TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከንቲባው እየተፈለጉ ነው...

የብቸና ከተማ ከንቲባ #ከሰሞኑን ከተፈጠረው ግጭት ጋር ተያይዞ #ተጠርጥረው እየተፈለጉ ሲሆን እስካሁን በቁጥጥር ሥር አልዋሉም። እስካሁን ምክትል ከንቲባው፣ የንግድ፣ የገቢዎች፣ የሲቪል ሰርቪስ፣ የቅሬታ ሰሚ፣ የማዘጋጃ ቤትና የገንዘብና ኢኮኖሚ ጽሕፈት ኃላፊዎችና አፈ-ጉባኤ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ከሰሞኑን

(ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት)

- በኢህአዴግ ዘመን የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር የነበሩት አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ፤ " የትምህርት ስልጠና ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር " ሆነው ሰሞኑን ተሹመዋል።

በሌላ የሹመት መረጃ ፤ የቀድሞ የ " ብአዴን " ከፍተኛ አመራር ዶ/ር አለምነው መኮንን የኢትዮጵያ ልማት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል። ሹመቱ ተቋሙን ለ10 ወራት በዋና ዳይሬክተርነት የመጡር አቶ ብሩ ወልዴ ከኃላፊነት በመልቀቃቸው ነው።

- ሰሞኑን አሜሪካ ፣ ብሪታንያ፣ ጀርመን፣ አውስትራሊያ ፣ ዴንማርክ እና ኔዘርላንድስ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እና ግጭት በአስቸኳይ እንዲቆም እና የሰላም ድርድር እንዲጀመር በጋራ ባወጡት መግለጫ ጠይቀዋል።

በመግለጫው ፦

• ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ወታደራዊ ግጭት እንዲቆም ፤ ይህንን ለማድረግ ስምምነት እንዲደረስ፣ 

• የሰብዓዊ እርዳታ እንዲቀርብ

#የኤርትራ_ሠራዊት ከግጭት ተሳትፎው እንዲታቀብ እና ከኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የሆኑት አምባሳደር መለስ ዓለም ፥ " መግለጫው ከዚህ በፊት ከወጡት መግጫዎች የተለየ ነገር የለውም " ብለዋል።

ቃል አቀባዩ ፤  " መንግሥት ሰላም እንዲመጣ ቀደም ሲል የወሰዳቸው የመተማመን ምንፈስ የሚፈጥሩ እርምጃዎች አሉ። " ያሉ ሲሆን " መንግሥት ለሰላም ዝግጁ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

- የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ሞኢቦን በቀለ ከትላንት በስቲያ በቡራዩ ከተማ እና አዲስ አበባ አዋሣኝ (ልዩ ቦታው ሳንሱዚ) ቤታቸው አካባቢ ምሽት 1 ሰዓት ገደማ " ማንነታቸው ባልታወቀ " ሰዎች #በጥይት_ተመተው መገደላቸውን ፓርቲው ገልጿል። አቶ ሞኢቦን በቀለ በጥይት ከተመቱ በኃላ ሆስፒታል ቢገቡም ህይወታቸው ሊተርፍ አልቻለም።  ኦነግ ግድያው ፤ " በገለልተኛ አካል " ይጣራሊኝ ሲል ጠይቋል።

- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፤ መተከል ዞን፤ ማንዱራ ወረዳ #በታጣቂዎች_ጥቃት የወረዳውን አስተዳዳሪ አቶ ሂስ ሄጮን ጨምሮ ስድስት (6) ሰዎች ተገድለዋል። ከሟቾች መካከል ሹፌራቸው እና አንድ የመከላከያ ፤ ሶስት የፌዴራል ፖሊስ ይገኙበታል።

- የኢትዮጵያ መንግስት #ለአይርላንድ በፃፈው ደብዳቤ ሀገሪቱ " በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ደባ እየፈፀመች " መሆኑን በመገልፅ ከዚህ አይነት ድርጊቷ እንድትታቀብ አስጠንቅቋል። ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር ተያያዞ አየርላንድ " ህወሓትን በመደገፍ በተመድ ፀጥታ ም/ቤት ውስጥ ያላትን የተለዋጭ መቀመጫ በመጠቀም በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲፈጠር ግፊት እያደረገች ነው " ብሏል። ከዚህም በተጨማሪ ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ህብረት ጋር ያላት ግንኙነት እንዲሻክር እየተንቀሳቀሰች ነው ሲል ገልጿል። ሀገሪቱ ከዚህ ድርጊቷ እንድትታቀብ አስጠንቅቋል።

NB. አየርላንድ ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዘ በተመድ ፀጥታ ም/ቤት ውይይት እንዲደረግ በተደጋጋሚ ለም/ቤቱ ጥያቄ ከሚያቀርቡ አገራት መካከል ዋነኛዋ ናት።

#ከሰሞኑን ፦ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የተሰባሰቡ እና በአጭሩ የቀረቡ።

@tikvahethiopia
#ከሰሞኑን - ሰሜን ኢትዮጵያ !

ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ ዛሬን ጨምሮ ባለፉት ቀናት ከኢፌድሪ መንግስት ፣ ከአሜሪካ መንግስት ፣ ከተመድ ፣ ከአውሮፓ ህብረት እንዲሁም ከአፍሪካ ህብረት የተሰጡ መግለጫዎች እና ወቅታዊ መረጃዎች ፦

➦ አሜሪካ ባወጣችው መግለጫ ፤ በባለፈው ዓመት ነሃሴ ወር አጋማሽ ላይ " ህወሓት / TPLF " በአማራ ክልል በ " ቆቦ " አካባቢ ዘመቻ ማካሄዱንና በዚህም ጦርነቱ #ዳግም_ለመቀስቀሱ አስተዋፆ ማድረጉን ይህን ተከትሎ ተጨማሪ የሰብአዊ መብት ረገጣ እና ግፎች ተጋላጭነት ከፍ እንዳደረገ ገልፃለች። አሜሪካ የኢትዮጵያ መከላከያ እና የኤርትራ መከላከያ በጋራ የሚያካሂዱትን ወታደራዊ ጥቃት እንዲያቆሙ እና ኤርትራ ጦሯን ከ " ሰሜን ኢትዮጵያ " እንድታስወጣም ጥይቃለች።

                           --------------------

➦ የአፍሪካ ህብረት ( #AU ) ኮሚሽን ሊቀ መንበር ፤ ሙሳ ፋኪ በሰሜን ኢትዮጵያ ውጊያ ውስጥ ያሉ አካላት " ያለምንም ቅድመ ሁኔታ " የተኩስ አቁም እንዲያደርጉ አሳስበው የሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎቶች ወደ ነበሩበት አንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት በደቡብ አፍሪካ ወደ ተጠራው " የሰላም ድርድር " እንዲመጡ ፋኪ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

                          --------------------

➦ የተመድ ዋና ጸኃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ፤ " በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ከቁጥጥር ውጪ እየሆነ ነው። " ሲሉ ተናግረው ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።

" አሁን በኢትዮጵያ ባለው ሁኔታ የማህበራዊ ትስስር እየተበጣጠ ነው ፤ የሲቪሎች ህይወት እየቀጠፈና ውድመት እያስከተለ ያለው ጦርነት ማብቃት አለበት ብለዋል።

" የኤርትራ ኃይሎች ከኢትዮጵያ መውጣት አለባቸው " ያለቱ ጉተሬዝ በትግራይ ክልል ያለው ግጭት አሁኑኑ ማብቃት አለበት ብለዋል።  አሁን በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ወታደራዊ መፍትሄ የለውም ሲሉ ተናግረዋል።

ጦርነቱ እንዲያበቃ ተመድ (UN) የአፍሪካ ህብረትን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑ አረጋግጠው " ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሁን ለሰላም መሰባሰብ አለበት ። " ብለዋል።

በተመሳሳይ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከኤርትራ ሰራዊት ጋር በመተባበር በትግራይ ክልል እያካሄዱት ያለውን  የጋራ ጥቃት እንዲያቆሙ ጠይቋል ፤  የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ሙሉ በሙሉ ለቀው እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል።

ህብረቱ ህወሓት በአማራ እና አፋር አጎራባች ክልሎች ያለውን ጦርነት እንዲያቆሙና ከወታደራዊ ዘመቻ እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

                        --------------------

➦ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፤ " በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ከቁጥጥር ውጪ የወጣ ነገር የለም፤ ሁሉም ነገር በታቀደው መሰረት እየሄደ ነው " ብለዋል።

መንግስት የአፍሪካ ሕብረት ( #AU ) የሰላም ውይይቱ የሚካሄድበትን ቀን እስኪያሳውቅ በመጠባበቅ ላይ ይገኛልም ብለዋል።

" አንዳንዶች በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረው ግጭት ከቁጥጥር ውጪ ሆኗል በሚል እየተጠቀሙበት ያለው አገላለጽ ከእውነት የራቀ ነው " ሲሉ  ገልፀዋል።

" ግጭቱ ወደ አማራና አፋር ክልሎች ተስፋፍቶ ነበር አሁን ያ ነገር የለም፤ የመከላከል እርምጃው በታሰበው መልኩ እየሄደ ይገኛል " ያሉ ሲሆን የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦትና #መሰረታዊ_አገልግሎት እንደሚጀመር አሳውቀዋል።

                        --------------------

➦ ዛሬ ጥቅምት 8 የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መንግስት ባወጣው መግለጫ የመከላከያ ሠራዊት በከተሞች ውስጥ ምንም ዓይነት ጦርነት ሳያካሂድ ፦
- ሽሬ፣ 
- አላማጣ
- ኮረም ከተሞችን እንደተቆጣጠረ ገልጿል።

በመግለጫው ላይ ፤ " የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተከተለው ጥብቅ ወታደራዊ ዲሲፕሊን፣ የሕወሐትን ፕሮፓጋንዳ ሲያስተጋቡ የነበሩ አካላትን ሟርት ያመከነ ነው። " ሲልም ገልጿል።

ከልዩ ልዩ የርዳታ ድርጅቶች ጋር በመሆን መከላከያ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ላይ ርዳታ እንዲደርስ በቂ ዝግጅት መደረጉን የገለፀው መንግስት እርዳታ የማድረሱ ስራ የሽሬ አውሮፕላን ማረፊያን መጠቀምን እንደሚጨምር ገልጿል።

በተጨማሪ በሰሜን ጎንደር ወደ ሽሬ የሚወስደውን እና ከኮምቦልቻ - ደሴ- ወልድያ- ቆቦ- አላማጣ ያለውን መንገድ ለመክፈት እየሠራ መሆኑም አሳውቆ ይሄንን ሥራ የሚያሣልጥ ኮሚቴ ከሚመለከታቸው አካላት ተወጣጥቶ ሥራ ጀምሯል ብሏል።

እነዚህ ሥራዎች ቴክኒካዊ የሆኑ ጥናቶችን እና ግጭት በነበረባቸው አካባቢዎች አገልግሎቶችን ለማስጀመር የሚያስችሉ መሠረታዊ ሥራዎችን ይጨምራል ሲልም አሳውቋል።

                             --------------------

➦ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ህወሓት ለ3ኛ ተከታታይ ጊዜ " ጦርነቱን ሆን ብሎ " በመቀስቀሱ ​​በሰሜን ኢትዮጵያ ላለው ወቅታዊ ሁኔታ ብቸኛ ተጠያቂ ነው ያለ ሲሆን ህወሓት ጊዜ እና ቦታ ከተሰጠው ይህን እንደገና ያደርጋል ብሏል።

በሌላ በኩል መንግስት ከ " ህወሓት " ነፃ ባወጣቸው እና በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ላይ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደርስ ከድጋፍ ከሚያደርጉ አካላት ጋር አብሮ እንደሚሰራ እና የሰብዓዊ ድጋፍ ሰራተኞችን ደህንነት እንደሚያረጋግጥ አሳውቋል።

ምንጭ፦ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መ/ቤት ፣ የአፍሪካ ህብረት ትዊተር ገፅ ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ድረገፅ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የመንግስት ኮሚኒኬሽን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

@tikvahethiopia