TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ነዳጅ

የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በሁለት ቀናት 43 ሺህ  የኤሌክትሮኒክ የነዳጅ የግብይት  ልውውጥ  መካሄዱን አሳወቀ።

ሚኒስቴሩ ይህን ያሳወቀው ለብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ / ኢብኮ በሰጠው ቃል ነው።

ሚኒስቴሩ ምን አለ ?

- በ2  ቀናት ብቻ 43 ሺህ  የኤሌክትሮኒክ የነዳጅ የግብይት  ልውውጥ ተካሂዷል። በዚህም 80 ሚሊዮን ብር የሚሆን ሽያጭ ተካሂዷል።

- አፈፃፀሙ ከቀን ወደ ቀን  መሻሻሎች እየታዩበት ነው።

- ለዝግጅት የተሰጠውን ጊዜ በአግባቡ ባለመጠቀም ከነዳጅ ማደያ ቀጂዎች  በኩል የመተግበሪያው አጠቃቀም ውስነት፣  የሰው ሀይል ቁጥር ማነስ  እና አንዳንድ አሽከርካሪዎች መተግበሪያው ሳይኖራቸው ለአገልግሎት መቅረባቸው ፤ የአገልግሎት አሰጣጡ እንዲስተጓጎልና ሰልፍ እንዲፈጠር አድርጓል። አሁን ላይ አፈፃፀሙ ከቀን ወደ ቀን መሻሻሎች  እየታዩበት  ነው።

- አንዳንድ  አሽከርካሪዎች በቂ ነዳጅ እያላቸው የክፍያ ስርዓቱ በቴክኖሎጂ  መደገፉን ተከትሎ በመደናገጥ  የመሰለፍ ሁኔታ በግንዛቤ እጥረት የተፈጠረ በመሆኑ እርምት ሊወሰድበት ይገባል።

- ነዳጅ የሚገዙት እና የሚሸጡት አካላት  ልምድ እያገኙ ሲሄዱ በአንድ ሳምንት ውስጥ ችግሩ ይቀረፋል።

- ከግንቦት 1 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ በክልሎች ጭምር የነዳጅ ግብይቱ  በኤሌክትሮኒክስ መካሄድ ይጀመራል። አሁን ያጋጠሙ ችግሮች እንዳይደገሙ  ከወዲሁ ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ በሰፊው እየተሰራ ነው።

#የንግድ_እና_ቀጠናዊ_ትስስር_ሚኒስቴር

@tikvahethiopia