደረግኩት ባለው ጥረት ላይ እንቅፋት ሆኖብኛል ሲል የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ማስታወቁን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አስነብቧል።

የቢሮ ኃላፊ አቶ አሥራት አዳሮ ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፦

" በክልሉ ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ #ባለሙያዎችንና #ኃላፊዎችን የትምህርት ማስረጃዎቻቸውን በመያዝ ትምህርታቸውን ባጠናቀቁበት ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች ድረስ በመሄድ ማስረጃዎቹ ሐሰተኛ ናቸው ወይስ አይደሉም የሚለውን ለማጣራት ሙከራ ብናደርግም የግል ትምህርት ተቋማት ፈቃደኞች አይደሉም፡፡

ከ5 እና 6 ወር በኋላ ተመልሳችሁ ኑ የሚል ምላሽ ስለሚሰጡን ወደ ትምህርት ተቋማቱ የምንልካቸው ባለሙያዎች ለእንግልት እየተዳረጉ ነው።

ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የትምህርት ጥራትን ከመጉዳትም ባሻገር የተማረ የሰው ኃይል በተፈለገው ቦታ ላይ እንዳይሠራና ጥራት ያለው አገልግሎት ለኅብረተሰቡ እንዳይሰጥ የሚያደርግ ነው።

በሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች ተቀጥረው በሥራ ላይ በሚገኙ #አመራርና #ባለሙያዎች ሕዝቡ ትክክለኛ አገልግሎት እንዳያገኝ ሲያደርጉ ነበር ፤ ክልሉ የሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች የትምህርት መረጃን አጣርቶ በሚያገኘው ውጤት መሠረት ከሥራ እና ከደመወዝ ከማገድ ባሻገር በሕግ እንዲጠየቁ ይደረጋል።

የማጣራቱን ውጤት ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከ6ቱም ዞኖች የተጠቃለሉ መረጃዎችን በማደራጀት ምን ያህል አመራርና ባለሙያ በሐሰተኛ ትምህርት ማስረጃ ተቀጥሮ ሲሠራ እንደነበር ለሕዝቡ ይፋ ይደረጋል።  "

#EPA

@tikvahethiopia
#MoE

106 ሺህ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በሚሰጠው የአቅም ማሻሻያ የትምህርት ፕሮግራም ተካተዋል፡፡

በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ወስደው #ከ50_በመቶ በታች ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ለአራት ወራት ያህል በሀገሪቱ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በሚሰጠው የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ይሳተፋሉ፡፡

#Remedial ፕሮግራሙ ከአ/አ ዩኒቨርሲቲ፣ ከአ/አ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ውጪ ባሉ ሁሉም የመንግስት እና የግል ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር ከዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ባለሙያዎች እና ፕሮፌሰሮች ኮሚቴ በማዋቀር ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉት የትምህርት አይነት ይዘቶችን መለየቱን በሚኒስቴሩ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

በአቅም ማሻሻያ ፕሮግራሙ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፊዚክስ፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ እንግሊዘኛ፣ የተፈጥሮ ሳይንስና ሂሳብ የትምህርት አይነቶችን የሚወስዱ ሲሆን፤ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ታሪክ፣ ጂኦግራፊ፣ እንግሊዘኛ፣ ማህበራዊ ሳይንስና ሂሳብ ትምህርት አይነቶችን እንደሚወስዱ መሪ ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡

የትምህርት ይዘቶቹን መሰረት አድርጎ በተቋማት የሚዘጋጅ (ከ30 በመቶ) እና በማዕከል የሚዘጋጅ (ከ70 በመቶ) የሚያዝ ፈተና በመፈተን በድምሩ 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ የሚያገኙ ተማሪዎች መደበኛ የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን በመንግስት እና በግል ዩኒቨርሲቲዎች መቀጠል ይችላሉ ብለዋል፡፡ #EPA

More : @tikvahuniversity
የሰራዊቱ ተሽከርካሪዎች ሰሌዳ እየተቀየረ መሆኑ ተነግሯል።

የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አዲስ የተሸከርካሪ ሰሌዳ በማዘጋጀት በአገልግሎት ላይ እያዋለ መሆኑን አሳውቋል።

ሰራዊቱ ከዚህ ቀደም ሲጠቀምበት የነበረውን የተሸከርካሪ ሰሌዳ በአዲስ ሠሌዳ የቀየረ ሲሆን ከነሃሴ 25 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተሸከርካሪዎች ላይ በመለጠፍ አገልግሎት መጀመሩ ተገልጿል።

በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሁሉም የተቋሙ ተሸከርካሪዎች አዲስ ሰሌዳ እንደሚደርስ ይፋ ሆናል።

የሰሌዳ / ታርጋ ቅያሪ የተደረገው በተለያየ ምክንያት የተቋሙ በርካታ ሰሌዳዎች ከተቋሙ እውቅና ወጪ በሌሎች እጅ በመገኘቱ ነው ተብሏል።

በመሆንም እነዚህ ከተቋሙ እውቅና ውጭ በሌሎች እጅ የገቡ ሰሌዳዎች ለህገ-ወጥ ተግባር እንዳይውሉ ለመከላከል ታሳቢ ተደርጎ ሰሌዳው መቀሩን ሚኒስቴሩ አስረድቷል።

የተቀየሩት ሰሌዳዎች የሠራዊቱን ተልዕኮ እና ግዳጅ መነሻ አድርጎ በሚሰጡት አገልግሎት መሰረት #በኮድ ተለይተው የተዘጋጁ ናቸው ተብሏል። #EPA

@tikvahethiopia
#ICS

የሕዝብ ተ/ም/ቤት የሕግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ፤ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትን የ9 ወር አፈጻጸም ትላንት ገምግሟል።

ኮሚቴው ከዚህ ግምገማ በፊት ማለትም ሚያዚያ 3/2016 ላይ #ድንገተኛ ምልከታ አድርጎ ነበር።

ቋሚ ኮሚቴው ምን አለ ?

- ምንም እንኳ የተጀመሩ ሥራዎች ጥሩና ተስፋ ሰጪ ቢሆኑም በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ ችግሮችን እና የተገልጋይን ቅሬታ መፍታት አልተቻለም።

- ተገልጋዮች አገልግሎት ለማግኘት ብለው በሚደርስባቸው እንግልትና ስቃይ ምክንያት በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንደሚያቀርቡ በድንገተኛ ምልከታ መመልከት ተችሏል።

- በዋና መ/ ቤቱ ተገልጋይ በተቋሙ ሠራተኞች ፦
➡️ #መሰደብ
➡️ #መመናጨቅ
➡️ #መገፍተር_ጭምር የሚደርስበት በመሆኑ ተገልጋይ በሥነ ምግባር መስተናገድ አለበት።

- በአዲስ አበባ " ካሳንቺስ አካባቢ " የሚገኘዉ የውጪ ዜጎች አገልግሎት ተቋም የሚሰጠው አገልግሎት ኢትዮጵያን የማይመጥን፣ ምቹ ያልሆነ እና የንጽህና ጉድለት ያለው ነው። ይህ መታረም አለበት።

- ዋናው መስሪያ ቤት ለአገልግሎት ምቹ ያልሆነ፣ ሕንፃው የቆየ እና አስፈላጊዉን የማሻሻያ ጥገና ያላገኘ ነው። ሕንፃው ከተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ባህሪ ጋር የማይጣጣም ስሪት ያለው ነው።

- በዋና መስሪያ ቤት ያለው መጨናነቅ እንዲቀንስ በአዲስ አበባ ከተማ ከአምስት ያላነሱ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እንዲከፈቱ የመፍትሔ ሃሳብ ቢሰጥም አልተፈጸመም። በተለይ በአዲስ አበባ ቅርንጫፍ የማስፋፋት ሥራዎች መሠራት አለበት።

- የደላላ ሰንሰለት በመለየት ማቋረጥ ያስፈልጋል።

- አሁንም ከደላሎች ጋር የሚመሳጠሩ የተቋሙ #ሠራተኞች በመኖራቸው ትኩረት ሰጥቶ መሥራት አለበት።

- የሠራተኛ ባጅ አለመኖሩም ሊታሰብበት ይገባል።

በምክር ቤቱ የተገኙት የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ለተነሱት ጉዳዮች ምላሽ ሰጥተዋል።

ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/EPA-04-27-2 #EPA

@tikvahethiopia