TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#MoH

#ጨረታው_ተሰርዟል !

30 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የወባ አጎበር ግዢ ጨረታ ተሰረዘ።

የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር 30 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት በኬሚካል የተነከረ የወባ መከላከያ አጎበር ግዢ በኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት በኩል ግዢ እንዲፈጸም ጥያቄ አቅርቦ ነበር።

በዚህም መሰረት ፤ ዓለም አቀፍ ግልጽ ጨረታ ወጥቶ ተጫራቾች ቀርበው አሸናፊውን ቢለይም በጨረታው ሂደት ላይ ቅሬታ መቅረቡን ተከትሎ ሚኒስቴሩ ማጣራት በማድረግ ጨረታውን እንዲሰረዝ ማድረጉን አሳውቋል።

የጤና ሚኒስቴር በሌሎች ተቋማት የማጣራት ስራ መሰራቱን እንዲሁም ደግሞ በራሱ ባደረገው የማጣራት ስራ በጨረታ ሂደቱ ላክ የተፈጸመ ህገ-ወጥ ድርጊት እንዳላገኘ ገልጿል።

ነገር ግን " የብቃት ማረጋገጫ " እና " ምዝገባ " ጋር በተያያዘ በግብርና ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በህግ የተሰጠ ነገር ግን የስልጣን መደራረብ የነበረ መሆኑን እና የጨረታ መገምገሚያ መስፈርት ጋር በተያያዘ ቅሬታ ቀርቦ ባለበት ሁኔታ ሂደቱን ከማስቀጠል የፋይናንስ ድጋፍ በሚያደርገው ድርጅት አማካኝነት ግዢው እንዲፈጸም ማድረግ ለሚኒስቴሩ የተሻለ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን በመገንዘብ ጨረታው እንዲሰረዝ ተደርጓል፡፡

(ተጨማሪ ማብራሪያ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia