TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.5K photos
1.41K videos
203 files
3.84K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የጋምቤላ ክልል የኢሰመኮን ሪፖርት እንደማይቀበለው እና እንደሚያወግዝ በገለፀበት መግለጫ ምን አለ ? - ሚዛናዊነት የጎደለው በመሆኑ ምርመራውን አልቀበለውም፤ በጥብቅም አወግዛለሁ። - ሪፖርቱ የአንድ ክልል የፀጥታ ተቋምን ከተራ የአሸባሪ ቡድን ተላላኪ ጋር በአንድነት ያየ፤ በክልልና በአገር ላይ ይደርስ የነበረ ከፍተኛ ጥቃት በመቀልበስ ሂደት የህይወት መስዋዕትነት የከፈለውን የፀጥታ ተቋሙን በጅምላ የፈረጀ፤…
* ከኢሰመኮ የተለከ መግለጫ !

" በጋምቤላ ከተማ በብሔራዊ ሰብአዊ መብቶች ተቋም እና ሠራተኞች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት በክልሉ የስብአዊ መብቶች አያያዝ ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ምልከታ የሚጥል በመሆኑ የፌዴራል እና የክልሉ የጸጥታ አካላት በአፋጣኝ ሊያስቆሙ ይገባል " - ኢሰመኮ

ከኢሰመኮ መግለጫ የተወሰደ ...

" ... የሪፖርቱን (https://t.me/tikvahethiopia/73948) ይፋ መደረግ ተከትሎ በማኅበራዊ ትስስር ድረ ገጾች እና መገናኛ ብዙኃን የተሳሳተ፤ አነሳሽ እና ዛቻ ያዘሉ መረጃዎች ሲሰራጩ  እንዲሁም በኢሰመኮ ባልደረቦች ላይ ያነጣጠሩ የጥላቻ መልእክቶች ሲዘዋወሩ ቆይተዋል።

ኮሚሽኑ ጉዳዩን ከሚመለከታቸው ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር መፍታት እንደሚቻል በማመን ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቦ ቆይቷል።

ሆኖም መስከረም 25 ቀን 2015 ዓ/ም በቡድን ሆነው የመጡ ሰዎች ወደ ኢሰመኮ ጋምቤላ ጽሕፈት ቤት በመሄድ የተለያዩ የጥፋት ድርጊቶችን የፈጸሙ ሲሆን፣ በኢሰመኮ ባልደረቦች ላይ #ዛቻ እና #ማስፈራሪያ አድርሰዋል።

እንዲሁም በከተማዋ የተለያዩ የስብአዊ መብቶች ሥራዎችን በሚያከናውኑ ሌሎች ድርጅቶች ላይ ተመሳሳይ ጥፋት አድርሰው ድርጅቶቹ ከከተማው ለቅቀው እንዲወጡ አስፈራርተዋል። "

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
° “ ልጄ በሕይወት ስለመኖሯ እርግጠኛ አይደለሁም ” - ልጄ ተጠለፈች ያሉ አባት

° “ የልጅቷን አባት መስለው ቃለ መጠይቅ የሚያደርጉ አሉ ” - የኮሬ ዞን አስተዳዳሪ 

° “ በ2015 ዓ/ም ብቻ 23 ሴቶች ጠለፋና አስገድዶ መድፈር ተፈጽሞባቸዋል ” - የዞኑ ፍትህ ቢሮ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ጠለፋና እየተስፋፋ መሆኑን፣ በዚህም ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት መላክ እንዳልቻሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ይገልጻሉ።

አቶ ወንድሙ ወዬሳ የተባሉ የዞኑ ነዋሪ ባለፈው ወር የማርያም የተባለች ልጃቸውን “ ጉልበተኞች ምሽት 3 ሰዓት በራቸውን ሰብረው ጠልፈው ዱልኬ ” ወደሚባል ቦታ እንደወሰዷት፣ ጠላፊዎቹ ከተያዙ በኋላ ከእስር እንደተለቀቁ በማህበራዊ ሚዲያ ሲገልጹ ተስተውለዋል።

“ ልጄ በሕይወት ስለመኖራ እርግጠኛ አይደለሁም ” ያሉት እኝሁ አባት፣ የጠላፊ ቤተሰቦች ይባስ ብለው ሽምግልና እንደላኩ፣ በዚህም እኝሁ አባት ለጸጥታ አካላት አሳውቀው ቢያሳስሯቸውም እንደተለቀቁ ፣ የጠላፊ ቤተሰቦችም #ፌዝ እና #ዛቻ እያደረሱባቸው በመሆኑ የዞኑ አካላት ፍትህ እንዲሰጧቸው ጠይቀው ነበር።

ይህች ልጅ በጠላፊዎች እጅ 2 ወር በላይ ሆኗታል።

ከዚህ ባለፈ ደስታ ደመቀ የተባለች ልጃገረድ ተጠልፋ የተወሰደች ሲሆን በጠላፊዎች እጅ ከወር በላይ እንደሆናት ተሰምቷል።

እንደ አጠቃላይ ያለውን የጠለፋን ወንጀል በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸውና ስሜ ባይጠቀስ ያሉ የዞሬ ዞን ፍትህ መምሪያ አካል፣ “#ችግሮቹ አሉ። ጠላፋዎቹ ከትምህርት ቤት መልስም ይፈጸማሉ” ሲሉ አረጋግጠዋል።

“ ለሚስትነት የሚጠለፉ አይመስልም። ጠላፊዎቹ ወደ ሱዳን በኩል ወርቅ አለ በጅማ በኩል የሚጓዙበት ‘በዚያ አካባቢ የሚመጡ ሎሌዎች ናቸው’ ነው የሚባለው። ይህ የሚሆነው ጎርካ ወረዳ ነው ” ሲሉ ተናግረዋል።

የየማርያምን ጨምሮ በ2016 ዓ/ም የተፈጸሙትን የጠለፋ ወንጀሎች በተመለከተ ገና መረጃ እያሰባሰቡ መሆኑን ገልጸው፣ “ በ2015 ዓ/ም 23 ሴቶች የጠለፋና አስገድዶ መድፈር ተፈጽሞባቸዋል ” ብለዋል።

ተመሳሳይ ጥያቄ የቀረበላቸው የኮሬ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ በበኩላቸው፣ “ ሚዲያ ላይ የሚባለው መሬት ላይ አለ ወይስ የለም ? የሚለውን በሚባለው ክላስተር ላይ ሂጄ የሃይማኖት አባቶችን፣ አረጋዊያንን ለማማከር ሞክሬአለሁ። አሁን በሚባለው ልክ አይደለም ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ‘ከፓሊስ ጣቢያ ሰው እየተለቀቀ ነው’ የሚለው ነገር ስም ለማጥፋትና ዞኑን ለማጠልሸት እየተደረገ ያለ ነው ” ያሉት አቶ ታረቀኝ፣ “ የልጅቷን አባት መስለው ቃለ መጠይቅ የሚያደርጉ አሉ። ቃለ መጠይቅም ራሱ አርሶ አደር መስሎ የሚሰጥ አለ ” ነው ያሉት።

የኮሬ ዞን ሰላምና ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተፈራ ቦንደሮ በበኩላቸው፣ ከወረዳው ወደ ዞን የቀረበላቸው ቅሬታ እንደሌለ፣ ጎርካ ወረዳ ለመረጃ ሩቅ በመሆኑ ጉዳዩን እንዳልሰሙ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ጥናት

" ሴቶችን በኢንተርኔት ላይ መሳደብ እና ማስፈራራት ኢትዮጵያ ውስጥ የተለመደ የኢንተርኔት ላይ መግባቢያ መንገድ ሆኗል "

ሴንተር ፎር ኢንፎርሜሽን ሬዚሊያንስ / #CIR / ጾታን መሰረት ያደረገ የኦንላይን ጥቃትና ትንኮሳ ተፅእኖዎች ላይ ያጠናውን ሰፊ ጥናት በቅርቡ ይፋ አድርጎ ነበር።

ጥናቱ ሁለት ክፍሎች ይዟል።

የመጀመሪያው የከዚህ ቀደም ጥናቶች ፤ በኢንተርኔት መድረኮች ላይ ንቁ ተሳትፎ ያላቸው / የነበራቸውንና ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ቃለ መጠይቅ የያዘ ነው።

ሁለተኛው በ3 (ቴሌግራም፣ ፌስቡክ፣ X) የማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ጥናት ያደረገ ነው።

በጥናቱ እንደተገለጸው ሴቶች ላይ የሚደርሱ የጥላቻ ንግግሮች በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።

ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ በተደረገው ጥናት ምን ተገኘ ?

ጥናቱ በ4 ቋንቋዎች (አማርኛ ፣ አፋን ኦሮሞ ፣ ትግርኛ እና እንግሊዘኛ) የጥላቻ ንግግሮችን ከኢንተርኔት ላይ ለመለየት የሚያግዙ 2058 ጥቃት አዘል ቃላቶችን በመምረጥ ተደርጓል።

ቃላቶቹ በተከታታይ ውይይቶች እና ጥናቶች የተለዩ የ " ጥላቻ ንግግር " ን ይገልጻሉ የተባሉ ናቸው።

አጠቃላይ ከተሰበሰበው መረጃ 44.5 በመቶ የብሔር ጥላቻን ሲወክሉ ፤ 30.2 በመቶ ፆታን ኢላማ ያደረጉ ጥላቻ ንግግሮች ናቸው። ከሃይማኖት ጋር የተያያዙ 17.5 ከመቶ ይይዛሉ።

ሴቶች (77.8 ከመቶ) ከወንዶች (22.2 ከመቶ) በላይ የጥላቻ ንግግር ይደረስባቸዋል፡፡

በተጨማሪም ሴቶች (13.5 ከመቶ) ከወንዶች (9.2 ከመቶ) በለይ ‘#ዛቻ’ የያዙ ንግግሮችን ያስተናግዳሉ፡፡

#ስድቦች ’ ከአጠቃላይ ጥቃት 36.6 ከመቶ በመያዝ ዋና ድርሻ የሚይዙ ሲሆን ዛቻና ማስፈራሪያዎች ደግሞ 13.4 ከመቶ ይይዛል፡፡

በቃ ለመጠይቅ የተሳተፉ ሴቶች ምን አሉ?

" በኢንተርኔት ላይ ሴቶችን መሳደብ እና ማስፈራራት ኢትዮጵያ ውስጥ የተለመደ የኢንተርኔት ላይ መግባቢያ መንገድ ሆኗል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከ21 በመቶ በላይ የሚሆኑት የጥናቱ ተሳታፊዎች ፣ ጥቃት ፈጻሚዎች፣ ሃይማኖትን እንደሽፋን ተጠቅመው ጥቃት እንዳደረሱባቸው አንስተዋል።

በደረሰባቸው ጥቃት በማህበራዊ ትሥሥር ድረ-ገጾች ላይ እንዲሁም ከኢንተርኔት ውጪ ያሉ ማሀበራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ እንዲያቆሙ እና ዝምታን እንዲመርጡ መገደዳቸውን ገልጸዋል።

ጥናቱን በዚህ ያገኛሉ👇
https://www.info-res.org/tfgbvinethiopia

@tikvahethiopia